• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጳጳሶችና ስደት

June 28, 2016 08:33 pm by Editor 1 Comment

እንዲያውም ርእሱን ካህናትና ስደት ብለው ይሻላል፤ ካህናት የሁሉንም ሃይማኖቶች መሪዎችን ይመለከታል፤ ዓላማዬም ሁሉም የሃይማኖት መሪዎችን የሚነካ ነው፤ ነገር ግን የእኔ እውቀት በክርስትናው ላይ ጎላ ያለ በመሆኑ የክርስቲያኖቹ መሪዎች ላይ ያተኮርኩ ቢመስልም ሁሉንም ይመለከታል፤ በተለይ መነኩሴዎች ላይ የማነጣጥርበትም የተለየ ምክንያት አለኝ፡፡

በመጀመሪያ አንድ መሠረታዊ ነገር ላብራራ፤ እንደማንኛውም ሰው ስለፍርሃትና ስለጥቃት አውቃለሁ፤ በተለያዩ መንገዶች በመርማሪዎች የተሰቃዩ ሰዎች ሲናገሩ ሰምቻለሁ፤ የጻፉትንም አንብቤአለሁ፤ ከሁሉም በላይ ፍርሃት የግል መሆኑን አውቃለሁ፤ በዚህም ምክንያት ሰውን ለምን ፈራህ ብሎ መውቀስም አስቸጋሪ መሆኑ ይገባኛል፤ ስለዚህም ይህንን የምጽፍበት ምክንያት የተሰደዱትን ለመውቀስና እነሱን ዝቅ አድርጌ ራሴን ከፍ ለማድረግ አይደለም፤ ከቃሌ በቀር ይህንን የማረጋግጥበት መንገድ የለም፤ እንዲህ ያለው ዓላማ ምንም ትርፍ የለውም፡፡

የኔ ዓላማ ሁለት ነው፤ አንደኛ የሚቀጥለው ትውልድ ሽሽትንና ስደትን እንደባህል እየወሰደው እንዳይቀጥልና የኢትዮጵያ መራቆት እንዳይባባስ እሪ! ለማለት ነው፤ እሪ! በማለት በተለይ የወጣቶቹን ትኩረት ለመሳብና ከሽሽትና ከስደት ሌላ አማራጭ እንዲፈልጉ ለማሳሰብ ነው፤ ይህንን ለማድረግ ስሞክር የማኅበረሰባዊ ግዴታዬ እስከዛሬ የተሰደዱትን ሰዎች የዜግነትም ሆነ የማኅበረሰባዊ፣ የሃይማኖትም ሆነ የታሪክ፣ የፖሊቲካም ሆነ የኑሮ ኃላፊነትን፣ ተጠያቂነትንና የወላጆችን ክብር አነሣለሁ፤ በዚህ ጽሑፍ ላይ የማተኩረው ከላይ እንደገለጽሁት በካህናት ላይ ነው፡፡

በክብረ ነገሥት ልጀምር፡–

“ለካህናትሰ ሰመዮሙ ጼወ፤ ወዓዲ ለካህናት ሰመዮሙ መኅቶተ፤ ካዕበ ሰመዮሙ ብርሃኖ ለዓለም፣ ወካዕበ ሰመዮሙ ጸሐየ ዘያበርህ ጽልመተ እንዘ ክርስቶስ ጸሐየ ጽድቅ ውስተ አልባቢሆሙ፤

ወካህንሰ ዘቦቱ ልቡና ይገሥጾ ለንጉሥ በእንተ ምግባራት ዘርዕየ ወዘኢርእየሰ እግዚአብሔር ይፈትን ወአልቦ ዘይወቅሶ፤

ወዓዲ ኢይሕምይዎሙ አሕዛብ ለጳጳሳት ወለካህናት እስመ ደቂቀ እግዚአብሔር ወሰብአ ቤቱ እሙንቱ በእንተ ዘገሠጾሙ በእንተ ኃጢአቶሙ ወጌጋዮሙ፤

ወአንተኒ ኦ ካህን ለእመ ርኢከ ዕውቀ ኃጢአቶ ለብእሲ ኢትኅፈር ገሥጾቶ ኢያፍራህከ ሰይፍ ወኢስደት፡፡”

እስቲ ዳዊት ያልደገሙት ይኮላተፉበት! ፍሬ ነገሩ ክብረ ነገሥት በመጀመሪያ ካህናትን በጣም ይክባቸዋል፤ ጨው አላቸው፤ መብራት አላቸው፤ የዓለም ብርሃን አላቸው እውነተኛው ጸሐይ ክርስቶስ በልባቸው ውስጥ ስላለ ጨለማን የሚያበራ የዓለም ብርሃን ይላቸዋል፡፡

ክብረ ነገሥት ክቦ፣ ክቦ አያቆምም፤ ይቀጥልና የካህናትን ግዴታ ይናገራል፤ ልቡና ያለው ካህን በሚያያቸው ጉዳዮች ንጉሡን ይገሥጻል፤ የማያየውን ጉዳይ ግን እግዚአብሔር ይመረምራል፤

ሕዝብ ጳጳሳትንና ካህናትን ማማት ተገቢ አይደለም፣ ስለምን የእግዚአብሔር ልጆችና ቤተሰቦች ናቸው፤

ካህን ሆይ አንተ ግን የሰውን ኃጢአት ስታይ መገሠጽን አትፍራ፤ ሰይፍም ሆነ ስደት አያስፈራህ፡፡

ዳዊትን የደገመ ሁሉ እንደሚያውቀው ፡- ኢይፈርሆ ለእኩይ እስመ አንተ ምስሌየ፤ ይላል፤ አንተ ከኔ ጋር ነህና አልፈራም ማለት ነው፤

እንግዲህ ይህ የክብረ ነገሥት ትእዛዝ በጣም ግልጽ ነው፤ የክርስቶስም ትእዛዝ በጣም ግልጽ ነው፤ ተራራውንም ማዘዝ ትችላላችሁ ይላል፤ ለደቀ መዛሙርቱ ስለእምነታቸው ጎዶሎነት ደጋግሞ ተናግሯል፤ እንግዲህ ስደት የቅንጣት ታህል እምነት መጉደል ያመጣው ፍርሃት አይደለም? ሽሽት የራስን አካላዊና መንፈሳዊ ኃይል መካድ አይደለም? “እስመ አንተ ምስሌየ”ን መካድ አይደለም? መትረየስ ፊት የቆሙትን ጴጥሮስን መካድ አይሆንም?

ወይስ የኛዎቹ ጳጳሳትና ካህናት ሌላ መመሪያ አላቸው? ወይስ አንድ አጭበርባሪ ሰባኪ ልጆቼ እንዲህ አታድርጉ፤ እንዲህም አታድርጉ እያለ ሲሰብክ አንድ በጣም የሚያውቀው ሰው ትኩር ብሎ ሲመለከተው ዓይን ለዓይን ሲጋጠሙ ማርሽ ለወጠና ልጆቼ እኔ እንደምላችሁ አድርጉ እንጂ እኔ እንደማደርገው አታድርጉ አለ ይባላል፡፡

ወደሐዲስ ኪዳንም ገብቶ ብዙ ነገር ማለት ይቻላል፤ ግን በጣም ያሳፍራል፤ በመጀመሪያ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ያፈርሁት አንድ ባሕታዊ በእስጢፋኖስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተገደለና በቤተ ክርስቲያን እንዳይቀበር የተደረገው ሙከራ ነው፤ ሁለተኛው በቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የሙጢኝ ያሉትን የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች  መስቀል የለበሱ ሰዎች አሳልፈው ሲሰጧቸው ነው፡፡

የተሰደዱና ያልተሰደዱ ካህናት ብሎ መለየቱ ዋጋ የለውም፤ ዋጋ የለውም የሚባለው በምእመናኑ፣ በበጎቹ፣ ዓይን ሲታይ ነው፤ በጎቹን ጥለው የሸሹትም “ስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘሀበነ ዘንተ ፀጋ በመዋዕለ ስደትነ።” እያሉ ለራሳቸው ይኖራሉ፤ ያልሸሹትም በሥጋ ነው እንጂ በመንፈስ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጋር መሆናቸው ያጠራጥራል፤ በአንድ በኩል ሲታይ ሁለት ሲኖዶሶች የሚባሉት በአካል የሚገኙት በኢትዮጵያና በአሜሪካ መሆናቸው ነው እንጂ በመንፈስ አንድ ናቸው፤ የዝንጀሮ ቆንጆ!

ይህች ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ልጆችን በትምህርት ስታሳድግ የኖረች፣ ደሀዎችን ስትረዳ አሮጊቶችና ሽማግሌዎችን ስትጦር፣ እናትና አባት የሌላቸውን ልጆችን እያስተማረች የምታሳድግ፣ የኢትዮጵያን ታሪካዊ ቅርሶች ስትጠብቅ የኖረች ዛሬ በብዙ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የሚደረገውን ስትፈጽም የኖረች ነች፤ መንፈሳውያን ሰዎች በነበሩባት ጊዜ፤ ዘመናዊነት በአጠቃላይ ለኢትዮጵያ እንዳልሆናት ሁሉ ለቤተ ክርስቲያኒቱም አልሆናትም፤ የዛሬ ሃምሳና ስድሳ ዓመት ግድም በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት የሠለጠኑትና በኋላም ነገረ መለኮት እንዲማሩ ወደወጭ የተላኩት ሁሉ እያደናቀፋቸው ቤተ ክርስቲያኒቱን ለመርዳት አልቻሉም፤ ቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ትምህርት ቤት ግን ባልተጠበቀበት መስክ ሙያተኞችን አፍርቷል፤ በሕዝብ “ደኅንነት”ና በጦር ሠራዊት ታላላቅ መኮንኖችን አበርክቷል፡፡

በአገር ውስጥ ያሉት ካህናት-ጳጳሳት “በዶልቼ ቪታ” (መለስ ታምራትን ሲያባርረው ስኳር ያለው) ተንደላቅቀው በመኖር ከአገር ውጭ ካሉት አያንሱም፤ አንዳንዶቹም ቀሚስ ለባሾች እዚያም እዚህም እየረገጡ አማርጠዋል፡፡

ወጣቱ ትውልድ ይቺን ታሪካዊ ቤተ ክርስቲያን ለትንሣኤ ማብቃት ያሻዋል፤ እግዚአብሔር ይርዳን!

ስደትን በሚከተሉት ቀልዶች አሳምረውታል!!!

“በሥጋ እንጅ ከቅድስት አገራችን የተሰደድነው፣ ከቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያናችን አልተሰደድንም።”

“የክርስትና ሃይማኖት እንደ ዓለማዊ መንግሥት የግዛት ወሰን የለውምና።”

(ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

(ምንጭ: መስፍን ወልደ ማርያም ብሎግ)

ሰኔ/2008

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. tesfai habte says

    June 29, 2016 11:15 am at 11:15 am

    ሰውን በአንድ እርግ በጥሩ ለመሮጥ ኣይቻልም። ከቻለም ውጤቱ ውድቀቱ እየበዛ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ከኢጣልያኑ የአምስት አመታት የግዛት ነጻ ከወጣ እስከ አሁኑ የመጡ መሪዎች፡ ከዶላር ፍቅር የተያዙ፡ ለራሳቸው ጥቅም እንቺ ለህዝቡ ሃሳብ መምጣት የማይፈልጉ፡ የክርስትና እምነትን ወደሃላ በማድረግ፡ ደም የሚጎርፍ ውግያ መዝመት የሚቀላቸው፡ ( vampire) ከእመነታችን የወጡ የድያብሎስ ልእካን፡ ሳጥነኤሎች፡ ከዋይት ሃውስ ከሚገኘው ሳጥናኤል (ድያብሎስ) ትእዛዝ የሚቀበሉ፡ በቀል፡ ጸብ፡ ፈላጊዎች፡ (ብክሪኽ ኢትዮጵያ ማለት ጥቁር ሰው የሚኖርዋት የጥቁር ምድር ማለት ነው።) ኢትዮጵያ የጥቁሮች ማእከል ከመሆን ቀርቶ፡ የጥቁሮች ዝርያ የማጥፋት ማእከል ያደረጉት የጥቅም ሰዎች መናሃርያ ስለሆነች፡ ሁሉም የጥቁር ዘር ከአፍሪካ እተሰደደ ወደ ኤውሮፓ መጓዙን የመረጠ ዘመን እያለን መሆናችን፡ እነዚ የሳጥናኤል ተከታዮች ከልጸዳ፡ ሰላም ማግኘት ማለት የማይታሰብ ነው። vampire ደም ካልኣገኘ መኖር ስለማችለው፡ እነዚህ የቫምፔር ተከታዮች ከልተደመሰሱ መኖር ኣንችልም!—–ከቫምፔሮች ውግያው ይቀጥላል!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule