እንዴትሀገር (ህዝብ) ይጥፋ? ያለመተማመን ስለዘራን ዘር እንሰበስባለን የማያልቅ ‘መከር’። ‘’መግዛት’’ እውቀት ሆኖ፣ ገንዘብና ሀይል አቋራጭ ጎዳናው ‘መቦልተክ’ ሆኗል። ሃይማኖት ተንቃ ስትሆን መቀለጃ የእግዚአበሄርም ቃል ሆነ ምነገጃ። ሳይሰሩ ያገኙት ሀብት፣ ክብር - ዝና ያስከብር ጀመረ መናቁ ቀረና። ፈረሀ - እግዚአብሄር ከልባችን ወ’ቶ ህገ - አውሬ ይገዛናል ሰው-ከሰው አባልቶ። ለመሾም - መሸለም፣ መክዳት - መከዳዳት ምግባራችን ሆኗል ዋናው ሀይማኖት። እያለን የሌለን ስለሆን ተመፅዋች መጠሪያችን ሆነ እናንተ ለማኞች። እውነት ተገንዞ ስለተቀበረ ውሸት ገዥ ሆነና ሰው ለ’ሱው አደረ። ፍቅርና ሰላም ፈላጊ ስለአጡ ተባረው ሄደዋል በአገር እንዳይመጡ። በሌሎች ደም - እምባ፣ ንዋይ … [Read more...] about እንዴት ሀገር (ህዝብ) ይጥፋ?
Literature
ጽፈኪን
መሰላል
መሰላል መሰላል ለመውጣት አለው ትልቅ ብልሃት፡፡ የላዩን ጨብጦ፣ የታቹን ረግጦ፣ ወደላይ መመልከት፡፡ እጆችን ዘርግቶ በኃይል መንጠራራት፡፡ ጨብጦ መጎተት የላዩን! ላዩ ታች እንዲሆን! አንድ ባንድ እየረገጡ፣ መሰላል የወጡ፡፡ ብልሆች የማይጣደፉ፣ ሞልተዋል በያፋፉ! ዘርግተው የጨበጡትን መርገጥ፣ የመውጣት ሕግ ነው የማይለወጥ ሲወርዱ ግን ያስፈራል፤ የረገጡትን ያስጨብጣል፡፡ (መስፍን ወልደማርያም፣ እንጉርጉሮ፣ 1967) yeKanadaw kebede “በሳቅ ፍርስ አሉ” በሚል ርዕስ ላቀረቡት የግጥም ጨዋታ ዱባለ፣ በለው እና dawit ለጨዋታው ምላሽ ስለሰጣችሁ ከልብ እናመሰግናችኋለን፡፡ የጨዋታውን ደራሲ yeKanadaw kebede እንዲሁ፡፡ ስለ “መሰላል”ስ ምን ትላላችሁ? እስቲ ጨዋታውን አምጡታ!? … [Read more...] about መሰላል
ማነው ተጠያቂው?
ማነው ተጠያቂው? ለኅሊናችን፣ ለትወልድ፣ ለሀገር ሰው - ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤ በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው? ጥቂቶች በቡድን፣ ብዙሀኑን ገፍተው የሰውን ስብዕና፣ ማንነቱን ገፈው፤ በጥይትም ይሁን፣ በታንክ ደፍጥጠው እነሱ እንዲገዙ … ማነው የፈቀደው? ሰለኅሊናችን፣ ስለ እውነት በሀቅ ሰው - ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ። ብዙ በልተው - ብዙ ‘ለማበት’ ብዙ ተግተው - ብዙ ለመሽናት፤ …ለጮማ - ቅርናታቸው… …ለውስኪ - ቅርሻታቸው… …ለእኩይ - ምግባራቸው፤… እንደ አንድ ሰው ሆነው፣ሲቆሙ በአንድነት ለክቡር አላማ፣ ሌላው ሲሆን “ኩበት’’፤ እነሱ ምን ያ’ርጉት?... ምንስ ያቅርቡለት…? ሰው ነኝ የሚል ዜጋ፣ ከተነዳ እንደ ከብት። ሀገርን አፍርሰው፣ ትውልደን አጥፈተው እንድ ቅርጫ ስጋ፣ ህዝብንም … [Read more...] about ማነው ተጠያቂው?
በሳቅ ፍርስ አሉ
በሳቅ ፍርስ አሉ አገራቸውን በመክዳት ወገናቸውን ለመጉዳት ያልነበረ ሕግ ጥሰው በነስብሐት ነጋ – በነ መለስ ተከሰው ሽብርተኛ ሲባሉ ‘በሳቅ ፍርስ አሉ’ አሉ፡፡ ሽ-ሽ-ት በሚል ርዕስ ላቀረብነው የአብዲ ሰኢድ ግጥም ግሩም የሆነ ምላሽ በመስጠት ጨዋታው ሞቅ ደመቅ ላደረጋችሁት dawit፣ ሽማግሌው፣ በለው፣ yeKanadaw kebede እና ዱባለ እጅግ ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡ በዚህ የግጥም ጨዋታችን የዘወትር ተሳታፊ የሆኑት የካናዳው ከበደ (yeKanadaw kebede) “ለሚቀጥለው የግጥም ጨዋታ አድርጓት” ብለው “በሳቅ ፍርስ አሉ” በሚል ርዕስ “አሸባሪ” በመባል ተከስሰው በእስር የሚማቅቁት ወገኖቻችንን በተመለከተ የላኩልንን ግጥም ነው ላሁኑ ጨዋታችን ያቀረብነው፡፡ እስካሁን ግጥም ስናቀርብ የነበረው ከሌሎች ቦታዎች ነበር አሁን ግን የካናዳው ከበደ የራሳቸውን … [Read more...] about በሳቅ ፍርስ አሉ
ሽ – ሽ – ት …!
ሽ - ሽ - ት …! እንደዋዛ ሲከንፍ ዕድሜዬ እኔን ጥሎ ስም ያልዘራሁበትን ወኔዬን ጠቅልሎ እንደ ቀልድ ፤ እንደ ህልም ፤ ሲከስም ወዘናዬ ብ … ን … ! ሲል የኋሊት ጠጉሬ ከላዬ እንደው እንደ ዘበት ልጆች ሲሉኝ ጋሼ መናገር ያምረኛል ዕድሜዬን ቀንሼ፡፡ ይህንንም ግጥም ያገኘነው ከፌስቡክ ላይ ሲሆን ታዋቂው ገጣሚ አብዲ ሰኢድ ነው የገጠመው፡፡ ምስጋናችንን እንቸረዋለን፡፡ በሥራ መደራረብ እንደታሰበው በወቅቱ የግጥም ጨዋታችንን በማዘግየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ ባለፈው “ህልመኛው” በሚል ርዕስ ላወጣነው ግጥም አጸፋ መልስ የሰጣችሁ የዘወትር ገጣሚዎቻችንን yeKanadaw kebede፣ inkopa፣ Tsinat፣ እና አሥራደው ከፈረንሳይ ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ስለ “ሽሽት” ምን ትላላችሁ? ሽሹ! ሽሹ! ወይስ …? እስቲ ጨዋታውን አምጡት? … [Read more...] about ሽ – ሽ – ት …!
ሞተ ያለው ማነው?
ፕ/ር አስራት አስራት ወልደየስን ሞተ ያለው ማነው? በረከቱን ያጣ የሞተ መለስ ነው፣ ፕ/ር አስራት አልሞተም ውሸት ነው፣ ኢትዮጵያን ሲቆርሷት ቁጭብየ እንደ ግርማ አላይም ነው ያለው፣ ታሞነው የሞተው? ማነው የገደለው? ያለ ይመስለኛል ስሙን ቀይረውት አለማየሁ ብለው፡፡ ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል … [Read more...] about ሞተ ያለው ማነው?
ማን ጸሎት ያሳርግ
ወ/ሮ ለምለም ጸጋው በእስልምና ሃይማኖትም ሆነ መብታቸውን ለማስጠበቅ በመናገራቸው በእስር ቤት ለሚማቅቁ ሁሉ በፎቶ አስደግፈው የጻፉትን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ፡፡ … [Read more...] about ማን ጸሎት ያሳርግ
ህልመኛው
ህልመኛው ህልመኛ ነው እርሱ ሳያልም አያድርም፤ ኑሮው ማለም እንጂ ህልሙን ኖሮ አያውቅም፡፡ የሚለውን የቃልኪዳንን ግጥም ፌስቡክ ላይ ያነበበው ታምራት አወቀ (ሚራ) “እሱ” እያለች የገለጸችው እርሱን መስሎት በመባነኑ ከያኔዎቹ ህልሞቹ አንዱን እንካችሁ ብሏል፡፡ ፍሬ አልባ አዝመራ ሕልሜን ከእውኑ ጋር አገናኝቶ ‘ሚያሳይ መሄጃ ጎዳና አቅጣጫ እንጂ የጠፋኝ የሕልም የሕልምማ ተጋድሜ ውዬ፣ ተኝቼ እያደርኩኝ ብዙ ያመረትኩት፣ ሁሌ ‘ሚናፍቀኝ ለሚዛን የሚከብድ፣ ፍሬ ያላፈራ፣ የሕልም አዝመራ አለኝ:: ታምራት አወቀ (ሚራ) 2003 ዓ.ም እናንተስ ምን ትላላችሁ? የምታካፍሉት “የህልም አዝመራ” አላችሁ? ወይስ ሌላ የምትሉት አለ? ባለፈው ኑረዲን ዒሳ እኔ ምን አገባኝ በሚል ርዕስ ላቀረበው ግጥም ምላሽ የሰጣችሁትን Tsinat፤ ሰማኸኝ፤ yeKanadaw kebede (ሁለት … [Read more...] about ህልመኛው
የአላሙዲ ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አዶላ ኑሮ በጭንቅ!
ከሳምንታት በፊት የለገደንቢ ወርቅ ሽያጭ ድራማ!! ወርቃችን እንዴት አላሙዲ እጅ ገባ? በሚል ርዕር ላቀረብነው ጽሑፍ የድረገጻችን አንባቢ አሥራደው የሚከተለውን በግጥም የተከሸነ መልዕክት ልከውልናል፡፡ ተናገር መጋዶ ተናገር ሻኪሶ፤ ወርቅ ወዴት ተጋዘ ላንተ አፈሩ ደርሶ፤ ተናገር ሃዲማ ደግሞም ኡላኡሎ፤ እነማን ዘረፉት የወርቁን አሎሎ?! የወርቁን ቡችላ የለገ ደንቢውን፤ ደብዛውን ንገሩን የደረሰበትን?! እነማን ዘረፉት ? ማንስ ከበረበት?! እነማን ተዝናኑ? ማንስ ጨፈረበት?! ድሃ በደከመ ድሃ በሞተበት፤ ጦሙን እንደዋለ አፈር ተንዶበት:: አካፋና ዶማ ይዘው ሳይቆፍሩ፤ ጨለማ መግፈፊያ ሻማ ሳያበሩ፤ ጠብ ሳይል ላባቸው ባቋራጭ ከበሩ፡ ያገር አንጡራ ሃብት እየመዘበሩ:: በገዛ መሬቱ በተወለደበት፤ ዕትብቱ ተቆርጦ ለተቀበረበት፤ ለወርቁ ባለቤት ምንም ሳይሰሩለት … [Read more...] about የአላሙዲ ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አዶላ ኑሮ በጭንቅ!
ዓዲስ ሰው
ተወዳጁ ገጣሚና ባለቅኔ ጋሽ አሰፋ ገ/ማርያም ረቡዕ ጥቅምት 7 ቀን 2005 ዓም (October 17,2012) የታላቁ ኢትዮጵያዊ ደራሲ የክቡር አቶ ሃዲስ አለማየሁ (ዶ/ር) 103ኛ ቀነ-ልደት (BIRTHDAY) በማስመልከት የጻፉትን ግጥም ልከውልናል፡፡ ግጥሙ ዘመን የማይሽረው በመሆኑ በዚህ ወቅት በድጋሚ አውጥተነዋል (በፎቶ የተከሸነውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) በተጨማሪ በአንድ ወቅት የተቀኙላቸውን በቃላቸው የሚስታውሱትን የአማርኛ መወድስ ቅኔ መርቀውልናል፡፡ ጋሽ አሰፋን ከልብ እናመሰግናለን፡፡ መወድሱ እንዲህ ይነበባል፡- መውደድ ካልቀረ ማፍቀር፤ ወገንና ሃገር፤ እንደ ደራሲው አዲስ ነገር፤ ፍቅር !...እስከ መቃብር! በመጨረሻም “ለወጣቱ ትውልድ መልካም አርአያ የሚሆን ኢትዮጵያዊ እምብዛም በሌለበት በዚህ ጉደኛ ዘመን እንደነ ሃዲስ አለማየሁ የመሳሰሉትንና በየወቅቱ … [Read more...] about ዓዲስ ሰው