• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ

January 22, 2013 06:30 am by Editor 4 Comments

በየከተማው በየገጠሩ

በየጥሻው በየቆንጥሩ

በለጋ ሕይወታችሁ

ገና ፀሐይ ሳትመታችሁ፤

“ነፃነት ነፃነት የምትሹ

ተዋጉለት አትሸሹ።”

እያላችሁ

ቆማችሁ፤

አባራሪ ግንባር

ሆናችሁ

ቀንዲል ብርሃን

ተነስታችሁ፤

ፀሐይዋ በዕርጋታ

በሀገራችን ወጥታ ገብታ፤

ጨለማው ፈርቶ ሸሽቶ

ብርሃን ባገር ሞልቶ

የማይታሰበውና ደረቁ ሀቅ

በውጥረትና በጭንቅ

ሴትና ወንድ ወጣቶች

ሕፃናትና ሽማግሎች፤

የመኖር ሕይወት ትርጉሙን

ለሌሎች ሕይወት መቆምን

አስተምራችሁን ያለፋችሁ

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ።

እሁድ ጥር ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓመተ ምህረት

(ስዕል: የገጣሚው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 24, 2013 12:56 am at 12:56 am

    —————————–
    የጥቁር ደመና ድሃ ቤት ላይ ከባ
    ከደሰሳው ጎጆ ውስጥ እየፈራ እየተባ
    የጥቁር ዓይን ዳሩ በነጭ ተከቦ
    አይኑን አፍጥጦ ያነባል በደቦ!
    እናንት ህልመኞች እራሳችሁን የሰዋችሁ
    ከቆሙት በታች ቀና ብላችሁ ባያችሁ
    በእርግጥ ይህ ነበርን ራዕያችሁ ?
    ቋሚን ይድላው ብላችሁ መሞታችሁ
    እናንተንስ መሬት ያዛችሁ ተመቻችሁ
    ደግመው አፍርሰው አውጥተው ከጣሏችሁ
    ግፍ ነው ሁለተኛ ሞት መች ደላችሁና ቆማችሁ?
    ክብር ለዜጋው በለው!
    ++++++++++++++++

    Reply
  2. ዱባለ says

    January 24, 2013 08:47 pm at 8:47 pm

    ያሰበው ያለመው በጋርዮሽ መኖር
    የሰው ጸባይን ነው ያልተረዳው ነገር
    መኖር የሚችለው ሌላውን በመቅበር
    የሞተው ይሻላል የሰውን ጉድ ሳያይ
    በቁም ለሞተ ነው የዘላለም ስቃይ::

    Reply
  3. YeKanadaw Kebede says

    February 1, 2013 12:26 am at 12:26 am

    ተው እንጂ ወንድም ዓለም
    ለጀግና አይታዘንም
    በታሪካችን ተዘክሮ
    በወስጣችን ተቀብሮ
    ስለ’ሚኖር ዘ’ላለም
    የጀግና ሞት፤ ሞት አይደለም
    ከትንሽ ውሎ ማነሱን
    ከርካሾች ጋር መርከሱን
    ስልተጠየፈ ነው
    እንደከብት እየተነዳ
    ሰበእናው እየተጎዳ
    አለመኖርን የመረጠው
    እና..ወንድም ዓለሜ..
    የሚታዘነው…..ለኛ ነው
    ተምረን ለደነቆርነው
    እያየን ለታወርነው
    ቃላችንን ለበላነው
    ዕምነታችንን ለረሳነው
    ጓዱና ጓዲትማ…
    ጥፍራቸው በጉጥ ሲነቀል
    ሥጋቸው በዘይት ሲቀቀል
    ወፌ-ይላላ ሲገረፉ
    ባፋቸው ደም እየተፉ
    ለጠላት ደስ እንዳይለው፤ ወኔያቸው ሳይደፈር
    ወደ መቃብር የሄዱት እየዘፈኑ ነበር
    እና…ወንድም ዓለሜ…
    አገራችን ለተወሰደው
    ክብራችን ለተዋረደው
    በቁማችን ለሞትነው
    የሚታዘነው…ለኛ ነው

    Jan.2013

    Reply
  4. እስከመቼ says

    February 2, 2013 12:51 am at 12:51 am

    ጎረበጠኝ አልኩኝ እንጂ
    ቆረቆረኝ ዕረፍት ነሳኝ፣
    አቅሌን ሳበው አልኩኝ እንጂ
    ቀን ተሌሊት ሰላም ነፍጎኝ፤
    ሰንደቃቸውን አወሳለሁ
    እላፊያቸውን አደንቃለሁ፤
    አልኩኝ እንጂ በኩራቴ
    ግብራቸውን ተሸክሜ በደረቴ፤
    ሕይወታቸው በውስጤ አድሮ
    ከኔ ሕይወት ተዳምሮ፤
    ተነስ ብሎ ቆጠቆጠኝ
    አልኩኝ እንጂ ቆረቆረኝ፤
    የምን ማዘን በየት አልፎ?
    ተደማምሮ በጣም ገዝፎ
    ማጣቴነው ተሰልፎ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule