• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ

January 22, 2013 06:30 am by Editor 4 Comments

በየከተማው በየገጠሩ

በየጥሻው በየቆንጥሩ

በለጋ ሕይወታችሁ

ገና ፀሐይ ሳትመታችሁ፤

“ነፃነት ነፃነት የምትሹ

ተዋጉለት አትሸሹ።”

እያላችሁ

ቆማችሁ፤

አባራሪ ግንባር

ሆናችሁ

ቀንዲል ብርሃን

ተነስታችሁ፤

ፀሐይዋ በዕርጋታ

በሀገራችን ወጥታ ገብታ፤

ጨለማው ፈርቶ ሸሽቶ

ብርሃን ባገር ሞልቶ

የማይታሰበውና ደረቁ ሀቅ

በውጥረትና በጭንቅ

ሴትና ወንድ ወጣቶች

ሕፃናትና ሽማግሎች፤

የመኖር ሕይወት ትርጉሙን

ለሌሎች ሕይወት መቆምን

አስተምራችሁን ያለፋችሁ

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ።

እሁድ ጥር ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓመተ ምህረት

(ስዕል: የገጣሚው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 24, 2013 12:56 am at 12:56 am

    —————————–
    የጥቁር ደመና ድሃ ቤት ላይ ከባ
    ከደሰሳው ጎጆ ውስጥ እየፈራ እየተባ
    የጥቁር ዓይን ዳሩ በነጭ ተከቦ
    አይኑን አፍጥጦ ያነባል በደቦ!
    እናንት ህልመኞች እራሳችሁን የሰዋችሁ
    ከቆሙት በታች ቀና ብላችሁ ባያችሁ
    በእርግጥ ይህ ነበርን ራዕያችሁ ?
    ቋሚን ይድላው ብላችሁ መሞታችሁ
    እናንተንስ መሬት ያዛችሁ ተመቻችሁ
    ደግመው አፍርሰው አውጥተው ከጣሏችሁ
    ግፍ ነው ሁለተኛ ሞት መች ደላችሁና ቆማችሁ?
    ክብር ለዜጋው በለው!
    ++++++++++++++++

    Reply
  2. ዱባለ says

    January 24, 2013 08:47 pm at 8:47 pm

    ያሰበው ያለመው በጋርዮሽ መኖር
    የሰው ጸባይን ነው ያልተረዳው ነገር
    መኖር የሚችለው ሌላውን በመቅበር
    የሞተው ይሻላል የሰውን ጉድ ሳያይ
    በቁም ለሞተ ነው የዘላለም ስቃይ::

    Reply
  3. YeKanadaw Kebede says

    February 1, 2013 12:26 am at 12:26 am

    ተው እንጂ ወንድም ዓለም
    ለጀግና አይታዘንም
    በታሪካችን ተዘክሮ
    በወስጣችን ተቀብሮ
    ስለ’ሚኖር ዘ’ላለም
    የጀግና ሞት፤ ሞት አይደለም
    ከትንሽ ውሎ ማነሱን
    ከርካሾች ጋር መርከሱን
    ስልተጠየፈ ነው
    እንደከብት እየተነዳ
    ሰበእናው እየተጎዳ
    አለመኖርን የመረጠው
    እና..ወንድም ዓለሜ..
    የሚታዘነው…..ለኛ ነው
    ተምረን ለደነቆርነው
    እያየን ለታወርነው
    ቃላችንን ለበላነው
    ዕምነታችንን ለረሳነው
    ጓዱና ጓዲትማ…
    ጥፍራቸው በጉጥ ሲነቀል
    ሥጋቸው በዘይት ሲቀቀል
    ወፌ-ይላላ ሲገረፉ
    ባፋቸው ደም እየተፉ
    ለጠላት ደስ እንዳይለው፤ ወኔያቸው ሳይደፈር
    ወደ መቃብር የሄዱት እየዘፈኑ ነበር
    እና…ወንድም ዓለሜ…
    አገራችን ለተወሰደው
    ክብራችን ለተዋረደው
    በቁማችን ለሞትነው
    የሚታዘነው…ለኛ ነው

    Jan.2013

    Reply
  4. እስከመቼ says

    February 2, 2013 12:51 am at 12:51 am

    ጎረበጠኝ አልኩኝ እንጂ
    ቆረቆረኝ ዕረፍት ነሳኝ፣
    አቅሌን ሳበው አልኩኝ እንጂ
    ቀን ተሌሊት ሰላም ነፍጎኝ፤
    ሰንደቃቸውን አወሳለሁ
    እላፊያቸውን አደንቃለሁ፤
    አልኩኝ እንጂ በኩራቴ
    ግብራቸውን ተሸክሜ በደረቴ፤
    ሕይወታቸው በውስጤ አድሮ
    ከኔ ሕይወት ተዳምሮ፤
    ተነስ ብሎ ቆጠቆጠኝ
    አልኩኝ እንጂ ቆረቆረኝ፤
    የምን ማዘን በየት አልፎ?
    ተደማምሮ በጣም ገዝፎ
    ማጣቴነው ተሰልፎ!

    Reply

Leave a Reply to እስከመቼ Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሆሩ ጉዱሩ ወለጋ ዞን የጉደኔ ጫላ ሲበሬ ቀበሌ ነዋሪዎች በኦነግ ሸኔ ላይ ጀብዱ ፈፀሙ August 11, 2022 03:04 pm
  • በኢትዮጵያ ግብርና ላይ ግብጽ ለዓመታት የፈጸመችው ሤራ August 10, 2022 10:58 am
  • የስሪ ላንካው “FamilyCracy” – ከመዓቱ እስከ ተውኔቱ August 8, 2022 09:45 am
  • “አበበ እንጂ መቼ ሞተ!”          July 19, 2022 04:57 pm
  • ሸኔ አመራሮቹንና ጠንካራ ይዞታዎቹን እያጣ ነው July 19, 2022 01:55 am
  • የወልቃይት አማራ የተሰቃየባቸው የትህነግ 15 ድብቅ እስር ቤቶች! July 18, 2022 03:13 pm
  • ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች July 17, 2022 05:36 pm
  • “ዛሬ ‘ኃያል ነን’ የሚሉ ሀገራት ኢትዮጵያ ላይ በሚዲያ /በመረጃ/፣ በዲፕሎማሲ፣ በሳይበር እና በተልእኮ የተቀነባበረ ‘ግራጫ ጦርነት’ እያካሄዱባት ነው” ጠ/ሚ ዐቢይ July 7, 2022 10:03 am
  • የኦሮሞ ልሂቃንና ፖለቲከኞች በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን “የዘር ማጥፋት” ወንጀል እንዲያወግዙት አብን ጠየቀ July 6, 2022 01:38 pm
  • “አማራን ኦሮሚያ ውስጥ የመግደል እና የመጨፍጨፍ እቅድ የኦነግ ሳይሆን የኦሮሚያ ብልጽግና ነው” አቶ ሃንጋሳ July 6, 2022 01:53 am
  • “በኢትዮጵያዊያን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ሀገሪቱን ማተራመስ አለብን” አይማን አብድልአዚዝ ግብጻዊው ፖለቲከኛ July 5, 2022 12:57 pm
  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule