• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ

January 22, 2013 06:30 am by Editor 4 Comments

በየከተማው በየገጠሩ

በየጥሻው በየቆንጥሩ

በለጋ ሕይወታችሁ

ገና ፀሐይ ሳትመታችሁ፤

“ነፃነት ነፃነት የምትሹ

ተዋጉለት አትሸሹ።”

እያላችሁ

ቆማችሁ፤

አባራሪ ግንባር

ሆናችሁ

ቀንዲል ብርሃን

ተነስታችሁ፤

ፀሐይዋ በዕርጋታ

በሀገራችን ወጥታ ገብታ፤

ጨለማው ፈርቶ ሸሽቶ

ብርሃን ባገር ሞልቶ

የማይታሰበውና ደረቁ ሀቅ

በውጥረትና በጭንቅ

ሴትና ወንድ ወጣቶች

ሕፃናትና ሽማግሎች፤

የመኖር ሕይወት ትርጉሙን

ለሌሎች ሕይወት መቆምን

አስተምራችሁን ያለፋችሁ

ቆረቆረኝ መቃብራችሁ።

እሁድ ጥር ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓመተ ምህረት

(ስዕል: የገጣሚው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    January 24, 2013 12:56 am at 12:56 am

    —————————–
    የጥቁር ደመና ድሃ ቤት ላይ ከባ
    ከደሰሳው ጎጆ ውስጥ እየፈራ እየተባ
    የጥቁር ዓይን ዳሩ በነጭ ተከቦ
    አይኑን አፍጥጦ ያነባል በደቦ!
    እናንት ህልመኞች እራሳችሁን የሰዋችሁ
    ከቆሙት በታች ቀና ብላችሁ ባያችሁ
    በእርግጥ ይህ ነበርን ራዕያችሁ ?
    ቋሚን ይድላው ብላችሁ መሞታችሁ
    እናንተንስ መሬት ያዛችሁ ተመቻችሁ
    ደግመው አፍርሰው አውጥተው ከጣሏችሁ
    ግፍ ነው ሁለተኛ ሞት መች ደላችሁና ቆማችሁ?
    ክብር ለዜጋው በለው!
    ++++++++++++++++

    Reply
  2. ዱባለ says

    January 24, 2013 08:47 pm at 8:47 pm

    ያሰበው ያለመው በጋርዮሽ መኖር
    የሰው ጸባይን ነው ያልተረዳው ነገር
    መኖር የሚችለው ሌላውን በመቅበር
    የሞተው ይሻላል የሰውን ጉድ ሳያይ
    በቁም ለሞተ ነው የዘላለም ስቃይ::

    Reply
  3. YeKanadaw Kebede says

    February 1, 2013 12:26 am at 12:26 am

    ተው እንጂ ወንድም ዓለም
    ለጀግና አይታዘንም
    በታሪካችን ተዘክሮ
    በወስጣችን ተቀብሮ
    ስለ’ሚኖር ዘ’ላለም
    የጀግና ሞት፤ ሞት አይደለም
    ከትንሽ ውሎ ማነሱን
    ከርካሾች ጋር መርከሱን
    ስልተጠየፈ ነው
    እንደከብት እየተነዳ
    ሰበእናው እየተጎዳ
    አለመኖርን የመረጠው
    እና..ወንድም ዓለሜ..
    የሚታዘነው…..ለኛ ነው
    ተምረን ለደነቆርነው
    እያየን ለታወርነው
    ቃላችንን ለበላነው
    ዕምነታችንን ለረሳነው
    ጓዱና ጓዲትማ…
    ጥፍራቸው በጉጥ ሲነቀል
    ሥጋቸው በዘይት ሲቀቀል
    ወፌ-ይላላ ሲገረፉ
    ባፋቸው ደም እየተፉ
    ለጠላት ደስ እንዳይለው፤ ወኔያቸው ሳይደፈር
    ወደ መቃብር የሄዱት እየዘፈኑ ነበር
    እና…ወንድም ዓለሜ…
    አገራችን ለተወሰደው
    ክብራችን ለተዋረደው
    በቁማችን ለሞትነው
    የሚታዘነው…ለኛ ነው

    Jan.2013

    Reply
  4. እስከመቼ says

    February 2, 2013 12:51 am at 12:51 am

    ጎረበጠኝ አልኩኝ እንጂ
    ቆረቆረኝ ዕረፍት ነሳኝ፣
    አቅሌን ሳበው አልኩኝ እንጂ
    ቀን ተሌሊት ሰላም ነፍጎኝ፤
    ሰንደቃቸውን አወሳለሁ
    እላፊያቸውን አደንቃለሁ፤
    አልኩኝ እንጂ በኩራቴ
    ግብራቸውን ተሸክሜ በደረቴ፤
    ሕይወታቸው በውስጤ አድሮ
    ከኔ ሕይወት ተዳምሮ፤
    ተነስ ብሎ ቆጠቆጠኝ
    አልኩኝ እንጂ ቆረቆረኝ፤
    የምን ማዘን በየት አልፎ?
    ተደማምሮ በጣም ገዝፎ
    ማጣቴነው ተሰልፎ!

    Reply

Leave a Reply to ዱባለ Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule