ቀይ-ሽብር ሲጀምር ከደርግ ዲሞክራሲ ከወያኔ እኩልነት......ከሰማይ ዳቦ ስንጠብቅ ሰብዕናችን ተፍቆ ማንነታችን ተንቆ.....ከዕምነታችን ስንርቅ ውርደታችንን ተመልክተን፤ በቃ ማለት ካቃተን ታስሮ መታረድ አይቀርም እንደ በግ ተጎትተን ----------------- ዘመናት አስቆጥራ ብዙ ትውልድ ተሻግራ መቃብር ዛፍ ሲያበቅል፤ የብሶቱ ቀን ሲርቅ የደም አሻራ ሲጠፋ፤ የወላጅ እምባ ሲደርቅ ያኔ ይመስለኝ ነበር ታሪክ እራሷን የምትደግም ሕብረተ-ሰቡ ሲዘናጋ፤ ሰው ከሐዘኑ ሲያገግም ለካ ተሳስቻለሁ! መፃፍ፤ መናገር ሲከለከል: ማሰር፤ ማሳደድ ሲጀመሩ የሐሰት ዶኩሜንታሪ በቴሊቪዥን ሲሠሩ በጋዜጣ ሲያስፈራሩ፤ … [Read more...] about ቀይ-ሽብር ሲጀምር
Literature
ጽፈኪን
ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ
እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ ሀገርንና ትውልድን የሚያጠፋ እኩይ አመለካከትና ምግባር ይዞ ተነስቶና ተሳክቶለትም የሚገዛ ከኢትዮጵያ ውጭ በአለም ላይ ያለ ሀገርም ሆነ የሚገዛ ህዝብ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግ የገዛ ወገኑንና ሀገሩን በጠላትነት ፈርጆ፣ ታጥቆና ተደራጅቶ የሚወጋና የሚያፈራርስ የለም። እንደ ወያኔ/ኢህአዴግዊ አገዛዝም ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊንን የማጥፋቱንና የመበታተኑን ምግባር እንዲያቆም እሽሩሩ የተባለና እየተለመነ ያለ የለም።..... በልመና ቢሆን..... ፍትህ - እኩልነት በልመና ቢሆን... ነጻነት - አንድነት በልመና ቢሆን.... ሰላምና ሕይወት፤ እመጣ ነበረ- አንች ካለሽበት ትመጭልኝ ነበር - እኔ ካለሁበት ዓለም ይሆን ነበር፣ የሁላችንም ቤት። እንደ ደርግ ያለ አምባገነን መንግስት ሀገሩን በክህደትና በጥላቻ ለተሞሉ፤ እንደ ሻአቢያዊንና እንደ … [Read more...] about ቀባሪ ያጣው የወያኔ/ኢህአዴግ የአገዛዝ ስረአትና ባለቤት የሌላት ኢትዮጵያ
እንደ ሻማ
አንደ ሻማ ነው ማንባት፣ ቀልጦ ጠብ እንደሚለው፤ የነፍሳችንን ስቃይ፣ ይሉኝታ ሳይጋርደው፤ ማስመሰል ሳያርቀው፡፡ እንደ ሻማ ነው መቅለጥ፣ በነበልባል ነዶ በግኖ፤ ሰብእናን በህይወት ጣር፣ ሰርቶ በማደር ፈትኖ፡፡ እንደ ሻማ ነው መብራት፣ ማለቅም እንደ ሻማ፤ ለሌላም ባይሆን ለነፍስ፣ አብርቶ የእውነትን ፋና፡፡ በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ፣ /ፍካት ናፋቂዎች፤1999ዓ.ም/ ባለፈው ሁለት ግጥሞችን አቅርበን ነበር፡፡ “ቅኔ” እና “የማይጠፋ ፍቅር” በሚል ርዕሶች ለቀረቡት ግጥሞች ጨዋታውን በማድመቅ የተቀኛችሁትን እና ማብራሪያም የሰጣችሁትን ተሳታፊዎቻችንን በለው፤ YeKanadaw Kebede፤ አሥረዳው፤ እስከመቼ እና ዱባለ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡ ለዛሬው ደግሞ በግጥም ልተንፍሥ ከተባለ የፌስቡክ ገጽ ይህንን ግጥም አግኝተን ለጨዋታ አቅርበነዋል፡፡ “እንደ … [Read more...] about እንደ ሻማ
ለቅሶ ሳቅ – ሳቅ ለቅሶ
አቅቶን መለወጥ ለቅሶን በደስታ፤ ሃዘን ጠል አልብሶን ሳቅ ደርቦ ኩታ፤ ያንዱን ቤት ገንብቶ የሌላውን ሲያፈርስ፤ አንዱን ሳቅ አጅቦት ሌላው ከፍቶት ሲያለቅስ፤ ለቅሶ ሳቅ - ሳቅ ለቅሶ - እየደባለቀ፤ ግማሽ ጎኑ ሲያለቅስ - ግማሽ ጎኑ ሳቀ:: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ለቅሶ ሳቅ – ሳቅ ለቅሶ
የማይጠፋ ፍቅር
ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድናችን በደቡብ አፍሪካ ያስመዘገበው ውጤት እስካሁን የብዙዎች መነጋገሪያ ዋና ሃሳብ ሆኗል፡፡ በተለይ ከእግር ኳሱ ጋር የታየው ወዳጅነት፤ አብሮነትና ተደጋጋፊነት ፖለቲከኞቻችንን “እንዴት ነገሩ፤ ካልሆነ … ብትሞክሩትስ?” የሚያስብል ሆኗል ቢባል የተጋነነ አይሆንም፡፡ ለዛሬ የግጥም ጨዋታ ይህንኑ መንፈስ የሚያንጸባርቅ ወቅታዊ ጨዋታ እንደሚሆን በማሰብ ከድንቅዬ ገጣሚዎቻችን መካከል ብሌን ከበደ በፌስቡክ ላይ የለቀቀችውን ከታላቅ ምስጋና ጋር እነሆ ብለናል፡፡ ባለፈው “የጠቆሩ ልቦች” በሚል ላቀረብነው ጨዋታ ድንቅዬ ችሎታችሁን በግጥም በመመለስ ጨዋታውን ላስዋባችሁት በለው፣ Alelign፣ Yekanadaw kebede፣ ዱባለና inkopa እጅግ የከበረ ምስጋናችንን እናቀርብላችኋለን፡፡ ክብረት ይስጥልን፡፡ … [Read more...] about የማይጠፋ ፍቅር
ቅኔ
የዘወትር የድረገጽ ጋዜጣችን ተሳታፊ የሆኑት ወዳጃችን ዱባለ፤ አቶ ይድነቃቸው ተሰማ ያባታቸውን የኪነት ስራ አስባስበው ካሳተሙት መጽሕፍ ያገኘሁት የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ቅኔ ነው ብለው ገጣሚ ከሆነ ምስል ጋር የላኩልንን ግጥም ነው፡፡ እንዲህ ይነበባል፡- ጎድን ከዳቢት ስብራዳ ይገባ ነበር ለእንግዳ አያችሁት ወይ ይህን ቀን ታላቅ ታናሽ ሲሆን? … [Read more...] about ቅኔ
ቆረቆረኝ መቃብራችሁ
በየከተማው በየገጠሩ በየጥሻው በየቆንጥሩ በለጋ ሕይወታችሁ ገና ፀሐይ ሳትመታችሁ፤ “ነፃነት ነፃነት የምትሹ ተዋጉለት አትሸሹ።” እያላችሁ ቆማችሁ፤ አባራሪ ግንባር ሆናችሁ ቀንዲል ብርሃን ተነስታችሁ፤ ፀሐይዋ በዕርጋታ በሀገራችን ወጥታ ገብታ፤ ጨለማው ፈርቶ ሸሽቶ ብርሃን ባገር ሞልቶ የማይታሰበውና ደረቁ ሀቅ በውጥረትና በጭንቅ ሴትና ወንድ ወጣቶች ሕፃናትና ሽማግሎች፤ የመኖር ሕይወት ትርጉሙን ለሌሎች ሕይወት መቆምን አስተምራችሁን ያለፋችሁ ቆረቆረኝ መቃብራችሁ። እሁድ ጥር ፲፪ ቀን ፳፻፭ ዓመተ ምህረት (ስዕል: የገጣሚው) … [Read more...] about ቆረቆረኝ መቃብራችሁ
“መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”
በበርካታዎች ዘንድ የተለያዩ ስሞች አሏቸው፤ የአደባባይ ምሁር፣ አንጋፋ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ፣ ጋሼ መስፍን፣ ወዘተ፡፡ በእኛ ግምት ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ የሚለው ገጣሚ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በተለይ በቅርብ ዓመታት ያሳተሟቸው መጻህፍት፣ የጻፏቸው ጦማሮች፣ ወዘተ ይህንን ማዕረግ ሊያሰጥዋቸው ይችላሉ ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡ ፕ/ር መስፍን በህይወት ዘመናቸው ካስተማሩትና ካስተላለፉት ዕውቀት በተጨማሪ እጅግ በርካታ መጻህፍትን በማሳተም ይህንን ለዘመናት የዳበረውን ዕውቀታቸውን ለመጪው ትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ አራት መጻህፍትን አሳትመዋል፡፡ በመጪው ሚያዚያ ወር 83 ዓመታቸውን ከማክበራቸው በፊት ባለቅኔው መስፍን በሰማኒያዎቹ ዕድሜያቸው ይህንን ሁሉ ለማድረግ መብቃታቸው ከጻፉት መጻህፍትና አርቆ … [Read more...] about “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”
“የጠቆሩ ልቦች”
“የጠቆሩ ልቦች” ይቺ አጉል ዘመናይ፣ የወንዜ ልጅ እቱ አፍሪካዊ መልኳ፤ “ደብሯት” ጥቁረቱ ፊቷን በ“ሜክ አፕ” እጇን በእንሶስላ ፀጉሯን ባንዳች ቀለም፣ ቀባችው ልትቀላ፡፡ ግን ባይገባት እንጂ፣ እንዲህ የምትደክም እንዲህ የምትለፋ … የቆዳችን ሳይሆን፣ የልባችን መጥቆር ነው አገር ያጠፋ፡፡ ሰለሞን ሽፈራው “ተወራራሽ ሕልሞች” መጽሐፍ ባለፈው “ሕልም እንኳ የታለ?” በሚል ርዕስ ላወጣነው ጨዋታ ምላሽ በመስጠት ጨዋታውን ላደመቃችሁት ዱባለ፣ በለው፣ inkopa እና Yekanadaw kebede ምስጋናችን እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡ በተለይ በዚህኛው አስደናቂ ቅኔዎችም ተዘርፈዋል፤ ወላድ በድባብ ተሂድና አገራችን አሁንም ባለቅኔዎችንና ጥበበኞችን እንዳላጣች እናንተ ምስክር ናችሁ፡፡ ክብረት ይስጥልን፡፡ ለዚህኛው ጨዋታ ደግሞ እስቲ ተቀኙልን! (ፎቶውን ያገኘነው … [Read more...] about “የጠቆሩ ልቦች”
ሕልም እንኳ የታለ?
ሕልም እንኳ የታለ? በሕልሜ ተኝቼ፣ ሸጋ ሕልም አይቼ በአገሬ በአፍሪካ ዲሞክራሲ በቅሎ ፍትህ፣ እኩልነት፣ መብቱ ተደላድሎ ወገኔ ሲያጣጥም የሰላምን ፍሬ ሽብር ተወግዶ በመላው አገሬ . . . ይህን እያለምኩኝ አልጋ ውስጥ አርፌ . . . ጥይት ቀሰቀሰኝ ከሞቀው እንቅልፌ፡፡ ሰሎሞን ሞገስ (ፋሲል) ከፀሐይ በታች መድብል 2004ዓ.ም “መሰላል” በሚል ርዕስ ላወጣነው የግጥም ጨዋታ ድንቅ ምላሽ በመስጠት ጨዋታውን ላደመቃችሁት በለው፣ ዱባለ፣ አሥራደው (ከፈረንሳይ) እና yeKanadaw kebede ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡ እያንዳንዳችሁ የቋጠራችሁት ግጥም በራሱ የግጥም ጨዋታ ሆኖ ሊቀርብ የሚችል ነው፡፡ በነገራችን ላይ ዛሬ ለጨዋታ ያቀረብነው ግጥም ከዚህ በፊት “ሕልመኛው” በሚል ካወጣነው ጨዋታ ጋር በ“ሕልም” እንኳን የማይገናኝ መሆኑን ለመግለጽ … [Read more...] about ሕልም እንኳ የታለ?