• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንደ ሻማ

February 13, 2013 07:06 am by Editor 3 Comments

አንደ ሻማ ነው ማንባት፣
ቀልጦ ጠብ እንደሚለው፤
የነፍሳችንን ስቃይ፣
ይሉኝታ ሳይጋርደው፤
ማስመሰል ሳያርቀው፡፡

እንደ ሻማ ነው መቅለጥ፣
በነበልባል ነዶ በግኖ፤
ሰብእናን በህይወት ጣር፣
ሰርቶ በማደር ፈትኖ፡፡

እንደ ሻማ ነው መብራት፣
ማለቅም እንደ ሻማ፤
ለሌላም ባይሆን ለነፍስ፣
አብርቶ የእውነትን ፋና፡፡

በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ፣ /ፍካት ናፋቂዎች፤1999ዓ.ም/

ባለፈው ሁለት ግጥሞችን አቅርበን ነበር፡፡ “ቅኔ” እና “የማይጠፋ ፍቅር” በሚል ርዕሶች ለቀረቡት ግጥሞች ጨዋታውን በማድመቅ የተቀኛችሁትን እና ማብራሪያም የሰጣችሁትን ተሳታፊዎቻችንን በለው፤ YeKanadaw Kebede፤ አሥረዳው፤ እስከመቼ እና ዱባለ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡

ለዛሬው ደግሞ በግጥም ልተንፍሥ ከተባለ የፌስቡክ ገጽ ይህንን ግጥም አግኝተን ለጨዋታ አቅርበነዋል፡፡ “እንደ ሻማ”ን እነሆ! ተቀኙበት፤ ቅኔ ዝረፉበት፤ …

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    February 12, 2013 11:29 pm at 11:29 pm

    *************************
    አይ አንቺ ‘ሻማ’ እራስሽን መስዕዋት ያደረገሽ
    መብራት በጠፋ ቀን ሁሉ የሚያበሩሽ
    እነሱ ሲደሰቱ አንቺን እየለኮሱሽ
    ሀዘንም ሲገጥማቸው አንችው ተቃጥለሽ
    ከቶ ማነው አንቺ ቀልጠሽ! አንብተሽ!
    ለሌላውን ብርሃን ሁኚ ብሎ የፈረደብሽ ?
    ***ሻማ !
    ምን ነበር ታዲያ ከአንቺ የሰው ልጅ ቢማር
    ውጭ ሄዶ ከሚቀልጥ ከሚያነባ ከሚማረር
    እንዳይሆን የጋን መብራት እንዳይጠፋ ሳያስተምር
    እንደሻማ ተለኩሶ በርቶ እየታየ ለህዝብ ቢናገር
    ስንት የጨለመባቸው ፍንትው ብሎ በታያቸው ነበር !!።
    *****************
    ከምስጋና ጋር፣ ከሀገረ ካናዳ በለው!

    Reply
    • ቱሉ ፎርሳ (ከነምሳ) says

      February 14, 2013 01:38 am at 1:38 am

      “እንደ ሴቴ ሸረሪት ጽንስ
      ራሴን በራሴ መዋጤ”
      የገዛ ብርሃኔን አስኳል
      እኔው በእኔው መሰልቀጤ፡
      ፍቅር ቢፈልቅ ብዬ እኮ ነው
      ከአለት ልብህ አንዳች ጥጋት
      ጀንበር ቢቀድ ብዬ እኮ ነው
      በልቦናህ የጎህ ንጋት፡
      አንተም ታዲያ ሲደርስ ቀኑ
      ሻማ እንድትሆን ለጭቁኑ
      ለድምፅ አልባው ለምስኪኑ!
      ጧፍ እንድትሆን ልክ እንደኔ
      አፍ እንድትሆን ለወገኔ፡፡
      ( ለእስክንድር ነጋ)

      Reply
  2. ዱባለ says

    February 16, 2013 02:09 am at 2:09 am

    እንደ ሻማ ቀልጦ ብርሀን መስጠት
    ራስን ሰውቶ መሆን ትሩፋት
    ጀግና መሆን በጎ ለሁሉም በረከት
    የሰው ልጅ ምሳሌ መሆን በትጋት
    ለግለሰብ ኣቅም ይሰጣል ብርታት
    ለብዙሀኑ ግን ስንፍና ያወርሳል
    የግል ሀላፊነት እኋላ ይቀራል
    የራሱን እጅ ኣጥፎ የሌላውን ያያል
    ለዚህ የሚበጀን ችቦ መሆንን ነው
    እንጨትን ሰብስቦ በልጥ ማያያዝ ነው
    ሁሉም የየራሱን መሀል መቆለል ነው
    የራስን ለኩሶ ሌላ ማቀጣጠል
    ብርሀን ያበዛል
    ደስታውም ይደምቃል
    ዘላቂም ይሆናል
    ችግር ይቀረፋል
    ሸክምም ይቀላል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule