• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እንደ ሻማ

February 13, 2013 07:06 am by Editor 3 Comments

አንደ ሻማ ነው ማንባት፣
ቀልጦ ጠብ እንደሚለው፤
የነፍሳችንን ስቃይ፣
ይሉኝታ ሳይጋርደው፤
ማስመሰል ሳያርቀው፡፡

እንደ ሻማ ነው መቅለጥ፣
በነበልባል ነዶ በግኖ፤
ሰብእናን በህይወት ጣር፣
ሰርቶ በማደር ፈትኖ፡፡

እንደ ሻማ ነው መብራት፣
ማለቅም እንደ ሻማ፤
ለሌላም ባይሆን ለነፍስ፣
አብርቶ የእውነትን ፋና፡፡

በድሉ ዋቅጅራ (ዶ/ር) ፣ /ፍካት ናፋቂዎች፤1999ዓ.ም/

ባለፈው ሁለት ግጥሞችን አቅርበን ነበር፡፡ “ቅኔ” እና “የማይጠፋ ፍቅር” በሚል ርዕሶች ለቀረቡት ግጥሞች ጨዋታውን በማድመቅ የተቀኛችሁትን እና ማብራሪያም የሰጣችሁትን ተሳታፊዎቻችንን በለው፤ YeKanadaw Kebede፤ አሥረዳው፤ እስከመቼ እና ዱባለ ልባዊ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡

ለዛሬው ደግሞ በግጥም ልተንፍሥ ከተባለ የፌስቡክ ገጽ ይህንን ግጥም አግኝተን ለጨዋታ አቅርበነዋል፡፡ “እንደ ሻማ”ን እነሆ! ተቀኙበት፤ ቅኔ ዝረፉበት፤ …

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    February 12, 2013 11:29 pm at 11:29 pm

    *************************
    አይ አንቺ ‘ሻማ’ እራስሽን መስዕዋት ያደረገሽ
    መብራት በጠፋ ቀን ሁሉ የሚያበሩሽ
    እነሱ ሲደሰቱ አንቺን እየለኮሱሽ
    ሀዘንም ሲገጥማቸው አንችው ተቃጥለሽ
    ከቶ ማነው አንቺ ቀልጠሽ! አንብተሽ!
    ለሌላውን ብርሃን ሁኚ ብሎ የፈረደብሽ ?
    ***ሻማ !
    ምን ነበር ታዲያ ከአንቺ የሰው ልጅ ቢማር
    ውጭ ሄዶ ከሚቀልጥ ከሚያነባ ከሚማረር
    እንዳይሆን የጋን መብራት እንዳይጠፋ ሳያስተምር
    እንደሻማ ተለኩሶ በርቶ እየታየ ለህዝብ ቢናገር
    ስንት የጨለመባቸው ፍንትው ብሎ በታያቸው ነበር !!።
    *****************
    ከምስጋና ጋር፣ ከሀገረ ካናዳ በለው!

    Reply
    • ቱሉ ፎርሳ (ከነምሳ) says

      February 14, 2013 01:38 am at 1:38 am

      “እንደ ሴቴ ሸረሪት ጽንስ
      ራሴን በራሴ መዋጤ”
      የገዛ ብርሃኔን አስኳል
      እኔው በእኔው መሰልቀጤ፡
      ፍቅር ቢፈልቅ ብዬ እኮ ነው
      ከአለት ልብህ አንዳች ጥጋት
      ጀንበር ቢቀድ ብዬ እኮ ነው
      በልቦናህ የጎህ ንጋት፡
      አንተም ታዲያ ሲደርስ ቀኑ
      ሻማ እንድትሆን ለጭቁኑ
      ለድምፅ አልባው ለምስኪኑ!
      ጧፍ እንድትሆን ልክ እንደኔ
      አፍ እንድትሆን ለወገኔ፡፡
      ( ለእስክንድር ነጋ)

      Reply
  2. ዱባለ says

    February 16, 2013 02:09 am at 2:09 am

    እንደ ሻማ ቀልጦ ብርሀን መስጠት
    ራስን ሰውቶ መሆን ትሩፋት
    ጀግና መሆን በጎ ለሁሉም በረከት
    የሰው ልጅ ምሳሌ መሆን በትጋት
    ለግለሰብ ኣቅም ይሰጣል ብርታት
    ለብዙሀኑ ግን ስንፍና ያወርሳል
    የግል ሀላፊነት እኋላ ይቀራል
    የራሱን እጅ ኣጥፎ የሌላውን ያያል
    ለዚህ የሚበጀን ችቦ መሆንን ነው
    እንጨትን ሰብስቦ በልጥ ማያያዝ ነው
    ሁሉም የየራሱን መሀል መቆለል ነው
    የራስን ለኩሶ ሌላ ማቀጣጠል
    ብርሀን ያበዛል
    ደስታውም ይደምቃል
    ዘላቂም ይሆናል
    ችግር ይቀረፋል
    ሸክምም ይቀላል::

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule