• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”

January 9, 2013 02:03 pm by Editor 3 Comments

በበርካታዎች ዘንድ የተለያዩ ስሞች አሏቸው፤ የአደባባይ ምሁር፣ አንጋፋ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ፣ ጋሼ መስፍን፣ ወዘተ፡፡ በእኛ ግምት ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ የሚለው ገጣሚ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በተለይ በቅርብ ዓመታት ያሳተሟቸው መጻህፍት፣ የጻፏቸው ጦማሮች፣ ወዘተ ይህንን ማዕረግ ሊያሰጥዋቸው ይችላሉ ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡

ፕ/ር መስፍን በህይወት ዘመናቸው ካስተማሩትና ካስተላለፉት ዕውቀት በተጨማሪ እጅግ በርካታ መጻህፍትን በማሳተም ይህንን ለዘመናት የዳበረውን ዕውቀታቸውን ለመጪው ትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ አራት መጻህፍትን አሳትመዋል፡፡ በመጪው ሚያዚያ ወር 83 ዓመታቸውን ከማክበራቸው በፊት ባለቅኔው መስፍን በሰማኒያዎቹ ዕድሜያቸው ይህንን ሁሉ ለማድረግ መብቃታቸው ከጻፉት መጻህፍትና አርቆ አሳቢነታቸው በተጨማሪ በአድናቆት ሊጠቀስ የሚገባው የመንፈስ ጥንካሬ ነው፡፡

በመጻህፍትና በመጽሔት ብቻ አልተወሰኑም፤ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ከወጣት እስከ ጎልማሳ ምሁራን በብዛት የማይጠቀሙበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመገልገል አስተዋዩ መስፍን በራሳቸው ብሎግ ላይ ጦማራቸውን እያተሙ በየጊዜው ያስተምሩናል፤ የወደፊቱን አበሳ እንድንወጣ ሥራቸውን ለዘመኑ ወጣት በፍጥነት ያስተላልፋሉ፡፡ ምክንያቱም ለመስፍን “ዝምታ ወርቅ” አይደለም፤ “አያገባኝም” ማለትም መፍትሔ አይደለም፡፡

የአገራችን ታሪክ ፈጽሞ እየተዛባና መስመር እየለቀቀ፤ የሕዝባችን ሞራልና ሰብዓዊነት ዕርቃኑን እየቀረ፣ እጅግ በርካታ ባዕድ ነገሮች እንደ ኢትዮጵያዊ ባህል ለዘመናት እየተጨመሩ ባለበት ባሁኑ ወቅት ፕ/ር መስፍን የሚያሳትሟቸው መጻህፍት በዕድሜያቸው ያካበቱትን ልምድ ለአሁኑ ዘመን ትውልድ ዋቢ ይሆን ዘንድ የተጻፉ ብቻ ሳይሆኑ በህዝባችን ውስጥ ለዘመናት የተንሰራፋውን ችግር ግልጽና ማንም ሊያስተውለው በሚችል መልኩ በትነው የሚስተምሩ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ችግሩ ብቻ አይደለም የሚጽፉት፤ መፍትሔውን ጭምር እንጂ፡፡ “ነቢይ በአገሩ አይከበር” እንደሚባል የአገራችንን አዋቂዎች ድንቅ ሥራዎች ቸል እያልን ወደምዕራባዊያንና ሌሎች የባዕድ ቋንቋ ሥራዎችና ትምህርቶች በማተኮራችን መሠረታዊውን የአገራችንን ችግር በውል ለመለየትና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ቸግሮናል፡፡

ከውጪ በቀጥታ በተቀዱና ለኢትዮጵያውያን ባህልና አኗኗር ፈጽሞ ባዕድ የሆኑ የፖለቲካ አመለካከቶችን በህዝባችን ላይ ተጭነው የሚናገረውን የማያውቅ ሰባኪ ቋንቋውን ለማያስተውል ሕዝብ ሲሰብክ ስንት ዘመን አለፈ?! ችግሩ መጫኑና ከሌሎች መቀዳቱ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ እንዲሆን አለመደረጉ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ የሥልጣኔ ዕድገት፣ ታሪክ፣ ባህል፣ … እንዲመጥን ተደርጎ ኢትዮጵያዊ እንዲሆን ሳይደረግ በመቅረቱ ችግሩ ያለው ችግሩ ላይ ይሁን ወይም መፍትሔው ላይ በውል ሳይታወቅ የሥልጣኔ ቀደምት የነበርን የዓለም ጭራ ሆነናል፡፡ ፕ/ር መስፍን እንደሚሉት ሥልጣንን መግራት አቅቶናል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ የታተሙት የፈላስፋው መስፍን መጻሕፍት “ሥልጣን፤ ባህልና አገዛዝ፤ ዴሞክራሲና ምርጫ”፤ “የክህደት ቁልቁለት” እና “አደጋ ያንዣበበበት የአፍሪካ ቀንድ” ከላይ የጠቀስናቸውን ብቻ ሳይሆን እጅግ ሰፋ ያሉና ጥልቀት ያላቸውን የአገራችንን ጉዳዮች ይዳስሳሉ፡፡ የችግራችንን ምክንያትና ምንጭ ያስረዳሉ፡፡ ግልጽና ለማንም የማያሻማ መፍትሔ ይሰጣሉ፡፡

ሰሞኑን ያሳተሙት “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ” የሚለው መጽሐፍ ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር የሚያውቅና አማርኛ የሚያስተውል ሁሉ ሊያነበው የሚገባ ነው፡፡ “ለምን ግን እኛ ኢትዮጵያውያን እንዲህ ሆንን?” ብሎ የሚጠይቅ ሁሉ የከሸፍንበትን ምክንያትና በየትኛው መስክ እንደከሸፍን ለማወቅ ይህ መጽሐፍ ለዘመናት ሲመኘው የነበረ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ መጽሐፉ ሲጀምር ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ እንዲህ በማለት

ቁም! በመጀመሪያ ለአንባቢው አንድ ማስጠንቀቂያ ልስጥ፤ መጽሐፉ በጠቅላላ፣ በተለይም ይህ መቅድም የከረረ ንዴት መግለጫ ነው፤ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ሁኔታ ያልተናደደ፣ የማይናደድና ያልተበሳጨ፣ ወይም ደልቶት የሞቀው ይህንን መጽሐፍ፣ በተለይም ይህንን መቅድም አያንብበው፤ የረጋውን መንፈሱን ያስሸብረዋል፡፡

ፕ/ር መስፍን መጽሐፍ በማሳተም ለመበልጸግ የሚመኙ ሰው እንዳልሆኑ የሚያስተውል ሁሉ ይህንን መጽሐፍ እዚህ ላይ ማስተዋወቃችን የትርፍ ጉዳይ ሳይሆን ለአገራችንና ለወደፊት ትውልድ ከማሰብ እንደሆነ ለማሳሰብ የሚያስፈልግ አይመስለንም፡፡ ስለሆነም መጽሐፉም ሆነ ሌሎች መጽሐፎቻቸውን በአሜሪካ አገር ትርፍ ላይ መሠረት ባላደረገ ነገር ግን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ሙያው የሚጠይቀው ወጪ ወጥቶባቸው ታትመው ስላሉ በቀጥታ ከአሳታሚዎቹ ወይም ከሕጋዊ ወኪሎቻቸው መግዛት አንድኛው የዜግነት ግዴታ እንደሆነ በግልጽ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ በተለያየ መልኩ በርካሽና ጥራቱን ባልጠበቀ ሁኔታ እያሳተሙ ለጥቂት ትርፍ መሯሯጥና ህጋዊ ሻጭ መስሎ የራስን ኪስ ለማደለብ መሞከር አንዱ የሥነምግባር ውድቀታችንና የመክሸፋችን ምልክት ነውና ህገወጥ ሥራን አናደፋፍር፤ በገሃድ ስናይም እንቃወም፡፡ ጥቂት ብሮችን ለማትረፍ ኅሊናችንን አናሸቅጠው!

አዲሱ መጽሐፍ “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”እና ቀደምት የፕ/ር መስፍን መጽሐፍቶች በሚከተሉት መንገዶች ማግኘት ይቻላል፡፡

የመስፍን ወልደማርያም ብሎግ
http://mesfinwoldemariam.wordpress.com/
(617) 543-3462 (ለማንኛውም ጥያቄ ይህንን ስልክ ይደውሉ)

ESAT Store
http://ethsat.com/store/

Tenadam International Market
3817 S George Mason Drive
Falls Church, VA 22041-3763
(703) 933-6038

Dama Restaurant
1503 Columbia Pike
Arlington, VA 22204
(703) 920-3559

Rosalind’s Ethiopian Restaurant
1044 South Fairfax Avenue Los Angeles, CA 90019
(323) 936-2486

Maru Grocery
8353 Park Lane Dallas, TX 75231
(214) 373-6278

Lalibela Cultural Gift Clothing And Variety Store
2257 Massachusetts Ave, Cambridge, MA 02140
(617) 876-2259

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. sintayhu tesfaye says

    February 11, 2013 10:18 am at 10:18 am

    etopyan peopil lov popel

    Reply
    • a says

      March 9, 2013 12:39 am at 12:39 am

      Yes Sintayhu, I agree, we do love people !

      I do appreciate if people strive to bring democracy and good governance to their country, but I wonder why they go to the extent of defacing their own country! To consider an extreme example, we all hate Hitler but we don’t have problem with the Germany.

      Reply
  2. a says

    March 9, 2013 12:41 am at 12:41 am

    (same message as above with minor correction)

    Yes Sintayhu, I agree, we do love people !

    I do appreciate if people strive to bring democracy and good governance to their country, but I wonder why they go to the extent of defacing their own country! To consider an extreme example, we all hate Hitler but we don’t have problem with Germany.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule