• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”

January 9, 2013 02:03 pm by Editor 3 Comments

በበርካታዎች ዘንድ የተለያዩ ስሞች አሏቸው፤ የአደባባይ ምሁር፣ አንጋፋ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ፣ ጋሼ መስፍን፣ ወዘተ፡፡ በእኛ ግምት ለፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ የሚለው ገጣሚ ነው ብለን እናምናለን፡፡ በተለይ በቅርብ ዓመታት ያሳተሟቸው መጻህፍት፣ የጻፏቸው ጦማሮች፣ ወዘተ ይህንን ማዕረግ ሊያሰጥዋቸው ይችላሉ ብንል ማጋነን አይሆንም፡፡

ፕ/ር መስፍን በህይወት ዘመናቸው ካስተማሩትና ካስተላለፉት ዕውቀት በተጨማሪ እጅግ በርካታ መጻህፍትን በማሳተም ይህንን ለዘመናት የዳበረውን ዕውቀታቸውን ለመጪው ትውልድ እያስተላለፉ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ አራት መጻህፍትን አሳትመዋል፡፡ በመጪው ሚያዚያ ወር 83 ዓመታቸውን ከማክበራቸው በፊት ባለቅኔው መስፍን በሰማኒያዎቹ ዕድሜያቸው ይህንን ሁሉ ለማድረግ መብቃታቸው ከጻፉት መጻህፍትና አርቆ አሳቢነታቸው በተጨማሪ በአድናቆት ሊጠቀስ የሚገባው የመንፈስ ጥንካሬ ነው፡፡

በመጻህፍትና በመጽሔት ብቻ አልተወሰኑም፤ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር ከወጣት እስከ ጎልማሳ ምሁራን በብዛት የማይጠቀሙበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመገልገል አስተዋዩ መስፍን በራሳቸው ብሎግ ላይ ጦማራቸውን እያተሙ በየጊዜው ያስተምሩናል፤ የወደፊቱን አበሳ እንድንወጣ ሥራቸውን ለዘመኑ ወጣት በፍጥነት ያስተላልፋሉ፡፡ ምክንያቱም ለመስፍን “ዝምታ ወርቅ” አይደለም፤ “አያገባኝም” ማለትም መፍትሔ አይደለም፡፡

የአገራችን ታሪክ ፈጽሞ እየተዛባና መስመር እየለቀቀ፤ የሕዝባችን ሞራልና ሰብዓዊነት ዕርቃኑን እየቀረ፣ እጅግ በርካታ ባዕድ ነገሮች እንደ ኢትዮጵያዊ ባህል ለዘመናት እየተጨመሩ ባለበት ባሁኑ ወቅት ፕ/ር መስፍን የሚያሳትሟቸው መጻህፍት በዕድሜያቸው ያካበቱትን ልምድ ለአሁኑ ዘመን ትውልድ ዋቢ ይሆን ዘንድ የተጻፉ ብቻ ሳይሆኑ በህዝባችን ውስጥ ለዘመናት የተንሰራፋውን ችግር ግልጽና ማንም ሊያስተውለው በሚችል መልኩ በትነው የሚስተምሩ ናቸው፡፡ ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ችግሩ ብቻ አይደለም የሚጽፉት፤ መፍትሔውን ጭምር እንጂ፡፡ “ነቢይ በአገሩ አይከበር” እንደሚባል የአገራችንን አዋቂዎች ድንቅ ሥራዎች ቸል እያልን ወደምዕራባዊያንና ሌሎች የባዕድ ቋንቋ ሥራዎችና ትምህርቶች በማተኮራችን መሠረታዊውን የአገራችንን ችግር በውል ለመለየትና ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ቸግሮናል፡፡

ከውጪ በቀጥታ በተቀዱና ለኢትዮጵያውያን ባህልና አኗኗር ፈጽሞ ባዕድ የሆኑ የፖለቲካ አመለካከቶችን በህዝባችን ላይ ተጭነው የሚናገረውን የማያውቅ ሰባኪ ቋንቋውን ለማያስተውል ሕዝብ ሲሰብክ ስንት ዘመን አለፈ?! ችግሩ መጫኑና ከሌሎች መቀዳቱ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ እንዲሆን አለመደረጉ ነው፡፡ ለኢትዮጵያ የሥልጣኔ ዕድገት፣ ታሪክ፣ ባህል፣ … እንዲመጥን ተደርጎ ኢትዮጵያዊ እንዲሆን ሳይደረግ በመቅረቱ ችግሩ ያለው ችግሩ ላይ ይሁን ወይም መፍትሔው ላይ በውል ሳይታወቅ የሥልጣኔ ቀደምት የነበርን የዓለም ጭራ ሆነናል፡፡ ፕ/ር መስፍን እንደሚሉት ሥልጣንን መግራት አቅቶናል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ የታተሙት የፈላስፋው መስፍን መጻሕፍት “ሥልጣን፤ ባህልና አገዛዝ፤ ዴሞክራሲና ምርጫ”፤ “የክህደት ቁልቁለት” እና “አደጋ ያንዣበበበት የአፍሪካ ቀንድ” ከላይ የጠቀስናቸውን ብቻ ሳይሆን እጅግ ሰፋ ያሉና ጥልቀት ያላቸውን የአገራችንን ጉዳዮች ይዳስሳሉ፡፡ የችግራችንን ምክንያትና ምንጭ ያስረዳሉ፡፡ ግልጽና ለማንም የማያሻማ መፍትሔ ይሰጣሉ፡፡

ሰሞኑን ያሳተሙት “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ” የሚለው መጽሐፍ ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር የሚያውቅና አማርኛ የሚያስተውል ሁሉ ሊያነበው የሚገባ ነው፡፡ “ለምን ግን እኛ ኢትዮጵያውያን እንዲህ ሆንን?” ብሎ የሚጠይቅ ሁሉ የከሸፍንበትን ምክንያትና በየትኛው መስክ እንደከሸፍን ለማወቅ ይህ መጽሐፍ ለዘመናት ሲመኘው የነበረ ነው ለማለት ይቻላል፡፡ መጽሐፉ ሲጀምር ማስጠንቀቂያ ይሰጣል፤ እንዲህ በማለት

ቁም! በመጀመሪያ ለአንባቢው አንድ ማስጠንቀቂያ ልስጥ፤ መጽሐፉ በጠቅላላ፣ በተለይም ይህ መቅድም የከረረ ንዴት መግለጫ ነው፤ በኢትዮጵያ አጠቃላይ ሁኔታ ያልተናደደ፣ የማይናደድና ያልተበሳጨ፣ ወይም ደልቶት የሞቀው ይህንን መጽሐፍ፣ በተለይም ይህንን መቅድም አያንብበው፤ የረጋውን መንፈሱን ያስሸብረዋል፡፡

ፕ/ር መስፍን መጽሐፍ በማሳተም ለመበልጸግ የሚመኙ ሰው እንዳልሆኑ የሚያስተውል ሁሉ ይህንን መጽሐፍ እዚህ ላይ ማስተዋወቃችን የትርፍ ጉዳይ ሳይሆን ለአገራችንና ለወደፊት ትውልድ ከማሰብ እንደሆነ ለማሳሰብ የሚያስፈልግ አይመስለንም፡፡ ስለሆነም መጽሐፉም ሆነ ሌሎች መጽሐፎቻቸውን በአሜሪካ አገር ትርፍ ላይ መሠረት ባላደረገ ነገር ግን ጥራቱን በጠበቀ መልኩ ሙያው የሚጠይቀው ወጪ ወጥቶባቸው ታትመው ስላሉ በቀጥታ ከአሳታሚዎቹ ወይም ከሕጋዊ ወኪሎቻቸው መግዛት አንድኛው የዜግነት ግዴታ እንደሆነ በግልጽ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ በተለያየ መልኩ በርካሽና ጥራቱን ባልጠበቀ ሁኔታ እያሳተሙ ለጥቂት ትርፍ መሯሯጥና ህጋዊ ሻጭ መስሎ የራስን ኪስ ለማደለብ መሞከር አንዱ የሥነምግባር ውድቀታችንና የመክሸፋችን ምልክት ነውና ህገወጥ ሥራን አናደፋፍር፤ በገሃድ ስናይም እንቃወም፡፡ ጥቂት ብሮችን ለማትረፍ ኅሊናችንን አናሸቅጠው!

አዲሱ መጽሐፍ “መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ”እና ቀደምት የፕ/ር መስፍን መጽሐፍቶች በሚከተሉት መንገዶች ማግኘት ይቻላል፡፡

የመስፍን ወልደማርያም ብሎግ
http://mesfinwoldemariam.wordpress.com/
(617) 543-3462 (ለማንኛውም ጥያቄ ይህንን ስልክ ይደውሉ)

ESAT Store
http://ethsat.com/store/

Tenadam International Market
3817 S George Mason Drive
Falls Church, VA 22041-3763
(703) 933-6038

Dama Restaurant
1503 Columbia Pike
Arlington, VA 22204
(703) 920-3559

Rosalind’s Ethiopian Restaurant
1044 South Fairfax Avenue Los Angeles, CA 90019
(323) 936-2486

Maru Grocery
8353 Park Lane Dallas, TX 75231
(214) 373-6278

Lalibela Cultural Gift Clothing And Variety Store
2257 Massachusetts Ave, Cambridge, MA 02140
(617) 876-2259

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. sintayhu tesfaye says

    February 11, 2013 10:18 am at 10:18 am

    etopyan peopil lov popel

    Reply
    • a says

      March 9, 2013 12:39 am at 12:39 am

      Yes Sintayhu, I agree, we do love people !

      I do appreciate if people strive to bring democracy and good governance to their country, but I wonder why they go to the extent of defacing their own country! To consider an extreme example, we all hate Hitler but we don’t have problem with the Germany.

      Reply
  2. a says

    March 9, 2013 12:41 am at 12:41 am

    (same message as above with minor correction)

    Yes Sintayhu, I agree, we do love people !

    I do appreciate if people strive to bring democracy and good governance to their country, but I wonder why they go to the extent of defacing their own country! To consider an extreme example, we all hate Hitler but we don’t have problem with Germany.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule