
ሕልም እንኳ የታለ?
በሕልሜ ተኝቼ፣
ሸጋ ሕልም አይቼ
በአገሬ በአፍሪካ ዲሞክራሲ በቅሎ
ፍትህ፣ እኩልነት፣ መብቱ ተደላድሎ
ወገኔ ሲያጣጥም የሰላምን ፍሬ
ሽብር ተወግዶ በመላው አገሬ
. . . ይህን እያለምኩኝ አልጋ ውስጥ አርፌ
. . . ጥይት ቀሰቀሰኝ ከሞቀው እንቅልፌ፡፡
ሰሎሞን ሞገስ (ፋሲል) ከፀሐይ በታች መድብል 2004ዓ.ም
“መሰላል” በሚል ርዕስ ላወጣነው የግጥም ጨዋታ ድንቅ ምላሽ በመስጠት ጨዋታውን ላደመቃችሁት በለው፣ ዱባለ፣ አሥራደው (ከፈረንሳይ) እና yeKanadaw kebede ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡ እያንዳንዳችሁ የቋጠራችሁት ግጥም በራሱ የግጥም ጨዋታ ሆኖ ሊቀርብ የሚችል ነው፡፡ በነገራችን ላይ ዛሬ ለጨዋታ ያቀረብነው ግጥም ከዚህ በፊት “ሕልመኛው” በሚል ካወጣነው ጨዋታ ጋር በ“ሕልም” እንኳን የማይገናኝ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
አሁን ደግሞ “ሕልም እንኳን የታለ?” ይለናል የ“አክሱምን አቃጥሉት” እና ሌሎች ግጥሞች ደራሲ ሰለሞን ሞገስ (ፋሲል)፡፡ እናንተስ ምን ትላላችሁ? “ሕልም ዱሮ ቀረ …” ወይስ … እስቲ በግጥም አድርጉታ ጨዋታውን!
አይመሳሰሉም ሕልምና ቅዠት
ሕልም ሰላማዊ ቅዠት ነው እብደት
ሚያስፈራ; ሚያስጮህ; ሚያፈራግጥ ቅዠት
ሕልም ግን በአንጻሩ እጅግ ጥሩ ምኞት
ለድህ ህብት ለጋሽ ሰላም ሰጪ ለህብታም
ላዘነ አጽናኝ አገናኝ ነው ለናፋቂም
ማን ያውቀዋል ዛሬ ጊዜው ተቀያይሯል!!
ባገሬ ኢትዮጵያ ሕልሙ ቅዠት ሆኗል::
ሁሌ እየተመኙ እንቅልፍ ሊወስድዎ
አስራአንደኛው ሰዓት ፍጥጥ ማለትዎ ?
ከቶ ማነው ያለው ሕልም ነው የሌለው
ሁሉ እያሰበ የሚያልምነው የጠፋው
ዲሞክራሲ በዘር የሚበቅል በነበር
አጭደንም ከምረን እንወቃው ነበር
ፍትህ እኩልነት ሰላም ብልፅግና
ያሰብነው ተሳክቶ ፍሬው በአፈራና
ሀገሬን እነደጥንት ባረጓት ገናና
ይች ነበረች ሕልሜ ሁሌም የማልማት
ሕልምን ወደድኩና ማሸለብን ጠላኋት።
*****************
በለው!ከሀገረ ከናዳ ከምስጋና ጋር
ህልምም ሆነ ቅዠት
አይገቡም ከኔ ቤት
ተባይ ፈልቶ በቅቶት
ጠግቦ በሚያድርበት
ስናውዝ አድሬ ስወጣ በጠዋት
ህልም ህልም አትበሉኝ ቁንጫን ጠይቋት
ሕልም የሚፈታ ሰው ጠይቄልህ ነበር
ሰላም፤ዴሞክራሲ፤ፍትሕ፤ ገሌ-መሌ
የሚባለው ነገር
አርጅቷል መሬቱ፤ አይበቅልም እኛ አገር
የጮኸውም ጥይት አንተን ያባነነው
የነቃ፤ ያወቀ፤ ሌላ አስተኝቶ ነው