• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ማነው ተጠያቂው?

December 4, 2012 06:54 pm by Editor Leave a Comment

ማነው ተጠያቂው?

ለኅሊናችን፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

ጥቂቶች በቡድን፣ ብዙሀኑን ገፍተው

የሰውን ስብዕና፣ ማንነቱን ገፈው፤

በጥይትም ይሁን፣ በታንክ ደፍጥጠው

እነሱ እንዲገዙ … ማነው የፈቀደው?

ሰለኅሊናችን፣ ስለ እውነት በሀቅ

ሰው – ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ።

ብዙ በልተው – ብዙ ‘ለማበት’

ብዙ ተግተው – ብዙ ለመሽናት፤

…ለጮማ – ቅርናታቸው…

…ለውስኪ – ቅርሻታቸው…

…ለእኩይ – ምግባራቸው፤…

እንደ አንድ ሰው ሆነው፣ሲቆሙ በአንድነት

ለክቡር አላማ፣ ሌላው ሲሆን “ኩበት’’፤

እነሱ ምን ያ’ርጉት?… ምንስ ያቅርቡለት…?

ሰው ነኝ የሚል ዜጋ፣ ከተነዳ እንደ ከብት።

ሀገርን አፍርሰው፣ ትውልደን አጥፈተው

እንድ ቅርጫ ስጋ፣ ህዝብንም ከፋፍለው

እጃቸውን በደም፣ በህዝብ አምባ ታጥበው፤

“ታላቁ ፍጡር፣ የዘመኑ ጀግና፣ ክቡር …” ከተባሉ

ገዥዎች ምን ያርጉ…?፣ ለምን አይፏልሉ…?

“ለምን እድሜ በቃህ’’ እንገዛለን አይሉ…?

ሰለ እውነት –  በእውነት ፣ ስለ እውነት በሀቅ

ሰው ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ።

የኪነ – ጥበብ ሰው፣ ‘ልሂቅ’ የተባለ

ማንነቱን ከዶ፣ ሞያውን አርክሶ፣ በከርሱ እየማለ፤

“…ሳይጠሩት – አቤት…!’’

“…ሳይልኩት – ወዴት…!’’

ጭራውን ከቆላ፣ “ውሾ!” እየተባለ

ከግራቸው ስር ልሁን፣ ልነጠፍ እያለ

ለገዠዎች እድሜ፣ ሱባኤ ካደረ፣ ሰበካ ከዋለ፤

ማነው ተጠታቄው? … በማን ላይ ይፈረድ?

“ከሀዲን’’ አንግሶ፣ ፍትህ አይወለድ፡፡

ለኅሊናችን ፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

እየተራብ – እያጠገባቸው

እየታረዘ – እያስጌጣቸው፤

እየደህየ – እያከበራቸው

እያዋረዱት – እየተዋረደላቸው፤

እየዘረፉት – እያሞካሻቸው

እየገደሉት – እያኖራቸው፤

በስሙ – በሀብቱ፣ ሲደለልበት

እንደ እቃ ሲቆጠር፣ ሲነገድበት፤

“ዜጋ’’ ነኝ ሲላቸው፣ እየሳቁበት

የ’ኔ እሚለው ሀገር – ቤቱን  ሲያሳጡት፤

“እኔ ምን ቸገረኝ፣ አለልኝ ‘ስደት”

ህሊና ተርቦ፣ ‘ከርስ’ እሚሞላበት

“አደናቅፎኝ ነው፣ የእናቴ መቀነት”

“ሆድ ይፍጀው’’ እያለ፣ ከጠበቀ ምፅ’ት፤

ገዥዎች ምን ያርጉ?…. ምን ይፈይዱለት?

ለመምራት አይደለም፣ ወይም ለመመራት

ለመግዛት እኮ ነው፣  “ገዳይ” ነን ያሉት።

ለኅሊናችን ፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

ፊልጶስ ፊልጶስ
philiposmw@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule