• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ማነው ተጠያቂው?

December 4, 2012 06:54 pm by Editor Leave a Comment

ማነው ተጠያቂው?

ለኅሊናችን፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

ጥቂቶች በቡድን፣ ብዙሀኑን ገፍተው

የሰውን ስብዕና፣ ማንነቱን ገፈው፤

በጥይትም ይሁን፣ በታንክ ደፍጥጠው

እነሱ እንዲገዙ … ማነው የፈቀደው?

ሰለኅሊናችን፣ ስለ እውነት በሀቅ

ሰው – ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ።

ብዙ በልተው – ብዙ ‘ለማበት’

ብዙ ተግተው – ብዙ ለመሽናት፤

…ለጮማ – ቅርናታቸው…

…ለውስኪ – ቅርሻታቸው…

…ለእኩይ – ምግባራቸው፤…

እንደ አንድ ሰው ሆነው፣ሲቆሙ በአንድነት

ለክቡር አላማ፣ ሌላው ሲሆን “ኩበት’’፤

እነሱ ምን ያ’ርጉት?… ምንስ ያቅርቡለት…?

ሰው ነኝ የሚል ዜጋ፣ ከተነዳ እንደ ከብት።

ሀገርን አፍርሰው፣ ትውልደን አጥፈተው

እንድ ቅርጫ ስጋ፣ ህዝብንም ከፋፍለው

እጃቸውን በደም፣ በህዝብ አምባ ታጥበው፤

“ታላቁ ፍጡር፣ የዘመኑ ጀግና፣ ክቡር …” ከተባሉ

ገዥዎች ምን ያርጉ…?፣ ለምን አይፏልሉ…?

“ለምን እድሜ በቃህ’’ እንገዛለን አይሉ…?

ሰለ እውነት –  በእውነት ፣ ስለ እውነት በሀቅ

ሰው ለራሱ ብሎ፣ ‘ራሱን ይጠይቅ።

የኪነ – ጥበብ ሰው፣ ‘ልሂቅ’ የተባለ

ማንነቱን ከዶ፣ ሞያውን አርክሶ፣ በከርሱ እየማለ፤

“…ሳይጠሩት – አቤት…!’’

“…ሳይልኩት – ወዴት…!’’

ጭራውን ከቆላ፣ “ውሾ!” እየተባለ

ከግራቸው ስር ልሁን፣ ልነጠፍ እያለ

ለገዠዎች እድሜ፣ ሱባኤ ካደረ፣ ሰበካ ከዋለ፤

ማነው ተጠታቄው? … በማን ላይ ይፈረድ?

“ከሀዲን’’ አንግሶ፣ ፍትህ አይወለድ፡፡

ለኅሊናችን ፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

እየተራብ – እያጠገባቸው

እየታረዘ – እያስጌጣቸው፤

እየደህየ – እያከበራቸው

እያዋረዱት – እየተዋረደላቸው፤

እየዘረፉት – እያሞካሻቸው

እየገደሉት – እያኖራቸው፤

በስሙ – በሀብቱ፣ ሲደለልበት

እንደ እቃ ሲቆጠር፣ ሲነገድበት፤

“ዜጋ’’ ነኝ ሲላቸው፣ እየሳቁበት

የ’ኔ እሚለው ሀገር – ቤቱን  ሲያሳጡት፤

“እኔ ምን ቸገረኝ፣ አለልኝ ‘ስደት”

ህሊና ተርቦ፣ ‘ከርስ’ እሚሞላበት

“አደናቅፎኝ ነው፣ የእናቴ መቀነት”

“ሆድ ይፍጀው’’ እያለ፣ ከጠበቀ ምፅ’ት፤

ገዥዎች ምን ያርጉ?…. ምን ይፈይዱለት?

ለመምራት አይደለም፣ ወይም ለመመራት

ለመግዛት እኮ ነው፣  “ገዳይ” ነን ያሉት።

ለኅሊናችን ፣ ለትወልድ፣ ለሀገር

ሰው – ስለ ሰው ብሎ፣ እስቲ ሰው ይናገር፤

በዚች ዓለምችን፣ መለኪያው ምንድን ነው

ከገዥና ተገዥ፣ ተጠያቂው ማነው?

ፊልጶስ ፊልጶስ
philiposmw@gmail.com

Filed Under: Literature

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule