የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡ ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡ የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡ “የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ … [Read more...] about ኢህአዴግ እያስታመመ ነው
News
ዜና
ሱዛን ራይስ የቤንጋዚው መዘዝ ሰለባ ሆኑ!
በተባበሩት መንግሥታ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑትና በፕሬዚዳንት ኦባማ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መስሪያቤትን እንዲመሩ ሊታጩ ይችላሉ የተባሉት ቀዳሚ ተወዳዳሪ ሱዛን ራይስ ራሳቸውን ከእጩነት አግልለዋል፡፡ ጉዳዩ ለፕሬዚዳንቱ የፖለቲካ ክስረት፤ ምርጫውን ሲቃወሙ ለነበሩት የሪፓብሊካን ፓርቲ አመራሮች እና በአሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውን ታላቅ ድል ሆኗል፡፡ በቅርቡ በተጠናቀቀው የአሜሪካ ምርጫ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለሁለተኛ ጊዜ መመረጣቸውን ካረጋገጡ በኋላ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሱዛን ራይስ ሂላሪ ክሊንተንን እንደሚተኩ በሰፊው መነገር ተጀመረ፡፡ የፕሬዚዳንቱ ቀዳሚ እጩ መሆናቸው ብዙ ቢነገርላቸውም ከተቃዋሚዎቹ የሪፓብሊካንና ሌሎች ጉዳየኞች የተቃውሞ ድምጽ ለመስማት ግን ብዙም ጊዜ አልወሰደም፡፡ መስከረም 1፤ 2005ዓም በሊቢያ ቤንጋዚ ከተማ የአሜሪካ … [Read more...] about ሱዛን ራይስ የቤንጋዚው መዘዝ ሰለባ ሆኑ!
አንድነት ስየን ሊሰርዝ ወይም ሊያስጠነቅቅ ይችላል
በነባር አመራሮች ሲንከባለል የኖረው “የቅንጅት ወራሽ” አንድነት ፓርቲ ኃላፊነቱንና አመራሩን ለተተኪ ሳያስረክብ መቆየቱ በአብዛኛው ትችት ሲያሰጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በተለይም አቶ ስየ አብርሃ ፓርቲውን በተቀላቀሉ ማግስት በከፍተኛ ኃላፊነት መሰየማቸው አልተወደደለትም ነበር፡፡ በአንድነት ፓርቲ ውስጥም እስከመከፋፈል የዘለቀ ልዩነት መፍጠሩ የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው፡፡ አሁን የረገበ የሚመስለው የፓርቲው የውስጥ ልዩነት፤ በወቅቱ “ዝም አንልም፤ መርህ ይከበር” የሚሉት ኃይሎች የወሰዷቸውን ጽንፈኛ አቋሞች ብዙዎች የሚደግፉት ባይሆኑም ያነሱትን ጥያቄ አግባብነት ግን ይቀበላሉ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ይሁን በሌላ የፓርቲው ተቀዳሚ ምክትል ሊመንበር የነበሩት ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም “እኛ የማማከር አገልግሎት መስጠት አለብን፤ አመራሩን መያዝ ያለበት አዲሱ ትውልድ ነው” በማለት ራሳቸውን … [Read more...] about አንድነት ስየን ሊሰርዝ ወይም ሊያስጠነቅቅ ይችላል
አልአሙዲ ያጠሩትን መሬት ተነጠቁ
የሼክ መሐመድ ሁሴን አልአሙዲ ኢንቨስትመንት ላይ ጥያቄ ያላቸው ጥቂት አይደሉም። የራሳቸውን ህንጻ ከመጨረስ ይልቅ በኪራይ አንድ ህንጻ የሚያሰራ ገንዘብ ለዓመታት ሲከፍሉ ማየትና መስማት የተለመደ ነው። የንግድ ሰዎች ይህንን ዝንባሌያቸውን ከነጋዴ የሚጠበቅ እንዳልሆነ ይናገራሉ። በዙሪያቸው ተሰባስበው ያሉትም ቢሆኑ አመቺ ቦታ ሲያገኙ በዚሁና በሌሎች ጉዳዮች ያሟቸዋል። ጊዮን ሆቴል አጠገብ የተሰራው የናኒ ህንጻ ሲጀመር የተወለደ ህጻን አስራ ሁለት ዓመት ሲሞላው ነው ያለቀው። ከጊዮን ሆቴል ፊትለፊት ለአስራ ሁለት ዓመት ለህንጻው መጋዘን ሆኖ ሲያገለግል የነበረው የአዲስ አበባ ስታዲየም የመኪና ማቆሚያ ተገቢው ክፍያ ሳያገኝ ቢኖርም የሳቸውን ፎቶ በስታዲየም ውስጥ ለመለጠፍ ቀዳሚ ነው። አሁን መለስ መጡና አሳነሷቸው እንጂ ስታዲየሙ የእርሳቸው የሚመስልበት አጋጣሚም … [Read more...] about አልአሙዲ ያጠሩትን መሬት ተነጠቁ
የጎልጉል ቅምሻ
ብልቴን ሰረቁት በምስራቅ ቻይና የዢያንግ አውራጃ የኒቂያዖ ፖሊስ የደረሰው ክስ ግራ የሚጋባ ሆኗል፡፡ የ41ዓመቱ ፌ ሊን “ተኝቼ ሳለ ሌቦች ክፍሌ በርግደው በመግባት ብልቴን ሰረቁት” በማለት ነበር ወንጀሉን ያብራራው፡፡ ሲቀጥልም ሌቦቹ ቤቱ እንደገቡ ጭንቅላቱ ላይ የሆነ ነገር አድርገው ሱሪውን ወደታች ካወረዱ በኋላ ሮጠው እንደጠፉ አስረድቷል፡፡ “በጣም ከመደንገጤ የተነሳ ምንም የተሰማኝ ነገር አልነበረም፤ በኋላ ግን እየደማሁ መሆኔን ሳስተውል ብልቴ ተበጥሶ መሄዱን አስተዋልኩ” ብሏል፡፡ ፖሊስ እንደሚለው ሌቦቹ ሊን በሚያዘወትራቸው በርካታ ሴቶች የቀኑ አፍቃሪዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ግምት በመስጠት ፍለጋውን ቀጥሏል፡፡ ሊን ግን ይህንን የፖሊስ መላምት ካለመቀበል በተጨማሪ የትም ሂያጅ ሳይሆን ታማኝ እንደሆነ ለራሱ ይመሰክራል፡፡ በስርቆቱ በርካታ አስተያየቶች እየተሰጡ ቢሆንም በርካታዎች … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
“በአገራችን የአሸባሪዎች ድር አለ”
ኢትዮጵያን መምራት ከጀመሩ ሶስት ወር ያስቆጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ኢትዮጵያ በአሸባሪዎች የተከበበች አገር መሆኗን አመለከቱ። ኦብነግ በመገንጠል ስም የፖለቲካ ንግድ የሚያካሂድ ድርጅት እንደሆነ ገለጹ። መንግስታቸው ለሚታማበት ጉዳይ ማስተባበያ አቀረቡ። ከአልጃዚራ ቴሌቪዥን እንግሊዝኛው ክፍለጊዜ ጋር ቃለ ምልልስ ያካሄዱት አቶ ሃ/ማርያም ስለ አሸባሪዎች የተናገሩት በአገሪቱ የተነሳው የእስልምና ሃይማኖት ጥያቄና ተቃውሞ ስለቀረበበት የአህባሽን አስተምሮ ተከትሎ ከአያያዝ ጉድለት ጉዳዩ ወደ ቀጠናው እንዳይሸጋገር ስጋት ስለመኖሩ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ ነው። “ጥያቄው የጥቂቶች ነው” በሚል አቃለው በማቅረብ ማብራሪያቸውን ጀመሩ። መንግስት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ በማመልከት አብዛኞቹ ሙስሊሞች ጥያቄያቸው የአስተዳደርና የሲስተም መሆኑንን አመላክተው … [Read more...] about “በአገራችን የአሸባሪዎች ድር አለ”
ከእሁድ እስከ እሁድ
የጉራ ፈርዳ አማሮች መሬታቸው በሃራጅ ተሸጠ ቪኦኤ ሰለባዎችን በማነጋገር እንደዘገበው የጉራ ፈርዳ ነዋሪ አማሮች መሬታቸውን እንዳያርሱ ከተከለከሉ በኋላ መሬታቸው በሃራጅ እየተሸጠባቸው እንደሆነ ይፋ አድርጓል። መሬታቸውን በህጋዊ መንገድ የግላቸው እንዳደረጉና ግብር እየከፈሉ የሚኖሩት ተበዳዮች ርምጃው የተወሰደባቸው ቅንጅትን በመምረጣቸውና ለመኢአድ መረጃ ትሰጣላችሁ በሚል እንደሆነ ተናግረዋል። በተደጋጋሚ መታሰራቸውንና በከሰሳቸውን የተናገሩት የጉራ ፈርዳ ነዋሪ ከእስር ከተፈቱ በኋላ “መሬታችሁን የያዛችሁት በህጋዊ መንገድ ነው” በማለት ለመኢአድ መረጃ መስጠታቸው እንደ ጥፋት እንደተወሰደባቸው አመልክተዋል። በ1997 ምርጫ ወቅት በምስጢር የድምጽ መስጫ ክፍል ውስጥ የጤና ባለሙያዎችን በማስቀመጥ ማንን እንደመረጡ መሰለላቸውንም አመልክተዋል። የሚሸጠውን መሬት የወረዳ፣ የቀበሌ፣ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
ኢህአዴግ ኦነግን እያሰበ አስመራ ላይ አነጣጥሯል!
ኢህአዴግ ከወትሮው በበለጠ አስመራ ላይና አስመራን ተገን ያደረጉ ተቃዋሚዎች አስመልክቶ የተንጠለጠሉ ጉዳዮችን አንድም በሰላማዊ መንገድ፣ አለያም በሃይል ለመቋጨት ፍላጎት እንዳለው ከተለያዩ ምንጮች ይሰማል። ይህንኑ መረጃ የሚያጠናክሩ መግለጫዎችና ዜናዎችም በቀጥታና በተዘዋሪ እየተደመጡ ነው። ድርድሩ የሚካሄደው ኦነግን ጨምሮ ከተለያዩ ድርጅት አመራሮች ጋር በተናጠል ስለመሆኑ ለስርዓቱ ቅርብ የሆኑ ሰዎች ጠቁመዋል። ኦነግንና ኢህአዴግን ለማስማማት ከላይ ታች የሚሉት የአገር ሽማግሌዎች የሚባለውን ቁጥሩ በውል የማይታወቅ ኮሚቴ የሚመሩት ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅን ጨምሮ የቀድሞው የኦነግ አመራር አባቢያ አባጆቢር፣ የኢትዮጵያ መካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት የነበሩት ቄስ ኢተፋ ጎበናና ከሳቸው ጋር የሚሰሩት ኮሚቴዎች፣ በአሜሪካ የወንጌላዊት ሉትራን ቤ/ክ የአፍሪካ ብሔራዊ … [Read more...] about ኢህአዴግ ኦነግን እያሰበ አስመራ ላይ አነጣጥሯል!
የጎልጉል ቅምሻ
ስኳር ለስኳር በሽታ ያጋልጣል “ጣመኝ ድገመኝ” የምንላቸው ዓይነት ብስኩቶች፣ የቸኮሌት ውጤቶች፣ አይስክሬም፣ ብርታት ሰጪ መጠጦች፣ … በከፍተኛ ሁኔታ ለስኳር በሽታ እንደሚያጋልጡ ሳይንስ ደርሼበታለሁ ይለናል፡፡ በእነዚህ የምግብ ውጤቶች ውስጥ የሚገኘው የበቆሎ ስኳር (fructose corn syrup - HFCS) ምግቦቹን ለማጣፈጥ የሚጨመር በመሆኑ ይህንን ተመጋቢ የሆኑ 20በመቶ ለስኳር በሽታ መጋለጣቸው የማይቀር ነው ይላል ውጤቱ፡፡ ከምዕራባውያን አገራት መካከል አሜሪካ በጣፋጩ አወሳሰድ ቀዳሚውን ስትይዝ በአማካይ አንድ ሰው በዓመት 24.78ኪሎ የበቆሎውን ስኳር በተለያዩ ምግቦች አማካኝነት ወደ ሆዱ ይጭናል፡፡ አንድ ካናዳዊ በዓመት 9.13ኪሎ ሲጭን አንድ ጣሊያናዊ ወይም እንግሊዛዊ ከግማሽ ኪሎ በታች እንደሆነ ጥናቱ ጠቁሟል፡፡ ግብጻዊያን 1.6ኪሎ በአማካይ እንደሚጭኑ ያስረዳው … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
ህወሓት ደብረጽዮንን ቀጣይ ጠ/ሚ/ር ያደርጋል!
ከአቶ መለስ መለየት በኋላ ወደ አደባባይ የወጡት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ እንደሚችሉ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ግምታቸውን ሰጡ። አገር ቤት ተቀምጠው በኢህአዴግ ላይ የሰላ ትችት በማሰማት ቀዳሚውን ስፍራ የያዙት በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና መምህርና እንደ ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም የአደባባይ ምሁር በመባል የሚታወቁት ዶ/ር ዳኛቸው ከአዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ይፋ እንዳደረጉት ለግምታቸው ምክንያት ሰጥተዋል። አቶ መለስ በህይወት እያሉ የስልጣን ክፍፍሉን በሶስት ለመመደብ መታሰቡን ሰምተው እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ዳኛቸው፣ ሃሳቡ ከስምምነት ላይ ሊደረስ ባለመቻሉ ተግባራዊ ሊሆን እንዳልቻለ አመልክተዋል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ማንም ይሁን ማን ከዚህ ቀደም እንደነበረው ስልጣኑ በአንድ ሰው ላይ ተጭኖ ሊቀጥል እንደማይችል … [Read more...] about ህወሓት ደብረጽዮንን ቀጣይ ጠ/ሚ/ር ያደርጋል!