የአራት ዓመት ማነጻጸሪያ የቀረበበትን የሪፖርቱ አንያንዳንዱ ክፍል ያስገርማል። የማነጻጸሪያው ማሳረጊያ አስደንጋጭ ነው። መረጃው በአሃዝ፣ በኩኔታ፣ በባህሪው ስደትን ይገልጻል። ትንታኔው በካርታ፣ በስደቱ መነሻና መድረሻ መካከል፣ እንዲሁም በስደት መዳረሻ ላይ የሚያጋጥመውን አፈና፣ ቶርቸር፣ አስገድዶ መደፈር፣ ስቃይ፣ የባህር ሲሳይ የሆኑ ወገኖችን ይጠቅሳል። በተለይ በምስራቅ አፍሪቃ በኤርትራ፣ በኢትዮጵያ በኬንያ፣ በጅቡቲ፣ በሶማሊያና፣ፑንት ላንድ፣ ሶማሊ ላንድ፣ ስደትና የስደትን አስከፊነት በሪፖርቱ ተዘርዝሯል። አገራችን ኢትዮጵያ በስደት የተለዩዋት ዜጎቿ ቁጥር አገር አልባ ከሆነችው ሶማሊያ የሚልቅበትን ሁኔታ ያመላክታል። የዓለም የስደተኞች ኮሚሽን ከፍተኛ ኮሚሽርን /UNHCR/ በመጥቀስ የኖቬምበር 2012 ሪፖርቱን ያቀረበው Regional Mixed Migration … [Read more...] about ከሶማሊያውያን የሚበልጡ ኢትዮጵያዊያን ተሰደዋል
News
ዜና
ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች
በጅቡቲ አዲስ የሚገነባው ወደብ ወጪ በኢትዮጵያ እንደሚሸፈን ተገለጸ። ወደቡ በቀጥታ ከትግራይ ከሚነሳው አዲሱ የባቡር መስመር ጋር እንደሚገናኝም ታውቋል። እያደር ይፋ በመሆን ላይ ያሉት ፕሮጀክቶች አቶ ሃይለማርያም አስመራ ድረስ ለመሄድ ያሳዩትን ፈቃደኛነት “ለኢሳያስ የቀረበ የፖለቲካ አይስክሬም” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተናገሩ፡፡ ባለፈው ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የመሰረት ድንጋይ ለማስቀመጥ ጅቡቲ መጓዛቸውን የዘገቡት ያገር ውስጥ መገናኛዎች ያድበሰበሱት ጉዳይ ይፋ የሆነው ዲሰምበር 18/2012 ለአሜሪካ ሬዲዮ መግለጫ የሰጡት በመቀሌ ዩኒቨርስቲ የአፍሪካ ፖለቲካ ተንታኝና የታሪክ ምሁር የሆኑት ረዳት ፕሮፌሰር አየለ በከሬ ናቸው። ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋ እያደገ በመሄዱ ተጨማሪ ወደቦች እንደሚያስፈልጓት የጠቆሙት እኚሁ ምሁር በጅቡቲ የሚሰራው አዲሱ የታጁራ ወደብ … [Read more...] about ኢትዮጵያ በጅቡቲ ወደብ መገንባት ጀመረች
“እስክንድር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ”
አስራ ስድስት የአውሮፓ ፓርላማ አባላት የተፈራረሙበት የተላዘበ ደብዳቤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ልከዋል። ደብዳቤው ጋዜጠኛ፣ አሳታሚና ጸሃፊ እስክንድር ነጋ ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ ባስቸኳይ እንዲፈታ የሚጠይቅም የሚያሳስብም ነው። ደብዳቤውን አስመልክቶ በዓለም ዙሪያ ላሉ የህሊና እስረኞች ጥብቅና የሚቆመው “የፍሪደም ናው” ነገረ ፈጅ ፓትሪክ ግሪፍተዝ ለቪኦኤ እንደተናገሩት እስክንድር ነጋ እንዲፈታ በመጠየቅ የተጀመረው ስራ እስክንድርን በማስፈታት እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡ እስክንድር ነጋ በየትኛውም መስፈርት ከሽብር ጋር የሚያገናኘው ጉዳይ እንደሌለ ማረጋገጣቸውን አስታውቀዋል። ህጉ የጋዜጠኞችን አፍ ለማዘጋት የተፈበረከ መሆኑንም አስታውቀዋል። አስራ ስድስቱ ፈራሚዎች በላኩት ደብዳቤ የእስክንድር ነጋን ቤት ለመውረስ ስለተጀመረው ሩጫ መረጃ እንዳላቸው አስታውሰው … [Read more...] about “እስክንድር ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ይፈታ”
MEPs demanded “unconditional release of (Eskinder) Nega”
16 Members of the European Parliament Call for the Release of Imprisoned Ethiopian Journalist Eskinder Nega Washington, D.C.: Today, 16 members of the European Parliament issued a public letter to Ethiopian Prime Minster Hailemariam Desalegn expressing their grave concern regarding the continued detention of imprisoned journalist and blogger Eskinder Nega. Arrested in 2011 and detained without access to an attorney for nearly two months, Mr. Nega was sentenced to 18 years in prison under the … [Read more...] about MEPs demanded “unconditional release of (Eskinder) Nega”
መስፍን ኢንጂነሪንግ 30ሚሊዮን ዶላር አተርፋለሁ አለ
በኤፈርት ስር ከታቀፉት የህወሃት የንግድ ተቋሞች መካከል አንዱ የሆነው መስፍን ኢንጂነሪንግ ኢንዱስትሪያል በመጪዎቹ ሁለት ዓመታት ሰላሳ ሚሊዮን ዶላር ለማትረፍ እንደሚሰራ አስታወቀ። ለሶስት ስኳር ፋብሪካዎች የአገዳ መቀቀያ ገንዳ (ቦይሊንግ ሃውስ) ለመስራት የሁለት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ብር ስምምነት አደረገ። የአማራ ክልል በብሄር ብሄረሰቦች ቀን በዓል ድምቀት ላሳየው “ቁርጠኛነት” ተደነቀ፣ ጣና ሃይቅና አካባቢውን የወረረውን አደገኛ አረም ለማጥፋት የአንድ ለአምስት የጥርነፋ አደረጃጀት ማከናወኑ የአካባቢውን አርሶ አደሮች እንዳስደሰተ ተጠቆመ። ኢቲቪ ትላንት ይፋ እንዳደረገው ከተቋቋመ አስራ ዘጠኝ ዓመት የሞላው መስፍን ኢንጂነሪንግ ከስኳር ፋብሪካዎቹ ጋር የገባውን ውል በአስራ አንድ ወራት ውስጥ ለማስረከብ ሃያ አምስት ቶን ብረት ከውጪ አስገብቷል። ስራውን አስመልክቶ መግለጫ … [Read more...] about መስፍን ኢንጂነሪንግ 30ሚሊዮን ዶላር አተርፋለሁ አለ
የጎልጉል ቅምሻ
ካውያ እንደ ስልክ ባለቤቱን በርካታ ሥራዎችን በአንድ ጊዜ መሥራት እንደሚችል በማሳየት ለማስደሰት ቆርጦ የተነሳው ፖላንዳዊው ባል እንዳሰበው አልሆነለትም፡፡ ባለቤቱ ከሥራ ስትመጣ ማከናወን የሚገባውን ሥራዎች በተገቢው ሁኔታ ሳይፈጽም መቅረቱ ሁልጊዜ የሚያሳስበው ባል ቴሌቪዥኑን ለኩሶ ከጎኑ ቢራውን እየተጎነጨ ልብስ መተኮስ ጀመረ፡፡ በመካከል ስልኩ ሲያንቃጭል እጁ ላይ ያለው የጋለ ካውያ ስልክ የመሰለው አባወራ ካውያውን ጆሮው ላይ በመደገን ባደረሰው ጉዳት አሁን በአንድ ጊዜ በርካታ ሥራዎችን ማከናወን በተመለከተ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች እጅግ ደካማ እንደሆኑ አስመስክሯል፡፡ ከእንግዲህ ወደቤት ሥራ እንደማይመለስ የተናገረው ባል ጉዳዩ ሲያት ቀላል እንደሚመስል ከዚህ በኋላ ግን ለባለቤቱ ተገቢውን ክብር እየሰጠ አርፎ እንደሚቀመጥ ተናግሯል፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ አራት ጊዜ ቃለመሃላ … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
“ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ታሰራችሁ”
አገር ቤት ያሉትን ወገኖች ለጊዜው መታደግ ካልተቻለ ቢያንስ ከማንም ተጽዕኖ ወጪ በስደት የሚኖሩትን ኢትዮጵያዊያኖች ለመርዳት ለሚቀርብ ጥያቄ የሚሰጠው ምላሽ የሚያሳዝን እንደሆነ አቶ ሳሙኤል አለባቸው በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን አንድነት ማህበር ሊቀመንበር ገለጹ። አቶ ኦባንግ ሜቶን ማህበሩ በተለይ መጋበዙን አስታወቁ። ከሚያሳዝን መከራ ተርፈው እስራኤል ከደረሱ በኋላ እስር ቤት እንዲቆዩ የተደረጉት ታዳጊዎች መፈታታቸውን አስመልክቶ መግለጫ ያሰራጩት አቶ ሳሙኤል በተለይ ለጎልጉል እንደተናገሩት “በተለያዩ አገራት መከራ እየተቀበሉ ያሉትን ወገኖች መታደግ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቋማትና የፖለቲካ ፓርቲዎች ተግባር ሊሆን እንደሚገባ ጠቅሰው፣ በተግባር ግን ይህንን ማየት” እንዳልቻሉ ተናግረዋል። በእስራኤል እየደረሰ ያለውን የወገኖች ስቃይ አስመልክቶ ለቀረበ ጥሪ ምላሽ ለመስጠት … [Read more...] about “ከኢትዮጵያ ስለመጣችሁ ታሰራችሁ”
ከእሁድ እስከ እሁድ
ገበያ የደራላት ጅቡቲ ታህሳስ 4 ቀን 2005 ዓም ከወደአገርቤት የተዘገበው ዜና መለስን በማስታወሻነት የሚዘክር ሆኗል። ዜናው እንዳለው ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በተገኙበት ጅቡቲ ታጁራ ላይ አዲስ ወደብ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ስነስርዓት አከናውናለች። የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ የወደቡ ግንባታ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የምትፈልገውን የወደብ አገልግሎት በተሟላ ደረጃ እንድታገኝ ያስችላታል ሲሉ የ “ገበያው ደራ” ንግግር አድርገዋል። በስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት ሃይለማርያም ደሳለኝ ፥ አዲሱ የወደብ ግንባታ የኢትዮጵያና የጅቡቲ ህዝብ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑንን ጠቅሰው መናገራቸውን የገለጸው ፋና ብሮድካስቲንግ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት በየብስና በባቡር ትራንስፖርት ፣ በሃይል አቅርቦትና በወደብ አገልግሎት የተቆራኘው የሁለቱ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
ኢህአዴግ እያስታመመ ነው
የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡ ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡ የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡ “የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ … [Read more...] about ኢህአዴግ እያስታመመ ነው
ሱዛን ራይስ የቤንጋዚው መዘዝ ሰለባ ሆኑ!
በተባበሩት መንግሥታ የአሜሪካ አምባሳደር የሆኑትና በፕሬዚዳንት ኦባማ ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መስሪያቤትን እንዲመሩ ሊታጩ ይችላሉ የተባሉት ቀዳሚ ተወዳዳሪ ሱዛን ራይስ ራሳቸውን ከእጩነት አግልለዋል፡፡ ጉዳዩ ለፕሬዚዳንቱ የፖለቲካ ክስረት፤ ምርጫውን ሲቃወሙ ለነበሩት የሪፓብሊካን ፓርቲ አመራሮች እና በአሜሪካ ለሚገኙ ኢትዮጵያውን ታላቅ ድል ሆኗል፡፡ በቅርቡ በተጠናቀቀው የአሜሪካ ምርጫ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ ለሁለተኛ ጊዜ መመረጣቸውን ካረጋገጡ በኋላ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሱዛን ራይስ ሂላሪ ክሊንተንን እንደሚተኩ በሰፊው መነገር ተጀመረ፡፡ የፕሬዚዳንቱ ቀዳሚ እጩ መሆናቸው ብዙ ቢነገርላቸውም ከተቃዋሚዎቹ የሪፓብሊካንና ሌሎች ጉዳየኞች የተቃውሞ ድምጽ ለመስማት ግን ብዙም ጊዜ አልወሰደም፡፡ መስከረም 1፤ 2005ዓም በሊቢያ ቤንጋዚ ከተማ የአሜሪካ … [Read more...] about ሱዛን ራይስ የቤንጋዚው መዘዝ ሰለባ ሆኑ!










