• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከእሁድ እስከ እሁድ

February 4, 2013 09:20 am by Editor 1 Comment

ማክሰኞ ኢቲቪ ድግስ አለበት

“ክርስቲያኖችም ሙስሊሞችም ልባችሁን ጠብቁ”

“እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ” የማስታወቂያው ፍንጣሪ ሃረግ ነው። በአብዛኛው የማህበራዊ ድረገጾች አስቀድመው የሚያስተላልፉት መልዕክት ደግሞ “ክርስቲያኑም ሙስሊሙም ልባችሁን ጠብቁ የሚል” ነው። ኢቲቪ ድግስ አለኝ ሲል ለማክሰኞ ቀጠሮ የያዘለት ዘጋቢ ፊልም አክራሪነት ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ቀደም ብሎ የተሰራጨው ማስታወቂያ ያስረዳል።

ከኢህአዴግ አፈጣጠርና የፕሮፓጋንዳ ልምዱ በመነሳት ለማክሰኞ በቀጠሮ የተዘጋጀውን ዘጋቢ ፊልም “አኬልዳማ ቁጥር ሁለት” በሚል ብዙዎች ሰይመውታል። አንዳንዶች ደግሞ “አዳዲስ ሆዳሞችን እንተዋወቃለን” ሲሉ ፊልሙ በደህንነት ሃይሎች የተቀነባበረ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው ይገልጻሉ። “የውሸት አባት ኢህአዴግና ወዲ ስምዖን የቆመሩት ቁማር” ሲሉ የሚገልጹትም ጥቂት አይደሉም።

“ጂሃዳዊ ሃረከት” የሚል ስያሜ የተሰጠው አዲሱ ዘጋቢ ፊልም ምንም ይሁን ምን ሙሉውን ለመመልከት ፍላጎት ያላቸው ትችቱ ባይቀድም ጥሩ ነው የሚል አቋምም እያራመዱ ነው “የአገራችን ጉዳይ የተወሳሰበ ነውና ልባችንን በመጠበቅ በጥበብ ነገሮችን ልንመረምር ይገባል” የሚል አስተያየት የለጠፉም አሉ። ብዙ እየተባለለት ያለው ይህ አዲስ ፊልም ከመውጣቱ በፊትና በኋላ በመላው አገሪቱ ያሉ ሙስሊሞች ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ለክርስቲያን ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ፍቅር እንዲሰጡና ኢህአዴግ ሊፈጥረው ያሰበውን የጥርጣሬ አመለካከት መስበር እንደሚገባ ተዘግቧል።

ኦማር አል በሺር ኢሳያስን ሊጎበኙ ነው

(ፎቶ:xinhuanet.com)

ዓወት የተሰኘው ድረገጽ በ3/2/2013 ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ለመጎብኘት የሱዳኑ ኦማር አልበሽር አስመራ መግባታቸውን ዘግቧል። በሽር በመከላከያ ሚኒስትራቸውና በደህንነት ሃላፊያቸው ታጅበው ለጉብኝት ሲጓዙ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ እንደተለመደው በደህንነት ሃላፊያቸውና በመከላከያ ሚኒስትራቸው እንዳልታጀቡ ዓወት አስታውቃል። የስራ ጉብኝቱ ለአንድ ቀን እንደሆነም ተመልክቷል።

በኤርትራ አኩራፊ ወታደሮች የማስታወቂያ ሚኒስትርን በመቆጣጠር ህገመንግስታዊ ጥያቄ ካቀረቡ በኋላ በመሪ ደረጃ ፕሬዚዳንት ኢሳያስን ለመገናኘት ቀዳሚ የሆኑት ኦማር አል በሽር የመጀመሪያ መሆናቸውን የጠቆመው ዓወት ስለ ጉብኝቱ አበይት ጉዳይ አለው ነገር የለም። ሁለቱም ፕሬዚዳንቶች በተመሳሳይ ውስጥ ችግር ውስጥ እንዳሉ ያመላከተው ዜና የሁለቱን ጎረቤት አገር መሪዎች የጋዳፊና የሙባረክ እጣፈንታ እንደሚጠብቃቸው አመልክቷል። የአልበሽር ያልተጠበቀ ግንኙነት የሱዳን ወዳጅና ጠበቃ ለሆነችው ኢትዮጵያ ምን እንደምታ ሊኖረው እንደሚችል በዘገባው አልተጠቆመም።

የ“ዳቦ” አመጽ አክሱም ዩኒቨርስቲ ደረሰ

(ፎቶ: ከዩኒቨርሲቲው ድረገጽ)

ዩኒቨርስቲዎች በዳቦ አነሰ፣ ሩዝ ሰለቸን፣ ስጋ አልታኘክ አለን … ጥያቄ አድማ እየመቱ፣ ፖሊስም ወዲያው እየደረሰ ሲደቁሳቸው ጩኸታቸውን መስማት የተለመደ ነው። ይኼው የተለመደ የዳቦ አነሰ ጥያቄ “የተበላሸ የዳቦ ዱቄት” በሚል ተሻሽሎ አክሱም ዩኒቨርስቲ መድረሱን የዘገበው ሪፖርተር ነው። ጥያቄውን ያቀረቡት አስር ተማሪዎች ከዩኒቨርስቲው እንዲባረሩ መደረጉን ተከትሎ ያመጹት ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ወደ ከተማ ሲወጡ አለመግባበት ተፈጥሮ ነበር።

ተማሪዎቹን አነጋግሮ የዘገበው ሪፖርትር፣ ሶስት ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎች ወደ ከተማ ተሰልፈው ሲወጡ ፖሊስ ጥይት ተኩሶባቸዋል። የደረሰው ጉዳት ባይገለጽም ተማሪዎቹ ተቃውሟቸውን እየገለጹ ነው፤ በርካታ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው ወጥተዋል። ከዳቦ ዱቄት መበላሸት ጥያቄ በስተቀር ከጀርባቸው ምንም አይነት የፖለቲካ አጀንዳ እንደሌለ ያስታወቁት ተማሪዎች ጥያቄው የመልካም አስተዳደር ስለሆነ ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ጣልቃ በመግባት ለጥያቄያቸው መፍትሄ እንዲያፈላልግ ተማጽነዋል።

ኢትዮ–ጅቡቲ ምድር ባቡር ሲታደስ በሰዓት 20 ኪሜ “ይከንፋል”

(ፎቶ: ቢቢሲ)

የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ የኢትዮ ጅቡቲን የምድር ባቡር ድርጅት የሞተ፣ የማይጠቅም፣ መፍረስ አለበት በማለት መግለጻቸውን የሪፖርተር የፓርላማ ጋዜጠኛ ጽፏል። “የማይጠቅም ነገር ዝም ብለን ማንከባለል አይጠቅምም” በማለት ድርጅቱ እጣ ፈንታው መፍረስ ብቻ እንደሆነ አመልክተዋል።

በሌላ በከል ለዚሁ መስመር እድሳት የተገኘ ገንዘብ ስራ ላይ ስለመዋሉ ተጠይቀው ሲመልሱ የባቡር መስመሩ ስራ እንዲጀምር በጅቡቲ በኩል ፍላጎት ስላለ ከድሬደዋ ጅቡቲ ያለው የባቡር መስመር ተጠግኖ ስራ እንዲጀምር ከስምምነት መደረሱን አስታውቀዋል። በስምምነቱ መሰረት አሮጌዎቹ ባቡሮች ተጠግነው ስራ ሲጀምሩ ስለሚኖረው ሁለኔታ ሲያስረዱ “ባቡሮቹ ተጠግነው ስራ ሲጀምሩ የሚጓዙት በሰዓት 20 ኪሎሜትር ነው” ብለዋል። አክሳሪና በሙስና የተወሳሰበ ድርጅት እንደሆነ ሚኒስትሩ የገለጹት ይህ ተቋም ለሰራተኞቹ የሚከፍለው ደሞዝ በማጣቱ ቀደም ባሉት ሚኒስትር ትዕዛዝ መሬት የማከራየት ስራ ይሰራ ነበር። በዓለማችን ፈጣን ተብለው ከአንድ እስከ አስር ደረጃ የተሰጣቸው ባቡሮች፤ አስረኛው በሰዓት 300ኪሜ አንደኛው ደግሞ 485 ኪሎሜትር ይጓዛል፡፡

የነጻ ሚዲያ ‘ፎቢያ’

ቀደም ሲል የፍትህ ጋዜጣን በተልካሻ ምክንያቶች የዘጉት ክፍሎች በተመሳሳይ አዲስ ታይምስ መጽሔትን ከህትመት ውጪ አድርገዋል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይህንኑ አስመልክቶ በተለያዩ ድረገጾች ላይ ባሰራጨው ጽሁፍ ውሳኔው ከአምባገነንነት እሳቤና ከጭፍን ፍርሃት እንደሚመነጭ አመልክቷል።

አገርቤት አገዛዙ አፍንጫ ስር በመሆን ኢህአዴግን በሰላ ብዕር በመተቸት የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተመስገን አቶ መለስ ከአንድ ክፍለጦር በላይ የተለየ ሃሳብና ነጻ ሚዲያ እንደሚፈሩ ይናገራል። ወራሾቻቸውም ከእርሳቸው በባሰ አምባገነኖች እንደሆኑ ያመላከተው ተመስገን ለነጻ ሚዲያ ካላቸው ፍርሃቻ የተነሳ ጭፍን አምባገነን መሆናቸውን ገልጿል። ከዚህ አቋማቸው የተነሳ “አገሪቱን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየገፏት ነው” ብሏል፡፡

“የመለስ ራዕይ በአዲስ ራዕይ መጽሄት ተተገበረ” በሚል ርዕስ ተመስገን ባሰራጨው ጽሁፍ ለአዲስ ራዕይ መጽሄት መዘጋት የቀረቡት ሶስት ምክንያቶች ተራና ፍጹም ተልካሻ መሆናቸውን አንባቢ እንዲፈርድ በዝርዝር አስቀምጧል።

አስራት ጣሴ ሬድዋንን አወገዙ

(ፎቶ: የአስራት ጣሴ Facebook)

ለምርጫ ቦርድ ቅሬታቸውን አቅርበው መልስ ስላልተሰጣቸው ራሳቸውን ከምርጫ ያገለሉት 39 ፓርቲዎች ተወካይ አቶ አስራት ጣሴ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑትን አቶ ሬድዋን ሁሴንን አወገዙ። አቶ አስራት ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ በሰጡት ማብራሪያ አቶ ሬድዋን ለመንግስት መገናኛዎች በሰጡት መግለጫ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ክብር ነክተዋል፤ ተሳድበዋል። ይህ ደግሞ “ከኢህአዴግ የሚጠበቅ አይደለም” ብለዋል። ከኢህአዴግ የሚጠበቀውን ስነስርዓት ግን አልጠቆሙም። እሳቸው አይግለጹት እንጂ ኢህአዴግ የሚምልበት የምርጫ ስነምግባር ኮድ ፓርቲዎችን ማውገዝን አጥብቆ ይከለክላል።

አቶ አስራት ጣሴ እንዳሉት “ብዙዎች ፓርቲዎች አባላትና ጽ/ቤት የላቸውም። በህይወት የሌሉና አንድ ሰው የሚመራቸው ናቸው” በማለት አቶ ሬድዋን የሰጡትን ቃለ ምልልስ ተከትሎ እሳቸው የሚያስተባብሯቸው ፓርቲዎች በህብረት የተቃውሞ መግለጫ አውጥተዋል። አብዛኞቹ ፓርቲዎች ከ1984 ዓም ጀምሮ እስካሁን የዘለቁና በርካታ ደጋፊ ያላቸው መሆኑንን ያመለከቱት አቶ አስራት፣ “ቢሮ ስንከራይ በዶዘር እስከመጥረግ ይደርሳል። አከራዮችን በማስፈራራት ያከላክላል” ሲሉ ኢህአዴግን ይከሳሉ። በማያያዝም ኢህአዴግ የፓርቲዎች ደራጃ መዳቢ መሆኑንን አውግዘዋል። ድርጊቱ ፓርቲዎችን ሙሉ በሙሉ የማጥፋት እቅድ ለመኖሩ ማስረጃ እንደሆነ አመልክተዋል።

“የታፈኑት ተማሪዎች የት ደረሱ?”

(ፎቶ: facebook)

ከጎንደር ዩኒቨርስቲ የደህንነት ሃይሎች አፍነው የወሰዷቸው ሁለት ተማሪዎች ጉዳይ ተቃውሞ ማስነሳቱን ኢሳት ዘግቧል። ጥር 25 ቀን 2005 ዓ ም አንድ ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን ያስታወቀው ኢሳት “በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ከእለት ወደ እለት እየጨመረ በመሄዱ ትምህርታቸውን ተረጋግተው መማር አልቻሉም” ሲል ተማሪዎቹን በመጥቀስ አመልክቷል።

ኢሳት በደህንነት ሃይሎች ታፍነው ተወሰዱት ሰዒድና ዑመር የተባሉት ተማሪዎች በተያዘው የትምህርት ዘመን ትምህርታቸውን ያጠናቅቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል። በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ የሙስሊም ስርዓተ አምልኮና ጸሎት እንዳናካሂድ ተከልክለናል ያሉ ተማሪዎች በተመሳሳይ ተቃውሞ ማሰማታቸው የሚታወስ ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    February 4, 2013 01:16 pm at 1:16 pm

    Ethnic and religious unity is a great nightmare for woyane ethnic fascists. Unity regardless of religion and ethnicity is the solution to free Ethiopia and Ethiopians from the home grown fascists who are looting and terrorizing the Ethiopian people in the name of the people of Tigrai. Tigrian economic, military, political, educational/scientific dominance is not sustainable and the Ethiopians will not be “YEBEY TEMELKACH” and second class citizens in their own country.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule