• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከእሁድ እስከ እሁድ

February 4, 2013 09:20 am by Editor 1 Comment

ማክሰኞ ኢቲቪ ድግስ አለበት

“ክርስቲያኖችም ሙስሊሞችም ልባችሁን ጠብቁ”

“እስላማዊ መንግስት በኢትዮጵያ” የማስታወቂያው ፍንጣሪ ሃረግ ነው። በአብዛኛው የማህበራዊ ድረገጾች አስቀድመው የሚያስተላልፉት መልዕክት ደግሞ “ክርስቲያኑም ሙስሊሙም ልባችሁን ጠብቁ የሚል” ነው። ኢቲቪ ድግስ አለኝ ሲል ለማክሰኞ ቀጠሮ የያዘለት ዘጋቢ ፊልም አክራሪነት ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነ ቀደም ብሎ የተሰራጨው ማስታወቂያ ያስረዳል።

ከኢህአዴግ አፈጣጠርና የፕሮፓጋንዳ ልምዱ በመነሳት ለማክሰኞ በቀጠሮ የተዘጋጀውን ዘጋቢ ፊልም “አኬልዳማ ቁጥር ሁለት” በሚል ብዙዎች ሰይመውታል። አንዳንዶች ደግሞ “አዳዲስ ሆዳሞችን እንተዋወቃለን” ሲሉ ፊልሙ በደህንነት ሃይሎች የተቀነባበረ እንደሆነ መረጃ እንዳላቸው ይገልጻሉ። “የውሸት አባት ኢህአዴግና ወዲ ስምዖን የቆመሩት ቁማር” ሲሉ የሚገልጹትም ጥቂት አይደሉም።

“ጂሃዳዊ ሃረከት” የሚል ስያሜ የተሰጠው አዲሱ ዘጋቢ ፊልም ምንም ይሁን ምን ሙሉውን ለመመልከት ፍላጎት ያላቸው ትችቱ ባይቀድም ጥሩ ነው የሚል አቋምም እያራመዱ ነው “የአገራችን ጉዳይ የተወሳሰበ ነውና ልባችንን በመጠበቅ በጥበብ ነገሮችን ልንመረምር ይገባል” የሚል አስተያየት የለጠፉም አሉ። ብዙ እየተባለለት ያለው ይህ አዲስ ፊልም ከመውጣቱ በፊትና በኋላ በመላው አገሪቱ ያሉ ሙስሊሞች ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ለክርስቲያን ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው ፍቅር እንዲሰጡና ኢህአዴግ ሊፈጥረው ያሰበውን የጥርጣሬ አመለካከት መስበር እንደሚገባ ተዘግቧል።

ኦማር አል በሺር ኢሳያስን ሊጎበኙ ነው

(ፎቶ:xinhuanet.com)

ዓወት የተሰኘው ድረገጽ በ3/2/2013 ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂን ለመጎብኘት የሱዳኑ ኦማር አልበሽር አስመራ መግባታቸውን ዘግቧል። በሽር በመከላከያ ሚኒስትራቸውና በደህንነት ሃላፊያቸው ታጅበው ለጉብኝት ሲጓዙ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ እንደተለመደው በደህንነት ሃላፊያቸውና በመከላከያ ሚኒስትራቸው እንዳልታጀቡ ዓወት አስታውቃል። የስራ ጉብኝቱ ለአንድ ቀን እንደሆነም ተመልክቷል።

በኤርትራ አኩራፊ ወታደሮች የማስታወቂያ ሚኒስትርን በመቆጣጠር ህገመንግስታዊ ጥያቄ ካቀረቡ በኋላ በመሪ ደረጃ ፕሬዚዳንት ኢሳያስን ለመገናኘት ቀዳሚ የሆኑት ኦማር አል በሽር የመጀመሪያ መሆናቸውን የጠቆመው ዓወት ስለ ጉብኝቱ አበይት ጉዳይ አለው ነገር የለም። ሁለቱም ፕሬዚዳንቶች በተመሳሳይ ውስጥ ችግር ውስጥ እንዳሉ ያመላከተው ዜና የሁለቱን ጎረቤት አገር መሪዎች የጋዳፊና የሙባረክ እጣፈንታ እንደሚጠብቃቸው አመልክቷል። የአልበሽር ያልተጠበቀ ግንኙነት የሱዳን ወዳጅና ጠበቃ ለሆነችው ኢትዮጵያ ምን እንደምታ ሊኖረው እንደሚችል በዘገባው አልተጠቆመም።

የ“ዳቦ” አመጽ አክሱም ዩኒቨርስቲ ደረሰ

(ፎቶ: ከዩኒቨርሲቲው ድረገጽ)

ዩኒቨርስቲዎች በዳቦ አነሰ፣ ሩዝ ሰለቸን፣ ስጋ አልታኘክ አለን … ጥያቄ አድማ እየመቱ፣ ፖሊስም ወዲያው እየደረሰ ሲደቁሳቸው ጩኸታቸውን መስማት የተለመደ ነው። ይኼው የተለመደ የዳቦ አነሰ ጥያቄ “የተበላሸ የዳቦ ዱቄት” በሚል ተሻሽሎ አክሱም ዩኒቨርስቲ መድረሱን የዘገበው ሪፖርተር ነው። ጥያቄውን ያቀረቡት አስር ተማሪዎች ከዩኒቨርስቲው እንዲባረሩ መደረጉን ተከትሎ ያመጹት ተማሪዎች ተቃውሟቸውን ለመግለጽ ወደ ከተማ ሲወጡ አለመግባበት ተፈጥሮ ነበር።

ተማሪዎቹን አነጋግሮ የዘገበው ሪፖርትር፣ ሶስት ሺህ የሚሆኑ ተማሪዎች ወደ ከተማ ተሰልፈው ሲወጡ ፖሊስ ጥይት ተኩሶባቸዋል። የደረሰው ጉዳት ባይገለጽም ተማሪዎቹ ተቃውሟቸውን እየገለጹ ነው፤ በርካታ ተማሪዎች ግቢውን ለቀው ወጥተዋል። ከዳቦ ዱቄት መበላሸት ጥያቄ በስተቀር ከጀርባቸው ምንም አይነት የፖለቲካ አጀንዳ እንደሌለ ያስታወቁት ተማሪዎች ጥያቄው የመልካም አስተዳደር ስለሆነ ትምህርት ሚኒስቴር በጉዳዩ ጣልቃ በመግባት ለጥያቄያቸው መፍትሄ እንዲያፈላልግ ተማጽነዋል።

ኢትዮ–ጅቡቲ ምድር ባቡር ሲታደስ በሰዓት 20 ኪሜ “ይከንፋል”

(ፎቶ: ቢቢሲ)

የትራንስፖርት ሚኒስትሩ አቶ ድሪባ ኩማ የኢትዮ ጅቡቲን የምድር ባቡር ድርጅት የሞተ፣ የማይጠቅም፣ መፍረስ አለበት በማለት መግለጻቸውን የሪፖርተር የፓርላማ ጋዜጠኛ ጽፏል። “የማይጠቅም ነገር ዝም ብለን ማንከባለል አይጠቅምም” በማለት ድርጅቱ እጣ ፈንታው መፍረስ ብቻ እንደሆነ አመልክተዋል።

በሌላ በከል ለዚሁ መስመር እድሳት የተገኘ ገንዘብ ስራ ላይ ስለመዋሉ ተጠይቀው ሲመልሱ የባቡር መስመሩ ስራ እንዲጀምር በጅቡቲ በኩል ፍላጎት ስላለ ከድሬደዋ ጅቡቲ ያለው የባቡር መስመር ተጠግኖ ስራ እንዲጀምር ከስምምነት መደረሱን አስታውቀዋል። በስምምነቱ መሰረት አሮጌዎቹ ባቡሮች ተጠግነው ስራ ሲጀምሩ ስለሚኖረው ሁለኔታ ሲያስረዱ “ባቡሮቹ ተጠግነው ስራ ሲጀምሩ የሚጓዙት በሰዓት 20 ኪሎሜትር ነው” ብለዋል። አክሳሪና በሙስና የተወሳሰበ ድርጅት እንደሆነ ሚኒስትሩ የገለጹት ይህ ተቋም ለሰራተኞቹ የሚከፍለው ደሞዝ በማጣቱ ቀደም ባሉት ሚኒስትር ትዕዛዝ መሬት የማከራየት ስራ ይሰራ ነበር። በዓለማችን ፈጣን ተብለው ከአንድ እስከ አስር ደረጃ የተሰጣቸው ባቡሮች፤ አስረኛው በሰዓት 300ኪሜ አንደኛው ደግሞ 485 ኪሎሜትር ይጓዛል፡፡

የነጻ ሚዲያ ‘ፎቢያ’

ቀደም ሲል የፍትህ ጋዜጣን በተልካሻ ምክንያቶች የዘጉት ክፍሎች በተመሳሳይ አዲስ ታይምስ መጽሔትን ከህትመት ውጪ አድርገዋል። ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ይህንኑ አስመልክቶ በተለያዩ ድረገጾች ላይ ባሰራጨው ጽሁፍ ውሳኔው ከአምባገነንነት እሳቤና ከጭፍን ፍርሃት እንደሚመነጭ አመልክቷል።

አገርቤት አገዛዙ አፍንጫ ስር በመሆን ኢህአዴግን በሰላ ብዕር በመተቸት የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተመስገን አቶ መለስ ከአንድ ክፍለጦር በላይ የተለየ ሃሳብና ነጻ ሚዲያ እንደሚፈሩ ይናገራል። ወራሾቻቸውም ከእርሳቸው በባሰ አምባገነኖች እንደሆኑ ያመላከተው ተመስገን ለነጻ ሚዲያ ካላቸው ፍርሃቻ የተነሳ ጭፍን አምባገነን መሆናቸውን ገልጿል። ከዚህ አቋማቸው የተነሳ “አገሪቱን ወደ ድቅድቅ ጨለማ እየገፏት ነው” ብሏል፡፡

“የመለስ ራዕይ በአዲስ ራዕይ መጽሄት ተተገበረ” በሚል ርዕስ ተመስገን ባሰራጨው ጽሁፍ ለአዲስ ራዕይ መጽሄት መዘጋት የቀረቡት ሶስት ምክንያቶች ተራና ፍጹም ተልካሻ መሆናቸውን አንባቢ እንዲፈርድ በዝርዝር አስቀምጧል።

አስራት ጣሴ ሬድዋንን አወገዙ

(ፎቶ: የአስራት ጣሴ Facebook)

ለምርጫ ቦርድ ቅሬታቸውን አቅርበው መልስ ስላልተሰጣቸው ራሳቸውን ከምርጫ ያገለሉት 39 ፓርቲዎች ተወካይ አቶ አስራት ጣሴ የኢህአዴግ ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑትን አቶ ሬድዋን ሁሴንን አወገዙ። አቶ አስራት ለጀርመን ድምጽ ራዲዮ በሰጡት ማብራሪያ አቶ ሬድዋን ለመንግስት መገናኛዎች በሰጡት መግለጫ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ክብር ነክተዋል፤ ተሳድበዋል። ይህ ደግሞ “ከኢህአዴግ የሚጠበቅ አይደለም” ብለዋል። ከኢህአዴግ የሚጠበቀውን ስነስርዓት ግን አልጠቆሙም። እሳቸው አይግለጹት እንጂ ኢህአዴግ የሚምልበት የምርጫ ስነምግባር ኮድ ፓርቲዎችን ማውገዝን አጥብቆ ይከለክላል።

አቶ አስራት ጣሴ እንዳሉት “ብዙዎች ፓርቲዎች አባላትና ጽ/ቤት የላቸውም። በህይወት የሌሉና አንድ ሰው የሚመራቸው ናቸው” በማለት አቶ ሬድዋን የሰጡትን ቃለ ምልልስ ተከትሎ እሳቸው የሚያስተባብሯቸው ፓርቲዎች በህብረት የተቃውሞ መግለጫ አውጥተዋል። አብዛኞቹ ፓርቲዎች ከ1984 ዓም ጀምሮ እስካሁን የዘለቁና በርካታ ደጋፊ ያላቸው መሆኑንን ያመለከቱት አቶ አስራት፣ “ቢሮ ስንከራይ በዶዘር እስከመጥረግ ይደርሳል። አከራዮችን በማስፈራራት ያከላክላል” ሲሉ ኢህአዴግን ይከሳሉ። በማያያዝም ኢህአዴግ የፓርቲዎች ደራጃ መዳቢ መሆኑንን አውግዘዋል። ድርጊቱ ፓርቲዎችን ሙሉ በሙሉ የማጥፋት እቅድ ለመኖሩ ማስረጃ እንደሆነ አመልክተዋል።

“የታፈኑት ተማሪዎች የት ደረሱ?”

(ፎቶ: facebook)

ከጎንደር ዩኒቨርስቲ የደህንነት ሃይሎች አፍነው የወሰዷቸው ሁለት ተማሪዎች ጉዳይ ተቃውሞ ማስነሳቱን ኢሳት ዘግቧል። ጥር 25 ቀን 2005 ዓ ም አንድ ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጋቸውን ያስታወቀው ኢሳት “በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚወሰደው ርምጃ ከእለት ወደ እለት እየጨመረ በመሄዱ ትምህርታቸውን ተረጋግተው መማር አልቻሉም” ሲል ተማሪዎቹን በመጥቀስ አመልክቷል።

ኢሳት በደህንነት ሃይሎች ታፍነው ተወሰዱት ሰዒድና ዑመር የተባሉት ተማሪዎች በተያዘው የትምህርት ዘመን ትምህርታቸውን ያጠናቅቃሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል። በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በተመሳሳይ የሙስሊም ስርዓተ አምልኮና ጸሎት እንዳናካሂድ ተከልክለናል ያሉ ተማሪዎች በተመሳሳይ ተቃውሞ ማሰማታቸው የሚታወስ ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. koster says

    February 4, 2013 01:16 pm at 1:16 pm

    Ethnic and religious unity is a great nightmare for woyane ethnic fascists. Unity regardless of religion and ethnicity is the solution to free Ethiopia and Ethiopians from the home grown fascists who are looting and terrorizing the Ethiopian people in the name of the people of Tigrai. Tigrian economic, military, political, educational/scientific dominance is not sustainable and the Ethiopians will not be “YEBEY TEMELKACH” and second class citizens in their own country.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አየር ጨብጦ አሁን ያለውን መንግሥት ከሥልጣን ልቀቁ አይሆንም March 29, 2023 09:47 am
  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule