“የኢትዮጵያ ፓርላማ” እየተባለ በሚጠራው የኢህአዴግ ምክር ቤት በአቶ መለስ አነጋገር “እስከ እንጥሉ ስለገማው ኢህአዴግና የመንግሥት ሌቦች” ጉዳይ (በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ አጠራር “መልካም አስተዳደር” ጉዳይ) ከቀናት በፊት ሪፖርት ቀርቦ ነበር፡፡ አዲስ ፎርቹን ከፎቶው ጋር አያይዞ ያተመው ዜና እንደሚያስረዳው እና ፎቶው በገሃድ እንደሚያሳየው በሪፖርቱ መ/ቤታቸው በአስተዳደር ብልሹነት የመጨረሻ ደረጃ ላይ የሚገኙት የኢህአዴግ ሹመኞች አባተ ስጦታው (የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ) እና መድኀን ኪሮስ (የፍርድ ቤቶች ምክትል ፕሬዚዳንት) ከአፈጉባኤው አባዱላ ጋር በቃላት ሰይፍ “ሕዝባዊነታቸውን” ለማሳየት ሞክረዋል፡፡ ጋዜጣው ሹመኞቹን በጓደኞቻቸው ፊት “ሲያጉረመርሙ” ተሰሙ ቢልም፤ በርካታ ማኅበራዊ ሚዲያዎች “ዱላ ቀረሽ” ግብግብ ብለውታል፡፡ ጋዜጣው እንዳለው ከሆነ የአዲስ አበባ … [Read more...] about ምግባረ ብልሹዎቹ “የመልካም አስተዳደር” ሰባኪዎች
Middle Column
ሩሲያ ሙሰኞችን “በመሣሪያ” ልትመረምር ነው
በሩሲያ የሞስኮ ባለሥልጣናት ሙስናን ለመዋጋት በሚል ውሸታሞችን በመፈተኛ (lie-detector test) የመንግሥት ሠራተኞችን ልትመረምር ነው፡፡ ሰሞኑን የሩሲያው ኢንተርፋክስ እንደዘገበው በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት በሙሉ ውሸታሞችን በሚመረምረው መሣሪያ ሞሳኞች መሆን አለመሆናቸው እንደሚመረመር አስታውቋል፡፡ የፖሊግራፍ መፈተኛ የሚባለው በተለምዶ ውሸታሞችን መመርመሪያ ተብሎ የሚጠራው መፈተኛ በወንጀለኝነት የተጠረጠሩ ሰዎች የሚፈተኑበት ነው፡፡ ተፈታኝ ሰው ላይ የሚገጠመው መሣሪያ ግለሰቡ ጥያቄዎች በቀረቡለት ጊዜ መልስ ሲሰጥ የሚከሰተውን የልብ ምት፣ የደም ግፊት፣ አተነፋፈስ፣ የቆዳ መቆጣት፣ ወዘተ ይመረምራል፡፡ በዚህም መሠረት ግለሰቡ ለተጠየቀው የመለሰው እውነት ወይም ውሸት መሆኑን መሣሪያው መጨረሻ ላይ በሚሰጠው ሪፖርት ያረጋግጣል፡፡ መሣሪያው ፍጹም እውነተኛ አይደለም … [Read more...] about ሩሲያ ሙሰኞችን “በመሣሪያ” ልትመረምር ነው
በሃዋሳ በሶስት ጥይት ስለተገደለው
ባፈው ሃሙስ በሃዋሳ ከተማ ከተማ ልዩ ስሙ ታቦር ት/ቤት በሚባል አካባቢ ፖሊስ በሦስት ጥይት አንድ ሰው መግደሉ በዕለቱ ወዲያውኑ ከሥፍራው መረጃ ቢደርሰንም እስካሁን ተጨማሪ መረጃዎችን ስናሰባስብ ቆይተናል፡፡ የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) የላኩልን በምስል የተደገፈ መረጃ እንደሚያመለክተው ድርጊቱ የተከሰተው ግለሰቡ ለቤ/ክ ወደተከራየ ጊቢ ለመግባት በር ላይ በተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነ ዘጋቢያችን ጠቁመዋል፡፡ ቤቱ ለቤተክርስቲያንነት ቢከራይም የቤተሰቦቹ የሆነውን ቤት እሱ ሳያውቅ የተከራ በመሆኑ እንዲለቁለት ተከራዮቹን በተደጋጋሚ ሲጠይቅ እንደነበር መረጃ አቀባያችን ያስረዳሉ፡፡ እንደተለመደው በዕለቱም ይህንኑ ጥያቄውን ለማቅረብና ወደ ጊቢው ለመግባት በሚሞክርበት ጊዜ ተከራዮቹና ሌሎች ውስጥ የነበሩ ተባባሪዎቻቸው ፖሊስ መጥራታቸውን ዘጋቢያችን በላኩልን መረጃ … [Read more...] about በሃዋሳ በሶስት ጥይት ስለተገደለው
በኢትዮጵያ የጸጥታ ሁኔታ አላስተማመነም
በኢትዮጵያ ያለው የጸጥታና ደኅንነት ሁኔታ አስተማማኝ ሁኔታ ላይ አለመሆኑ ተነገረ፡፡ የዕርዳታ ድርጅት ሠራተኞች ወደ መስክ የሚያደርጉት የሥራ ጉብኝት ተከለከለ፤ የፕሮጀክት ሥራዎች ሊደናቀፉ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ያለው የጸጥታ ሁኔታ አስቸጋሪ ደረጃ ላይ በመድረሱ ኢህአዴግ የዕርዳታ ድርጅት ሠራተኞችን ወደተወሰኑ የአገሪቱ ክፍሎች እንዳይንቀሳቀሱ ማስጠንቀቂያ የሰጣቸው መሆኑን መረጃው የደረሳቸው ለጎልጉል አስታውቀዋል፡፡ በሰሜን ምዕራብ ኢትዮጵያ በተለይ የአማራ ክልልና በምዕራብ ደግሞ የጋምቤላ ክልል አካባቢ ያለው ውጥረት እጅግ እያየለ በመምጣቱ በቦታዎቹ ላይ የሚንቀሳቀሱ የዕርዳታ ድርጅት ሠራተኞች ሊደርስባቸው ስለሚችል ጉዳት ተጠያቂ እንደማይሆን ኢህአዴግ በሰጠው ማሳሰቢያ አስታውቋል፡፡ ማስጠንቀቂያ ከተሰጣቸው የዕርዳታ ድርጅቶች መካከል የካቶሊክ ዕርዳታ … [Read more...] about በኢትዮጵያ የጸጥታ ሁኔታ አላስተማመነም
አቅም የተፈጠረላቸው ፈላሾች – ህወሃቶች
ከ1997 ምርጫ በኋላ ወደ አዲስ አበባ ከፈለሱት የክልል ነዋሪዎች መካከል ከ87 በመቶ በላይ የትግራይ ተወላጆች እንደሆኑ አንድ የስታትስቲክስ ባለስልጣን ባለሙያ ጠቆሙ። ቁጥሩ የሚያሳየው ባግባቡ ከሃብትና ንብረት፣ ወይም ከመተዳደሪያ ጋር የተመዘገቡትን ብቻ እንደሚያካትት ባለሙያው አመልክተዋል። ከዘጠና በመቶ በላይ ከሌሎች ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚፈልሱት የእለት ጉርስ ፍለጋ ነው። በኢንቨስትመንት ስም በሚፈናቀሉ ዜጎች ኮቴ፣ በኮንደሚኒየም ቤቶች ዝውውር፣ መከላከያ፣ ደህንነትና ሁሉንም ዓይነት የፖሊስ ተቋማት ጨምሮ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ቅጥርና በመሳሰሉት ሰፊ ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ ተምመዋል፤ እየተመሙም ናቸው። እንደባለሙያው የሌሎች ክልል ተወላጆች በስፋት ወደ አዲስ አበባ ቢፈልሱም፣ የትግራይ ተወላጆችን ልዩ የሚያደርገው “አቅም እየተፈጠረላቸው … [Read more...] about አቅም የተፈጠረላቸው ፈላሾች – ህወሃቶች
መለስ ሳይጠየቁ ሾለኩ
* “የሟቾች ቁጥር እስከ መቶ ሊደርስ ይችላል” ነዋሪዎች * “የሞቱት 14 ሰዎች ናቸው” ኢህአዴግ ሰሞኑን በጋምቤላ በደረሰው የእርስበርስ ፍልሚያ እስከመቶ የሚጠጉ መሞታቸውን የክልሉ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ኢህአዴግ በበኩሉ የሞቱት 14 ብቻ ናቸው ይላል፡፡ ዘረኝነትንና ጠባብ ጎሰኝነትን ለኢትዮጵያ እንደ “ገጸ በረከት” ያመጡት መለስ በየቦታው የጫሩት እሣት ለፍርድ ሳያቀርባቸው ሾልከዋል፡፡ እሣቱ ግን አሁንም እየነደደ ነው፡፡ ጎልጉል ከአካባቢው ነዋሪዎችና ጉዳዩን በቅርብ ሲከታተሉ ባገኘው መረጃ መሠረት በግጭቱ የሞቱት እስከ መቶ እንደሚደርስ ይነገራል፡፡ ግጭቱ ከመነሻው በቀላሉ የተነሣ ቢሆንም ወዲያውኑ ወደከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ሥር የሰደደ ፖለቲካዊ ምክንያት እንዳለው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡ ይህንኑ ዜና ኢሳት ሲዘግብ የሟቾቹ ቁጥር ከመቶ እንደሚያልፍ ምንጮቹን ጥቅሶ … [Read more...] about መለስ ሳይጠየቁ ሾለኩ
“አፋኝ ህጎችና ፖሊሲዎች ለማሻሻል የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ የለም”
እ.ኤ.አ. በ2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ መንግስት በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት፣ ጋዜጠኞች፣ እና ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ አድራጊዎች ላይ እያደረገ ያለውን ጫና ቀጥሏል፤ አብዛኞቹ እንግልት፣ ዘፈቀዳዊ እስር እና በፖለቲካ የተቀናበረ ክስ ገጥመዋቿል፡፡ ገዢው ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ግንቦት ወር በተካሄደው ምርጫ 547 የፓርላማ መቀመጫዎችን አሸንፏል፤ ይሄውም የሆነበት አንዱ ምክንያት ጠንካራ ተጻራሪ ሃሳብ የላቸው ወይንም ተቃዋሚዎች በመታፈናቸው ነው፡፡ በሰኔ ወር የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያን ከመጎብኘታቸው አስቀድሞ የተወሰኑ ታዋቂ እስረኞች ከመፈታታቸው ባሻገር በኢትዮጵያን መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና መገናኛ ብዙሃኑን አስረው የያዙትን እጅግ አፋኝ ህጎች እና ፖሊሲዎች ለማሻሻል የተደረገ መሰረታዊ … [Read more...] about “አፋኝ ህጎችና ፖሊሲዎች ለማሻሻል የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ የለም”
የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ ሊያስገባ”?!
* ውሳኔው “ማዕቀብና የዕርዳታ ቅነሳ አያስከትልም” አና ጎሜዝ * የቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያዊ ልመና” አልሰራም የአውሮጳ ፓርላማ ሐሙስ ዕለት ባለ 19 ነጥብ ውሳኔ ህወሃት/ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ ላይ አስተላልፏል፡፡ ጉዳዩ ኢህአዴግ “ልክ ሊገባ ይሆን” የሚል አመለካከት ጭሯል፡፡ ረቂቁ ለውይይት እንዳይቀርብ የቻሉትን ያህል የጣሩት ቴድሮስ አድሃኖም “ዲፕሎማሲያቸው” አልሠራም፡፡ ውሳኔው “ማዕቀብና የዕርዳታ ቅነሳ አያስከትልም” በማለት አና ጎሜዝ ተናገሩ፡፡ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ውሳኔው “ውስጡ በብረት የተወጠረ የቦክስ ጓንቲ ነው” ብለውታል፡፡ የአውሮጳ ፓርላማ ሐሙስ ዕለት የኢትዮጵያን ጉዳይ በተመለከተ የቀረበለትን ረቂቅ ውይይትና ክርክር ካካሄደ በኋላ በከፍተኛ አብላጫ ድምጽ ያለ አንዳች ማሻሻያና ለውጥ እንዳለ አጽድቆታል፡፡ ጉዳዩን ከሥሩ ሲከታተሉና ለኅብረቱ … [Read more...] about የአውሮጳ ፓርላማ ኢህአዴግን “ልክ ሊያስገባ”?!
አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያም ኔታኒያሁ አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እየሆነ መጥቷል በማለት ተናገሩ፡፡ ጉዳዩ ያስቆጣቸው የሙስሊም መሪዎች ንግግሩ በሃይማኖታችን ላይ ማዕቀብ ለመጣል የተቃጣ ነው ብለውታል፡፡ ባለፈው አርብ በእስራኤል ሸንጎ የሊኩድ ፓርቲ አባላት በተገኙበት ኔታኒያሁ ባደረጉት ንግግር በእስራኤል የሚገኙ የአረብ ከተሞች ለአገሪቷ ሕግ መገዛት አለባቸው ብለዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ ለአገሪቷና ለማኅበረሰቡ ግዴታቸውን መወጣት አለባቸው በማለት አስታውቀዋል፡፡ “በአብዛኛዎቹ የአረብ ከተሞች ሕግ አይከበርም፤ ይህም አዛን እና ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ተጠቃሽ ናቸው” በማለት ቢኒያም ኔታኒያሁ የተናገሩ ሲሆን ከዚህ አኳያ ከበርካታ መስጊዶች የሚሰማው አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት እያስከተለ” ስለሆነ መንግሥታቸው ሕግ ሊያወጣ መወሰኑን አስታውቀዋል፡፡ አዛን … [Read more...] about አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ
የህወሓት ተስፋፊነት በኢትዮጵያ
በሰሜን በጌምድር (ጎንደር) ወልቃይት ፀገዴ፣ ፀለምት በአማራው ላይ ተስፋፊው ተሓህት/ህወሓት የፈጸመው የዘር ማጽዳት ወንጀል ይህ ታሪካዊ መረጃ በተቀነባበረ መልኩ የሚጀምረው ገና ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ (ተሓህት) ሲፈጠር ጀምሮ አስቀድሞ ለማጥፋት ያነጣጠረው በአማራው ህዝብ ላይ እንደሆነ በማስገንዘብ ነው። ከዚህ በመነሳት የተሓህት ፕሮግራም ገና ከ1967 ጀምሮ የረቀቀው በዲማ ኮንፈረንስ በየካቲት ወር 1968 ከ150 ያነሱ የተሓህት ታጋዮችን በማሰባሰብ ሕጋዊ ሆነ ተብሎ ቢነገርም፣ ሁሉም ታጋዮች ግን አልተቀበሉትም። በመጥፎ መልኩ የተዘጋጀውና አማራውን በማውገዝና ጠላት ብሎ የፈረጀ ነው። በኢትዮጵያና በህዝቧ፣ 1ኛ፣ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት አውዳሚ፣ 2ኛ፣ አንድነቱን ጠብቆ ለዘመናት አብሮ የኖረውን የኢትዮጵያ ህዝብ በጎሳ በዘር ለመበታተን ተደምሮና ተቀንሶ የተቀነባበረ አደገኛ … [Read more...] about የህወሓት ተስፋፊነት በኢትዮጵያ










