• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በሃዋሳ በሶስት ጥይት ስለተገደለው

February 10, 2016 06:01 am by Editor Leave a Comment

ባፈው ሃሙስ በሃዋሳ ከተማ ከተማ ልዩ ስሙ ታቦር ት/ቤት በሚባል አካባቢ ፖሊስ በሦስት ጥይት አንድ ሰው መግደሉ በዕለቱ ወዲያውኑ ከሥፍራው መረጃ ቢደርሰንም እስካሁን ተጨማሪ መረጃዎችን ስናሰባስብ ቆይተናል፡፡

የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ (ireporter) የላኩልን በምስል የተደገፈ መረጃ እንደሚያመለክተው ድርጊቱ የተከሰተው ግለሰቡ ለቤ/ክ ወደተከራየ ጊቢ ለመግባት በር ላይ በተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነ ዘጋቢያችን ጠቁመዋል፡፡

ቤቱ ለቤተክርስቲያንነት ቢከራይም የቤተሰቦቹ የሆነውን ቤት እሱ ሳያውቅ የተከራ በመሆኑ እንዲለቁለት ተከራዮቹን በተደጋጋሚ ሲጠይቅ እንደነበር መረጃ አቀባያችን ያስረዳሉ፡፡ እንደተለመደው በዕለቱም ይህንኑ ጥያቄውን ለማቅረብና ወደ ጊቢው ለመግባት በሚሞክርበት ጊዜ ተከራዮቹና ሌሎች ውስጥ የነበሩ ተባባሪዎቻቸው ፖሊስ መጥራታቸውን ዘጋቢያችን በላኩልን መረጃ ጠቁመዋል፡፡

awassaበእጁ ላይ ስለት ይዞ እንደነበር የተገለጸው ግለሰብ ስለቱ ግን ሆን ተብሎ የተቀነባበረበት ስለመሆኑ መረጃ እንዳለ ተነግሯል፡፡ የጎልጉል እማኝ ዘጋቢ እንደሚሉት ከሆነ “ስለቱ ለማስመሰል (ሆን ተብሎ) የተዘጋጀ እንጂ በእርግጥ ግለሰቡ ይዞት የነበረ ለመሆኑ ምንም ማረጋገጫ” የለም፡፡ “ከዚያም የመጣው ፖሊስ (ግለሰቡን) ይዞ ወደ ፖሊስ ጣቢያ መውሰድ ሲገባው አይኑ ላይ በጥይት ደበደበው።” ከመረጃው ለመረዳት እንደተቻለው ክላሽንኮቭ ያነገበው የኢህአዴግ ታጣቂ በሶስት ጥይት ግለሰቡን እንደገደለው የመረጃው አቀባይ ያስረዳሉ፡፡

ግለሰቡ የተገደለ ጊዜ ፎቶግራፍ ማንሳት የተቻለ በመሆኑ ድርጊቱ በፎቶ ማስረጃ የተደገፈ ሲሆን መሳሪያ አንጋቢው ግድያውን ከፈጸመ በኋላ ሲሸሽ “በወቅቱ ከኅብረተሰቡ ጋር ከፍተኛ ግጭት ተፈጥሮ በመጨረሻም በአስለቃሽ ጭስና በኃይል” አስከሬኑ መነሳቱን እማኝ ዘጋቢያችን ያስረዳሉ፡፡

“አስከሬኑም የት እንዳለ ከፖሊስ ውጭ የሚያውቅ የለም” ያሉት መረጃ አቀባያችን “ገዳዩን ፖሊስ ለማዳን ሁሉም ነገር ሚስጥር ተደርጓል” ሲሉ ገልጸዋል፡፡

ጎልጉል ከሚመለከታቸው አካላትም ሆነ ከሌላ ሦስተኛ ወገን ሁኔታውን በተመለከተ ለማጣራት ያደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡ (ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule