• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሩሲያ ሙሰኞችን “በመሣሪያ” ልትመረምር ነው

February 11, 2016 08:30 am by Editor Leave a Comment

በሩሲያ የሞስኮ ባለሥልጣናት ሙስናን ለመዋጋት በሚል ውሸታሞችን በመፈተኛ (lie-detector test) የመንግሥት ሠራተኞችን ልትመረምር ነው፡፡

ሰሞኑን የሩሲያው ኢንተርፋክስ እንደዘገበው በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት በሙሉ ውሸታሞችን በሚመረምረው መሣሪያ ሞሳኞች መሆን አለመሆናቸው እንደሚመረመር አስታውቋል፡፡

የፖሊግራፍ መፈተኛ የሚባለው በተለምዶ ውሸታሞችን መመርመሪያ ተብሎ የሚጠራው መፈተኛ በወንጀለኝነት የተጠረጠሩ ሰዎች የሚፈተኑበት ነው፡፡ ተፈታኝ ሰው ላይ የሚገጠመው መሣሪያ ግለሰቡ ጥያቄዎች በቀረቡለት ጊዜ መልስ ሲሰጥ የሚከሰተውን የልብ ምት፣ የደም ግፊት፣ አተነፋፈስ፣ የቆዳ መቆጣት፣ ወዘተ ይመረምራል፡፡ በዚህም መሠረት ግለሰቡ ለተጠየቀው የመለሰው እውነት ወይም ውሸት መሆኑን መሣሪያው መጨረሻ ላይ በሚሰጠው ሪፖርት ያረጋግጣል፡፡

መሣሪያው ፍጹም እውነተኛ አይደለም ብለው የሚከራከሩ ውጤቱን መቀበል ያቅተናል ቢሉም መሣሪያው በበርካታ አገራት ወንጀለኞችን በመመርመር አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡ እስካሁን እጅግ ጠቃሚነቱ ጥያቄ ላይ አልወደቀም፡፡

በቅርቡ በወጣው ዓለምአቀፋዊ የግልጽነት ዘገባ መሠረት ከ168 አገራት 119 ደረጃ ላይ የምትገኘው ሩሲያ ሙስናን ለመዋጋት “ግብረኃይል፤ ታስክፎርስ፤ …” ከማቋቋም ሙሰኞችን በሳይንሳዊ መንገድ መመርመር መፈለጓ ይበል የሚያሰኝ ነው በማለት አስተያየቶች ይሰጣሉ፡፡

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመመለስ ከሙስና ነጻ መሆናቸው ይፈተናል፡፡ ከዚያም የፈተናቸውን ውጤት እየተቀበሉ ወደ ቀጣዩ የጸረ ሙስና ምርመራ ይሸጋገራሉ፡፡ ጉዳዩን እየመሩ ባሉ የኢኮኖሚ፣ የሳይንስና የጸረ ሙስና ባለሙያዎች መሠረት ይህ አይነቱ ሙሰኛን የመመርመሪያ አሠራር ሙስናን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስተዋጽዖ አለው ይላሉ፡፡

ሙሰኞችን በእንዲህ ዓይነት መሣሪያ መመርመር ውጤት የለውም የሚሉ “የሰለጠኑ የመንግሥት ሌቦች” መሣሪያውን ማምታታት እንደሚችሉ ይናገራሉ፡፡ “የሰለጠኑ ሙሰኞች” ሙስናን እንደ አንድ ሙያ ስለሚያዩት ማንኛውንም ነገር ለማምለጥ የሚቻላቸውን ዝግጅት ያደርጋሉ፤ ስለዚህ የመሣሪያውንም ፈተና ማምለጥ ይችላሉ ይላሉ፡፡

ህወሃት/ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ የሙስና ጉዳይ ከላይ ጀምሮ እስከ መጨረሻው የበታች አመራር ድረስ እንደ መብት እና የአባልነት ግዴታ የሚተገበር እንደሆነ በራሱ በኢህአዴግ ሲነገር የቆየ ሃቅ ነው፡፡

ከሞቱ በኋላ ከሙስና ነጻ እንደነበሩ በአፍቃሪዎቻቸው እጅግ የሚነገርላቸው መለስ በአንድ ወቅት ራሳቸውን በሙስናው ክበብ ውስጥ በመጨመር “እስከ እንጥላችን ገምተናል” ማለታቸው ይታወሳል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule