• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሩሲያ ሙሰኞችን “በመሣሪያ” ልትመረምር ነው

February 11, 2016 08:30 am by Editor Leave a Comment

በሩሲያ የሞስኮ ባለሥልጣናት ሙስናን ለመዋጋት በሚል ውሸታሞችን በመፈተኛ (lie-detector test) የመንግሥት ሠራተኞችን ልትመረምር ነው፡፡

ሰሞኑን የሩሲያው ኢንተርፋክስ እንደዘገበው በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት በሙሉ ውሸታሞችን በሚመረምረው መሣሪያ ሞሳኞች መሆን አለመሆናቸው እንደሚመረመር አስታውቋል፡፡

የፖሊግራፍ መፈተኛ የሚባለው በተለምዶ ውሸታሞችን መመርመሪያ ተብሎ የሚጠራው መፈተኛ በወንጀለኝነት የተጠረጠሩ ሰዎች የሚፈተኑበት ነው፡፡ ተፈታኝ ሰው ላይ የሚገጠመው መሣሪያ ግለሰቡ ጥያቄዎች በቀረቡለት ጊዜ መልስ ሲሰጥ የሚከሰተውን የልብ ምት፣ የደም ግፊት፣ አተነፋፈስ፣ የቆዳ መቆጣት፣ ወዘተ ይመረምራል፡፡ በዚህም መሠረት ግለሰቡ ለተጠየቀው የመለሰው እውነት ወይም ውሸት መሆኑን መሣሪያው መጨረሻ ላይ በሚሰጠው ሪፖርት ያረጋግጣል፡፡

መሣሪያው ፍጹም እውነተኛ አይደለም ብለው የሚከራከሩ ውጤቱን መቀበል ያቅተናል ቢሉም መሣሪያው በበርካታ አገራት ወንጀለኞችን በመመርመር አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡ እስካሁን እጅግ ጠቃሚነቱ ጥያቄ ላይ አልወደቀም፡፡

በቅርቡ በወጣው ዓለምአቀፋዊ የግልጽነት ዘገባ መሠረት ከ168 አገራት 119 ደረጃ ላይ የምትገኘው ሩሲያ ሙስናን ለመዋጋት “ግብረኃይል፤ ታስክፎርስ፤ …” ከማቋቋም ሙሰኞችን በሳይንሳዊ መንገድ መመርመር መፈለጓ ይበል የሚያሰኝ ነው በማለት አስተያየቶች ይሰጣሉ፡፡

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመመለስ ከሙስና ነጻ መሆናቸው ይፈተናል፡፡ ከዚያም የፈተናቸውን ውጤት እየተቀበሉ ወደ ቀጣዩ የጸረ ሙስና ምርመራ ይሸጋገራሉ፡፡ ጉዳዩን እየመሩ ባሉ የኢኮኖሚ፣ የሳይንስና የጸረ ሙስና ባለሙያዎች መሠረት ይህ አይነቱ ሙሰኛን የመመርመሪያ አሠራር ሙስናን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስተዋጽዖ አለው ይላሉ፡፡

ሙሰኞችን በእንዲህ ዓይነት መሣሪያ መመርመር ውጤት የለውም የሚሉ “የሰለጠኑ የመንግሥት ሌቦች” መሣሪያውን ማምታታት እንደሚችሉ ይናገራሉ፡፡ “የሰለጠኑ ሙሰኞች” ሙስናን እንደ አንድ ሙያ ስለሚያዩት ማንኛውንም ነገር ለማምለጥ የሚቻላቸውን ዝግጅት ያደርጋሉ፤ ስለዚህ የመሣሪያውንም ፈተና ማምለጥ ይችላሉ ይላሉ፡፡

ህወሃት/ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ የሙስና ጉዳይ ከላይ ጀምሮ እስከ መጨረሻው የበታች አመራር ድረስ እንደ መብት እና የአባልነት ግዴታ የሚተገበር እንደሆነ በራሱ በኢህአዴግ ሲነገር የቆየ ሃቅ ነው፡፡

ከሞቱ በኋላ ከሙስና ነጻ እንደነበሩ በአፍቃሪዎቻቸው እጅግ የሚነገርላቸው መለስ በአንድ ወቅት ራሳቸውን በሙስናው ክበብ ውስጥ በመጨመር “እስከ እንጥላችን ገምተናል” ማለታቸው ይታወሳል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule