• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሩሲያ ሙሰኞችን “በመሣሪያ” ልትመረምር ነው

February 11, 2016 08:30 am by Editor Leave a Comment

በሩሲያ የሞስኮ ባለሥልጣናት ሙስናን ለመዋጋት በሚል ውሸታሞችን በመፈተኛ (lie-detector test) የመንግሥት ሠራተኞችን ልትመረምር ነው፡፡

ሰሞኑን የሩሲያው ኢንተርፋክስ እንደዘገበው በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት በሙሉ ውሸታሞችን በሚመረምረው መሣሪያ ሞሳኞች መሆን አለመሆናቸው እንደሚመረመር አስታውቋል፡፡

የፖሊግራፍ መፈተኛ የሚባለው በተለምዶ ውሸታሞችን መመርመሪያ ተብሎ የሚጠራው መፈተኛ በወንጀለኝነት የተጠረጠሩ ሰዎች የሚፈተኑበት ነው፡፡ ተፈታኝ ሰው ላይ የሚገጠመው መሣሪያ ግለሰቡ ጥያቄዎች በቀረቡለት ጊዜ መልስ ሲሰጥ የሚከሰተውን የልብ ምት፣ የደም ግፊት፣ አተነፋፈስ፣ የቆዳ መቆጣት፣ ወዘተ ይመረምራል፡፡ በዚህም መሠረት ግለሰቡ ለተጠየቀው የመለሰው እውነት ወይም ውሸት መሆኑን መሣሪያው መጨረሻ ላይ በሚሰጠው ሪፖርት ያረጋግጣል፡፡

መሣሪያው ፍጹም እውነተኛ አይደለም ብለው የሚከራከሩ ውጤቱን መቀበል ያቅተናል ቢሉም መሣሪያው በበርካታ አገራት ወንጀለኞችን በመመርመር አመርቂ ውጤቶችን ማስመዝገቡ እስካሁን እጅግ ጠቃሚነቱ ጥያቄ ላይ አልወደቀም፡፡

በቅርቡ በወጣው ዓለምአቀፋዊ የግልጽነት ዘገባ መሠረት ከ168 አገራት 119 ደረጃ ላይ የምትገኘው ሩሲያ ሙስናን ለመዋጋት “ግብረኃይል፤ ታስክፎርስ፤ …” ከማቋቋም ሙሰኞችን በሳይንሳዊ መንገድ መመርመር መፈለጓ ይበል የሚያሰኝ ነው በማለት አስተያየቶች ይሰጣሉ፡፡

በተያዘው ዕቅድ መሠረት በሞስኮ የሚገኙ የመንግሥት ሹማምንት የሚቀርብላቸውን ጥያቄ በመመለስ ከሙስና ነጻ መሆናቸው ይፈተናል፡፡ ከዚያም የፈተናቸውን ውጤት እየተቀበሉ ወደ ቀጣዩ የጸረ ሙስና ምርመራ ይሸጋገራሉ፡፡ ጉዳዩን እየመሩ ባሉ የኢኮኖሚ፣ የሳይንስና የጸረ ሙስና ባለሙያዎች መሠረት ይህ አይነቱ ሙሰኛን የመመርመሪያ አሠራር ሙስናን ለመከላከልና ለመቆጣጠር አስተዋጽዖ አለው ይላሉ፡፡

ሙሰኞችን በእንዲህ ዓይነት መሣሪያ መመርመር ውጤት የለውም የሚሉ “የሰለጠኑ የመንግሥት ሌቦች” መሣሪያውን ማምታታት እንደሚችሉ ይናገራሉ፡፡ “የሰለጠኑ ሙሰኞች” ሙስናን እንደ አንድ ሙያ ስለሚያዩት ማንኛውንም ነገር ለማምለጥ የሚቻላቸውን ዝግጅት ያደርጋሉ፤ ስለዚህ የመሣሪያውንም ፈተና ማምለጥ ይችላሉ ይላሉ፡፡

ህወሃት/ኢህአዴግ በሚገዛት ኢትዮጵያ የሙስና ጉዳይ ከላይ ጀምሮ እስከ መጨረሻው የበታች አመራር ድረስ እንደ መብት እና የአባልነት ግዴታ የሚተገበር እንደሆነ በራሱ በኢህአዴግ ሲነገር የቆየ ሃቅ ነው፡፡

ከሞቱ በኋላ ከሙስና ነጻ እንደነበሩ በአፍቃሪዎቻቸው እጅግ የሚነገርላቸው መለስ በአንድ ወቅት ራሳቸውን በሙስናው ክበብ ውስጥ በመጨመር “እስከ እንጥላችን ገምተናል” ማለታቸው ይታወሳል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule