• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ማስፈጸም አይችልም

July 13, 2013 01:49 am by Editor 1 Comment

“ዕድገት”፣ “ትራንስፎርሜሽን”፣ “ህዳሴ”፣ “የመለስ ውርስ (ሌጋሲ)”፣ … በሚመሯት ኢትዮጵያ ሙስና እየከፋ መሄዱ ታወቀ፤ ከመቶ ሰዎች ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት ጉቦ የሚሰጡ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡

ሰሞኑን ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት (Transparency International) ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በርካታ የአፍሪካ አገራት በሙስና “መበስበሳቸውን” ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ አገራት መካከል እንደምትገኝ ዘግቧል፡፡

ከዚህ በፊት በያዝነው ዓመት ጥር ወር የሙስና አደጋ የተጋረጠባቸው አገራትን ዝርዝርና የአደጋውን መጠን በሰባት ደረጃ በመከፋፈል ይኸው ድርጅት ባወጣበት ጊዜ ኢትዮጵያን በከፍተኛ የሙስና አደጋ ውስጥ ከሚገኙ አገራት ዝርዝር ውስጥ አስገብቷት ነበር፡፡ በዚህ ዘገባ መሠረት በሙስና የተዘፈቁትን አገራት በመከፋፈል ባስቀመጠው ባለዘጠኝ መዘርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛው ውስጥ አካትቷታል፡፡

bribe 1ሰሞኑን የወጣው ዘገባ ይህንን እንዲል ያስቻለው አንዱ መረጃ “ጉቦ ሰጥተዋል ወይ (ያውቃል)?” በማለት ለአንድ ሺህ ሰዎች ያቀረበውን ናሙና መሠረት በማድረግ ነው፡፡ በጥያቄው መሠረት በኢትዮጵያ 44በመቶው “አዎን” በማለት መመለሳቸውን ዘግቧል፡፡

ጥናቱ የ3በመቶ የስህተት ገደብ ያደረገ ቢሆንም፤ የነጻ ሚዲያ፣ በነጻነት የመናገር፣ ያለፍርሃትና ዛቻ ሃሳብን የመግለጽ፣ ወዘተ መብት በተረገጠባት ኢትዮጵያ የዘገባው ቁጥር ከዚህ በላይ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፡፡ በቅርቡ ራሱ ኢህአዴግ በሙስና ላይ ዘመቻ ጀምሬያለሁ በማለት የወሰደው እርምጃ ጎልጉል “ሙስናን በስንጥር” በማለት የዘገበው ቢሆንም ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት ካወጣው መረጃ ጋር ሲነጻጸር “የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቀውንና የሚኖረውን ብታውቁና ብትኖሩ ኖሮ” የሚያስብል ነው፡፡

ከህዝቧ ግማሽ በላይ ሥራአጥ በሆነባት (የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ነው)፣ 86በመቶ ምንጥ ያለ ድሃና 80በመቶ በግብርና የተሰማራ ችግረኛ ሕዝብ በሚኖርባት አገር፤ ዘገባው ያወጣው አኃዝ ጉዳይ ከሚያስፈጽመው ሕዝብ መካከል ግማሽ ያህሉ ጉቦ መስጠት ግዴታው መሆኑ፤ ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ለማስፈጸም ጨርሶ አቅቶታል ወይም ጉዳዩን ከማስፈጸም ተቆጥቧል የሚያስብል ነው፡፡

ለ5ዓመታት በአዲስአበባ ኃላፊነት ከቆዩ በኋላ ሰሞኑን ወደ ጠ/ሚ/ር ጽ/ቤት “ማቀዝቀዣ” የገቡት ኩማ ደመቅሳ በስንብታቸው ወቅት በኢህአዴግኛ “ኪራይ ሰብሳቢነት” አሁንም የከተማዋ አሳሳቢ ችግር እንደሆነ አምርረው ተናግረዋል፡፡ ይህ ሁኔታና አሁን የወጣው ዘገባ “ውርሳቸውን እናስጠበቃለን” የሚባሉት ሟቹ መለስ፤ በረሃ በነጻአውጪነት ከዚያም በመንግሥትነት ራሳቸው ስለመሩት ድርጅት የተናገሩትን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት “ከእንጥላችን ገምተናል”!

(የዘገባውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Liberalism says

    July 26, 2014 03:49 pm at 3:49 pm

    Liberalism

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule