• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ማስፈጸም አይችልም

July 13, 2013 01:49 am by Editor 1 Comment

“ዕድገት”፣ “ትራንስፎርሜሽን”፣ “ህዳሴ”፣ “የመለስ ውርስ (ሌጋሲ)”፣ … በሚመሯት ኢትዮጵያ ሙስና እየከፋ መሄዱ ታወቀ፤ ከመቶ ሰዎች ውስጥ ከ40 በላይ የሚሆኑት ጉቦ የሚሰጡ መሆናቸውን አስታወቁ፡፡

ሰሞኑን ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት (Transparency International) ያወጣው መረጃ እንደሚያመለክተው በርካታ የአፍሪካ አገራት በሙስና “መበስበሳቸውን” ከእነዚህም መካከል ኢትዮጵያ ከቀዳሚዎቹ አገራት መካከል እንደምትገኝ ዘግቧል፡፡

ከዚህ በፊት በያዝነው ዓመት ጥር ወር የሙስና አደጋ የተጋረጠባቸው አገራትን ዝርዝርና የአደጋውን መጠን በሰባት ደረጃ በመከፋፈል ይኸው ድርጅት ባወጣበት ጊዜ ኢትዮጵያን በከፍተኛ የሙስና አደጋ ውስጥ ከሚገኙ አገራት ዝርዝር ውስጥ አስገብቷት ነበር፡፡ በዚህ ዘገባ መሠረት በሙስና የተዘፈቁትን አገራት በመከፋፈል ባስቀመጠው ባለዘጠኝ መዘርዝር ውስጥ ኢትዮጵያ ከመጨረሻ ሁለተኛው ውስጥ አካትቷታል፡፡

bribe 1ሰሞኑን የወጣው ዘገባ ይህንን እንዲል ያስቻለው አንዱ መረጃ “ጉቦ ሰጥተዋል ወይ (ያውቃል)?” በማለት ለአንድ ሺህ ሰዎች ያቀረበውን ናሙና መሠረት በማድረግ ነው፡፡ በጥያቄው መሠረት በኢትዮጵያ 44በመቶው “አዎን” በማለት መመለሳቸውን ዘግቧል፡፡

ጥናቱ የ3በመቶ የስህተት ገደብ ያደረገ ቢሆንም፤ የነጻ ሚዲያ፣ በነጻነት የመናገር፣ ያለፍርሃትና ዛቻ ሃሳብን የመግለጽ፣ ወዘተ መብት በተረገጠባት ኢትዮጵያ የዘገባው ቁጥር ከዚህ በላይ እንደሚሆን መገመት አያዳግትም፡፡ በቅርቡ ራሱ ኢህአዴግ በሙስና ላይ ዘመቻ ጀምሬያለሁ በማለት የወሰደው እርምጃ ጎልጉል “ሙስናን በስንጥር” በማለት የዘገበው ቢሆንም ዓለምአቀፉ የግልጽነት ድርጅት ካወጣው መረጃ ጋር ሲነጻጸር “የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚያውቀውንና የሚኖረውን ብታውቁና ብትኖሩ ኖሮ” የሚያስብል ነው፡፡

ከህዝቧ ግማሽ በላይ ሥራአጥ በሆነባት (የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ነው)፣ 86በመቶ ምንጥ ያለ ድሃና 80በመቶ በግብርና የተሰማራ ችግረኛ ሕዝብ በሚኖርባት አገር፤ ዘገባው ያወጣው አኃዝ ጉዳይ ከሚያስፈጽመው ሕዝብ መካከል ግማሽ ያህሉ ጉቦ መስጠት ግዴታው መሆኑ፤ ድሃው ሕዝብ ጉዳዩን ለማስፈጸም ጨርሶ አቅቶታል ወይም ጉዳዩን ከማስፈጸም ተቆጥቧል የሚያስብል ነው፡፡

ለ5ዓመታት በአዲስአበባ ኃላፊነት ከቆዩ በኋላ ሰሞኑን ወደ ጠ/ሚ/ር ጽ/ቤት “ማቀዝቀዣ” የገቡት ኩማ ደመቅሳ በስንብታቸው ወቅት በኢህአዴግኛ “ኪራይ ሰብሳቢነት” አሁንም የከተማዋ አሳሳቢ ችግር እንደሆነ አምርረው ተናግረዋል፡፡ ይህ ሁኔታና አሁን የወጣው ዘገባ “ውርሳቸውን እናስጠበቃለን” የሚባሉት ሟቹ መለስ፤ በረሃ በነጻአውጪነት ከዚያም በመንግሥትነት ራሳቸው ስለመሩት ድርጅት የተናገሩትን የሚያረጋግጥ ነው፡፡ እንዲህ ነበር ያሉት “ከእንጥላችን ገምተናል”!

(የዘገባውን ሙሉ መረጃ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ)

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Liberalism says

    July 26, 2014 03:49 pm at 3:49 pm

    Liberalism

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule