• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እያስከተለ ነው – ኔታኒያሁ

January 21, 2016 08:35 am by Editor 1 Comment

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያም ኔታኒያሁ አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት” እየሆነ መጥቷል በማለት ተናገሩ፡፡ ጉዳዩ ያስቆጣቸው የሙስሊም መሪዎች ንግግሩ በሃይማኖታችን ላይ ማዕቀብ ለመጣል የተቃጣ ነው ብለውታል፡፡

ባለፈው አርብ በእስራኤል ሸንጎ የሊኩድ ፓርቲ አባላት በተገኙበት ኔታኒያሁ ባደረጉት ንግግር በእስራኤል የሚገኙ የአረብ ከተሞች ለአገሪቷ ሕግ መገዛት አለባቸው ብለዋል፡፡ ይህንንም በማድረግ ለአገሪቷና ለማኅበረሰቡ ግዴታቸውን መወጣት አለባቸው በማለት አስታውቀዋል፡፡

“በአብዛኛዎቹ የአረብ ከተሞች ሕግ አይከበርም፤ ይህም አዛን እና ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት ተጠቃሽ ናቸው” በማለት ቢኒያም ኔታኒያሁ የተናገሩ ሲሆን ከዚህ አኳያ ከበርካታ መስጊዶች የሚሰማው አዛን “መታገስ የማይቻል ጩኸት እያስከተለ” ስለሆነ መንግሥታቸው ሕግ ሊያወጣ መወሰኑን አስታውቀዋል፡፡

አዛን (አድሃን) ለጸሎትና ለስግደት ሙስሊሙ እንዲሰበሰብ የሚደረግ ጥሪ ነው፡፡ ድምጸ መረዋ በሆኑ የሚሰማው ይህ ጥሪ በበርካታ ቦታዎች በድምጽ ማጉያ የሚደረግ ሲሆን በአንዳንድ ቦታዎች ያለ ድምጽ ማጉያም የሚከናወን ነው፡፡

“ይህንን (ጩኸት) መቀበል በጭራሽ አይቻልም” ያሉት ኔታኒያሁ በአረብም ሆነ በአውሮጳ አገራት እንዲህ ያለ ጩኸት በድምጽ ማጉያ እንዲሰማና ሰዎች እንዲረበሹ የሚፈቅድ ሃይማኖታዊ ፅሁፍ የለም ብለዋል፡፡ ስለዚህ ገደብ ሊደረግበት ይገባል፤ እንዲያውም ጩኸትን የሚከለክል ሕግ አለን እርሱን ተግባራዊ እናድርገው ብለዋል፡፡

በእስራኤል በሚገኙ የአረብ ከተሞች የሚታየው ከአንድ በላይ ሚስት የማግባት ሁኔታን በተመለከተም “ይህንን ክስተት በተመለከተ የሴቶች (መብት ተሟጋች) ድርጅቶች እንደ ሙታን ዝምታን” መምረጣቸውን የወቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ የተወሳሰበ መሆኑን ከመናገር ግን አልተቆጠቡም፡፡ ሲያጠቃልሉም “ሕግ የምንከተል አገር መሆን አለብን ወይም የለብንም” በማለት ቃላት በተግባር መተርጎም እንዳለባቸው ተናግረዋል፡፡

በየሩሳሌምና በፍልስጤም ግዛቶች ጠቅላይ ሙፍቲ የሆኑት ሼክ መሐመድ ሁሴን ጉዳዩን በመስጊዶቻችን ላይ የተሰጠ “ማስጠንቀቂያ”፤ በሃይማኖቱ ላይ ማዕቀብ ለመጣል ያነጣጠረ ነው ብለውታል፡፡ በእስራኤል ሸንጎ አረባውያኑ እንደራሴዎች ጉዳዩ የዘረኝነት መንፈስ የተጠናወተው በማለት የጠቀሱት ሲሆን ኔታኒያሁ የአረብ ጥላቻ በመቀስቀስ ርካሽ የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘት በመደጋገም የሚሞክሩት አደገኛ አካሄድ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

“ኔታኒያሁ እንደ አገር አስተዳዳሪ ጉዳዮችን መመልከት ይገባቸዋል እንጂ እንደ አምባገነን ወታደራዊ መሪ መሆን የለባቸውም” በማለት ሌላኛው እንደራሴ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ወቅሰዋል፡፡al-aqsa-mosque-southern-wall

የእስራኤል ሸንጎ አባላትና አይሁዳዊ ሰፋሪዎች በወታደሮችና በፖሊሶች በመታገዝ ባለፈው መስከረም ወር የአል-አቅሳን መስጊድ ከወረሩበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ከ2400 በላይ ፍልስጤማውያን ታስረዋል፤ 30 ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ጨምሮ 158 ተገድለዋል፤ 10ሺህ የሚጠጉ ደግሞ ቆስለዋል፡፡ የየሩሳሌም ኢንቲፋዳ የሚባለውን ተቃውሞ ቀስቅሷል የሚባልለት ይህ ድርጊት ለእስራኤል በየሩሳሌም አካባቢ በሚገኙ የአረብ ሰፈሮች ላይ የከረሩ ሕግጋትን እንደትተገብር ነጻነት እንደሰጣት በሰፊው ይነገራል፡፡ (ለዜናው ጥንቅር የተለያዩ የዜና ምንጮችን ተጠቅመናል፤ የመግቢያ ፎቶ ሲያሳት ዴይሊ)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Hunde says

    January 21, 2016 06:52 pm at 6:52 pm

    I fully agree with the PM. There is no reason to disturb the silent life of non-Muslims in the area. I travel to Finfinnee (Addis Ababa ) and one of the reasons I hate to be there is the uncontrollable and truly disturbing shouting from the. Mosques, specially in early morning.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule