• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Archives for January 2019

ለኢትዮጵያ ትንሣኤ ወያኔን ማገድ ብቸኛው አማራጭ ነው!

January 26, 2019 11:46 am by Editor Leave a Comment

ለኢትዮጵያ ትንሣኤ ወያኔን ማገድ ብቸኛው አማራጭ ነው!

አሁን የተጀመረውን አገራዊ ለውጥ በመቀልበስ እንደዘበት ከእጁ አፈትልኮ የወጣውን ስልጣን መልሶ ለመጨበጥ መቀሌ የመሸገው ምንደኛው ኃይል የማይፈነቅለው ድንጋይ የማይሸርበው ሤራ የለም። ይህ ጥቅመኛ እና ሴረኛ ቡድን ገና ከፍጥረቱ ጀምሮ በኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ላይ ቂም እና ጥላቻን ጸንሶ ወደ ስልጣን በመምጣቱ የአገሪቱን መሰረታዊ ጥቅሞች ለባዕዳንና ለታሪካዊ ጠላቶቻችን ጭምር አሳልፎ ሲሰጥ ቆይቷል። ነጻ ያልወጡት የትህነግ ነጻ አውጪ ነን ባዮች የጥንታዊት ግሪክ ፈላስፎች እነ ሶቅራጥስ፣ ኤዞፕ፣ አሪስቶትል፣ ዲዮዶሩስ እና ሌሎችም በታሪካዊ የፍልስፍና ድርሳኖቻቸው ደጋግመው እያወደሱ የጠቀሷትን ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት በማዋረድ እና በማንኳሰስ የአማራ ነፍጠኞች ተረት እንጂ ኢትዮጵያ ከመቶ ዓመት የዘለለ ታሪክ የላትም የሚል ጥላቻን ያዘለ ትርክት ፈጥረው ጀግኖች ለዘመናት ደማቸውን … [Read more...] about ለኢትዮጵያ ትንሣኤ ወያኔን ማገድ ብቸኛው አማራጭ ነው!

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ

January 25, 2019 01:13 pm by Editor 2 Comments

አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ባለፈው ሳምንት ያፀደቀው “የስደተኞች አዋጅ” ከሚመለከታቸው ባለጉዳዮች ከፍተኛ ተቃውሞ እየደረሰበት ነው። በተለይ የስደተኛ ቁጥር በብዛት በሚገኝባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ የኅልውና ጥያቄ እንዳለባቸው ይናገራሉ። የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችም ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። በፀደቀው አዋጅ መሠረት ማንኛውም ዕውቅና የተሰጠው ስደተኛ ወይም ጥገኝነት ጠያቂ፤ በመረጠው የአገሪቷ አካባቢ የመዘዋወር፣ የመኖሪያ ቤት የመመሥረት፣ መንጃ ፈቃድ የማውጣት፣ የመታወቂያና የውጪ ቪዛ (የጉዞ ሰነድ) የማግኘት፣ የባንክ ሂሳብ የመክፈትና ገንዘብ የማንቀሳቀስ፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ዜጎች ጋር ተዋህደው የመኖርና የኢትዮጵያን ዜግነት የመጠየቅ መብት ተሰጥቷቸዋል። አዋጁ ወደ ሥራ የመጣው Road map for the implementation of the Federal Democratic … [Read more...] about አወዛጋቢውና ባለጉዳዮች ያልመከሩበት የስደተኞች ሕግ ጉዳይ

Filed Under: Law, News Tagged With: ARRA, crrf, Full Width Top, Middle Column, refugees ethiopia

“በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ

January 25, 2019 12:54 pm by Editor 3 Comments

“በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ

በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር የዋሉት በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሣ “በማረፊያ ቤት ቆይታችን ሰብዓዊ መብታችንን እና ክብራችንን የሚነካ ድርጊት ተፈጽሞብናል” በማለት ለፍርድቤት ቅሬታ አቀረቡ። ጉዳያቸው በአዲስ አበባ እንዲታይ ለፍርድቤቱ ያቀረቡት ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ የአስራ አራት ቀን ቀጠሮ ሰጥቷል። በረከት ስምዖንና ታደሰ ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ ጥር 17 ቀን 2011 ዓ.ም. በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል። ተጠርጣሪዎቹ ካለባቸው የጤና ችግር አንጻር በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ እንደሚመገቡ ገልጸው፤ ይሁንና በማረፊያ ቤቱ ምግብ በአግባቡ እና በሰዓቱ እንደማይቀርብላቸው ተናግረዋል። ለአብነትም ትናንት ምሳ በ10፡00 እንደቀረበላቸው ለችሎቱ አስረድተዋል። የኢኮኖሚ ችግር እንዳለባቸው እና ጡረታ በአግባቡ … [Read more...] about “በማረፊያ ቤት ሰብዓዊ መብታች ተጥሷል”፤ በጥንቃቄ የተዘጋጀ ምግብ በአግባቡና በሰዓቱ አይቀርብልንም – በረከትና ታደሰ

Filed Under: News Tagged With: bereket, court, Full Width Top, kassa, Middle Column

ይድረስ ለሰብአ ትግራይ

January 24, 2019 08:16 pm by Editor Leave a Comment

ይድረስ ለሰብአ ትግራይ

1) በመጀመሪያ ራሴን ላስተዋውቅ፤ የተወለድሁት አዲስ አበባ ስድስት ኪሎ አካባቢ ነው፤ ዘመኑም 1922 ዓ. ም. ነው፤ የአገዛዝ የመንግሥት ለውጥ የተደረገበት ዘመን ነበር፤ አባቴ አቶ ወልደ ማርያም እንዳለ (ከአንኮበር፣ ሸዋ)፣ እናቴ ወይዘሮ ይመኙሻል ዘውዴ (ከየጁ፣ ወሎ) ናቸው፤ ሚስቴ የነበረችው በአባትዋ ሸዋ (መርሐቤቴ) በእናትዋ ትግራይ (አድዋ፣ እንትጮ) ነች። በሥራዬ አብዛኛው ዕድሜዬ ያለፈው በአስተማሪነት ነው፤ መጀመሪያ በእቴጌ መነን ትምህርት ቤት፣ በኋላ በዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ፣ ከዚያ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሳስተምር ነበር፤ በአጼ ኃይለ ሥላሴ አገዛዝ በፓርላማ ተመርጬ ለአንድ ዓመት ያህል በመርማሪ ኮሚስዮን ሠርቻለሁ፤ ጡረታ ከወጣሁ በኋላ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤን አቋቁሜ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ስለ ሰብአዊ መብቶች ለማስተማር ሞክሬአለሁ፤ የመጨረሻ ሥራ የምለው … [Read more...] about ይድረስ ለሰብአ ትግራይ

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Final Ethiopia Trip Report: Speaking engagements at various institutions

January 24, 2019 10:21 am by Editor Leave a Comment

Final Ethiopia Trip Report: Speaking engagements at various institutions

Because of the unstable political atmosphere in Ethiopia, I have never gone back to Ethiopia since I came to the US in 2005. In April this year, however, the ruling party elected a new Prime Minister- Abiy Ahmed, who has been spearheading a reform that includes inviting political opponents, some of whom were sentenced to death in absentia. Since then, thousands of Ethiopians in the Diaspora returned home after many years of exile. After 13 long years stay in the US, me too, I decided to visit … [Read more...] about Final Ethiopia Trip Report: Speaking engagements at various institutions

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

January 23, 2019 12:15 pm by Editor 2 Comments

“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

በኦሮሞ የባሕል ማዕከል ኦዴፓ ከኦነግ ጋር ስምምነት ባደረገበት ወቅት ዕርቀ ሰላሙን ከመሩት የአገር ሽማግሌዎች መካከል ኦቦ ኃይሌ ገብሬ እጅግ ጥልቅ ንግግር አድርገው ነበር። ይህ በአፋን ኦሮሞ እያለቀሱ የተናገሩት ልብ የሚነካ ንግግር ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ የሚል ነበር፤ “ዕርቀ-ሰላም በሚሆንበት ጊዜ እንዲሳካ ከብት ማረድ ካስፈለገ ገዝተን እናርዳለን፤ አይ ከብት አይደለም ሰው ይታረድልን የምትሉ ከሆነ ይኸው የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ”። ይህንን ዓይነት መስዋዕትነት የተከፈለበት ዕርቀ-ሰላም አንቀበልም የሚሉ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኃይሎች ለራሳቸው ሲሉ ከዚህ በኋላ ጥንቃቄ ቢያደርጉ መልካም ነው በማለት ስምምነቱን የተካፈሉ ይናገራሉ። የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ በኋላ ማንኛውንም ዓይነት ከፋፋይና ደም አፋሳሽ ተግባር መሸከም የሚችልበት ትከሻ የለውም። በኦሮሞ ስም … [Read more...] about “የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

Filed Under: News Tagged With: haile gebre, Left Column

በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) በቁጥጥር ሥር ውለዋል

January 23, 2019 10:32 am by Editor 2 Comments

በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) በቁጥጥር ሥር ውለዋል

በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ከጥረት ኮርፖሬት ጋር በተያያዘ በሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው ነው በቁጥጥር ሥር የዋሉት። ዜናው በአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት የተዘገበ ሲሆን ከመኖሪያ ቤታቸው እንደተያዙ መረጃው ጨምሮ ገልጾዋል። ታደሰ ካሳ ጥረት ኮርፖሬትን በዋና ስራ አስፈፃሚነት ለበርካታ ዓመታት የመራ ሲሆን በረከት ስምኦን ደግሞ ከበርካታ የመንግሥት የሥራ ኃላፊነት ቦታዎች ባሻገር የጥረት ኮርፖሬት የቦርድ ኃላፊ ሆኖ ሲመዘብር የነበረ ለመሆኑ ብዙዎች ይናገራሉ። ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ … [Read more...] about በረከት ስምኦንና ታደሰ ካሳ (ጥንቅሹ) በቁጥጥር ሥር ውለዋል

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

ኦነግ በአማርኛ መግለጫ ባወጣ ጥቂት ቀን “ትጥቃችንን ለኦሮሞ ሕዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” አለ

January 23, 2019 12:30 am by Editor Leave a Comment

ኦነግ በአማርኛ መግለጫ ባወጣ ጥቂት ቀን “ትጥቃችንን ለኦሮሞ ሕዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” አለ

ኢትዮጵያን “አቢሲኒያ ኢምፓዬር” በማለት ሲጠራ የኖረውና ራሱን የኦሮሞ ነጻአውጪ ግምባር ብሎ የሰየመው “ኦነግ” አቢሲኒያ ከሚላት ኢትዮጵያ ለመገንጠል ብቻ ሳይሆን አማርኛንም እንደ ጨቋኝ ቋንቋ በመቁጠር በዚያ ከመጠቀም ተቆጥቦ መኖሩ የሚታወቅ ነው። ለአብነት ያህል በቅርቡ ወዳገር ቤት የገቡት ገላሳ ዲልቦ እነ መለስ በጠሩት የሽግግር መንግሥት ምሥረታ ወቅት በእንግሊዝኛ ሲናገሩ ሌንጮ ለታ ከጎናቸው በመሆን በኦሮሚኛ ያስተረጉሙ ነበር። አሁን ደግሞ እኚሁ ገላሳ ዲልቦ በየሚዲያው በአማርና ቃለምልልስ ብቻ ሳይሆን ቅኔም ሲዘርፉ ሰምተናል። በግሩም የአማርኛ ብሒል የታጀበውና “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር በሚል ርዕስ የወጣው የኦነግ መግለጫ ያተኮረው መንግሥት ምዕራብ ወለጋን በአየር ስለመደብደቡ የጠ/ሚ/ሩ ፕሬስ ክፍል (እንግሊዝኛ) ቢልለኔ ስዩም ማስተባበላቸውን ተከትሎ … [Read more...] about ኦነግ በአማርኛ መግለጫ ባወጣ ጥቂት ቀን “ትጥቃችንን ለኦሮሞ ሕዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” አለ

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ

January 22, 2019 03:58 am by Editor 1 Comment

አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ

ለጥቁር ገበያ ለሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ እና ግምቱ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ልዩ ልዩ ቁሳቁስ ከኅብረተሰብ በደረሰ ጥቆማ መያዙን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ “ትዕግስት ብሩክ ቶታል ማደያ” ውስጥ ጥር 12 ቀን 2011 ዓ/ም በ44 ጀሪካን 995 ሊትር ቤንዚን ከማደያው በመቅዳት ላይ እንዳሉ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል። የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የተቀዳውን ከአስራአንድ ሺ ብር በላይ ዋጋ የሚያወጣ ቤንዚን እና ሌላ ሊቀዳበት የነበረ አርባ አራት ባዶ ጀሪካን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3 አ/አ 29642 ከሆነ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በቁጥጥር ሥር አውሏል። ድርጊቱን ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 5 ግለሰቦችም ፖሊስ በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን አስታውቋል። የክፍለ ከተማው ፖሊስ መምሪያ የወንጀልና ትራፊክ አደጋ … [Read more...] about አንድ ሚሊዮን ብር የሚገመት ለጥቁር ገበያ ሽያጭ ሊቀርብ የነበረ ነዳጅ ተያዘ

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው

January 22, 2019 02:30 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው

በድርብ አኻዝ በከፍተኛ ፍጥነት ዕድገት ላይ ነች እየተባለ ሲደሰኮርባት በነበረችው አገር በቅርቡ ይፋ የተደረገ ጥናት እንደጠቆመው ሰላሣ ስድስት ሚሊየን የሚጠጉ ህፃናቶቿ ዘርፈብዙ በሆነ መልኩ ድሃ መሆናቸው ተነገረ። ይህም ማለት ህፃናቱ ለመኖር የሚያስፈልጓቸው መሠረታዊ አገልግሎቶችን እንኳን ማግኘት ብርቅ ሆኖባቸዋል ነው ጥናቱ ያለው። በኢትዮጵያ ከ18 አመት በታች ከሆኑት ከ41 ሚሊየን ውስጥ 36 ሚሊዮኑ በድህነት ውስጥ እንዳሉ የስታቲስቲክ ኤጀንሲ እና ዩኒሴፍ ጥናት አስረድቷል። ጥናቱ በተለያዩ ዘጠኝ ክፍሎች ተለይቷል። ድህነቱ በዕድገት፣ በምግብ፣ በጤና፣ በውሃ፣ በንፅህና እና በመጠለያ ሲሆን ሌሎቹ የድህነት መለኪያ መስፈርቶች ደግሞ ትምህርት፣ ከጤና ጋር በተያያዘ በቂ ዕውቀት፣ መረጃና ተሳትፎን የሚጨምር ነው ተብሏል። በጥናቱ እንደተገለጸው 88 በመቶ የሚሆኑት ዕድሜያቸው … [Read more...] about በኢትዮጵያ 36 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በድህነት ደረጃ ላይ ናቸው

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

  • Page 1
  • Page 2
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule