If one dares to assign responsibility to Ethiopia’s fate of turmoil and tragedy over the past 50 years,the lion’s share would unequivocally fall on the shoulder of the educated class.The uncertainty that has become the trademark of Ethiopia starting with the Student Movement in the late 60s, followed by theentanglement of the youth – the cream of the crop - in meaningless bloodshed in the 70s, the share of the educated is undeniably significant. As a result, the impact of that period will keep … [Read more...] about The Curse of Education: An Ethiopian Paradox
Archives for January 2019
ሕዝባችን ከፍተኛ መስዕዋትነት የከፈለለትን ተጋድሎ አማራጭ ካሳጡን ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ጭምር መጠበቅ ይኖርበታል!
ባለፉት ሶስት ዓመታት የተካሄደው ይፋዊ ሕዝባዊ ተጋድሎ የፋሽስት ወያኔን የትግራይ የአፓርታይድ አገዛዝ ከስር መሰረቱ እንዳናጋው ሲታገል የኖረው ሕዝብ ብቻ ሳይሆን ከአዲስ አበባ ተባረው መቀሌ የመሸጉትና እንደ ተቃዋሚ የሚያደርጋቸው ፋሽስት ወያኔዎች ራሳቸው ምስክሮች ናቸው። ሕዝባዊ ተጋድሎውን ተከትሎ ሕዝባዊ አላማ በማንገብ፤ ግብ አስቀምጠውና ወዳስቀመጡት ሕዝባዊ ግብም የሚያደርሰን ያሉትን የትግል ስልት በመንደፍ እንደሚንቀሳቀሱ ሲናገሩ የምናውቃቸው በርካታ ድርጅቶች ነበሩ። ዛሬ ላይ ግን እነዚህን ድርጅቶች ሲያስተጋቡ የነበሩትን አላማ ይዘው ከሕዝቡ መካከል ማግኘት የማንችልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) “ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ … [Read more...] about ሕዝባችን ከፍተኛ መስዕዋትነት የከፈለለትን ተጋድሎ አማራጭ ካሳጡን ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ጭምር መጠበቅ ይኖርበታል!
በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው
በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን ነዳጅ እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባባስ በሚያደርጉ ነዳጅ አቅራቢዎች እና አከፋፋዮች ላይ አስፈላጊውን ክትትል እያደረገ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአገር አቀፍ ደረጃ በቂ ነዳጅ እያለ ነገር ግን በአዲስ አበባ ከተማ የቤንዚን እጥረት እንዲከሰት እና እንዲባበስ በመደረጉ ያጋጠመውን ችግር ለመፍታት አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽንን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ያካተተ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ኢንጂነር ታከለ ኡማ የሚመራ ግብረ ኃይል ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ ይታወቃል። በከተማችን ነዳጅ ለማከፋፈል 120 ገደማ የሚሆኑ የነዳጅ ማደያዎች በሕግ አግባብ ፈቃድ መውሰዳቸው እየታወቀ 106ቱ ብቻ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል። ጥር 8 ቀን 2011 ዓ/ም በስራ ላይ ከሚገኙ 106 … [Read more...] about በአዲስ አበባ ለተከሰተው የነዳጅ አሻጥር መፍትሔ ሊበጅለት ነው
የአዴፓና የአማራ ክልል መንግስት ሆደ ሰፊነት ልክ ቢኖረው
"ኧረ ጎራው፣ ኧረ ደኑ፣ ኧረ ናማ! እባብ አረጀ አሉ፣ አባብ መለኮሰ - ጠመጠመ ሻሽ፣ የዛለ ሰው ቢያገኝ በመርዝ ሊያበለሽ።" ሲል ያቅራራቀው የጎጃም አርሶ አደር ወዶ አይደለም ግፉ ቢበዛበት ነው። እባብ በህይወት እያለ ጉንዳንን ይበላል። እባብ ሲሞት ጉንዳኖች ይበሉታል። ጊዜ በማንኛውም ሰዓት ይለወጣል በህይወት ዘመንህ የማንንም ዋጋ አታሳንስ ምናልባት አንተ ሀይለኛ ትሆን ይሆናል ጊዜ ግን ካንተ የበለጠ ጉልበተኛ ነው አስብ አንድ ዛፍ መቶ ሺ ክብሪቶችን ሲሰራ አንድ ክብሪት ግን መቶ ሺህ ዛፎችን ታቃጥላለች። አንድ መጥፎ ስራም ብዙ መልካም ነገሮችን ታጠፋለች። ዋናው ነገር ለአንድ አገር በአስተሳሰብ መልካም የሆነ ድርጅት፣ መንግስትና ሕዝብ ያስፈልጋል። መልካም አስተሳሰብ ብቻውን አገር አይገነባም፣ ታሪክም አይሰራም። ድርጅት በሉት መንግስት የሕዝብ ማንነትን ካረከሱ በሕሊናቸው … [Read more...] about የአዴፓና የአማራ ክልል መንግስት ሆደ ሰፊነት ልክ ቢኖረው
ከዐምሐራ ክልል ውጭ ያለው የሰፊው ዐምሐራ ሕዝብ
በታሪክ አጋጣሚ ከክልሉ ውጭ በሰፋትና በብዛት በኢትዮጵያ ተበትኖ የሚኖረው የዐምሐራ ሕዝብ ነው። ዛሬ የወለጋ ዐምሐራ፣ የኢሉአባቦር ዐምሐራ፣ የጋሞጎፋ ዐምሐራ፣ የከፋ ዐምሐራ፣ የሲዳሞ ዐምሐራ፣ የሸዋ ዐምሐራ፣ የአርሲ ዐምሐራ፣ የባሌ ዐምሐራ፣ የሐረር ዐምሐራ፣ የሶማሌ ዐምሐራ፣ የጋምቤላ ዐምሐራ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ዐምሐራ፣ የአዲስ አበባ ዐምሐራና የድሬዳዋ ዐምሐራ ሕዝብ ቁጥሩ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ በግልጽ ይታወቃል። ከዐምሐራ ክልል ውጭ የሚኖረው ዐምሐራ ሕዝብ ለዘመናት በሚኖርበት ቦታ ሁሉ ከአከባቢው ሕዝብ ጋራ ሰምና ፈትል ሆኖ ተጋብቶ፣ ተዋልዶ፣ በሥጋና በደም ተዋህዶ ኖሮአል። በቋንቋ፣ በባህል፣ በወግ፣ በሥርዓት እና በሀይማኖት ተስማምቶ ከሺህ ዓመታት በላይ በቤተሰብነት ክፉውንም ደጉንም በማሳለፉ በቀላሉ የማይፈርስ የወል ማንነት ገንብቷል። (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ … [Read more...] about ከዐምሐራ ክልል ውጭ ያለው የሰፊው ዐምሐራ ሕዝብ