• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

January 23, 2019 12:15 pm by Editor 2 Comments

በኦሮሞ የባሕል ማዕከል ኦዴፓ ከኦነግ ጋር ስምምነት ባደረገበት ወቅት ዕርቀ ሰላሙን ከመሩት የአገር ሽማግሌዎች መካከል ኦቦ ኃይሌ ገብሬ እጅግ ጥልቅ ንግግር አድርገው ነበር። ይህ በአፋን ኦሮሞ እያለቀሱ የተናገሩት ልብ የሚነካ ንግግር ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ የሚል ነበር፤

“ዕርቀ-ሰላም በሚሆንበት ጊዜ እንዲሳካ ከብት ማረድ ካስፈለገ ገዝተን እናርዳለን፤ አይ ከብት አይደለም ሰው ይታረድልን የምትሉ ከሆነ ይኸው የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ”።

ይህንን ዓይነት መስዋዕትነት የተከፈለበት ዕርቀ-ሰላም አንቀበልም የሚሉ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኃይሎች ለራሳቸው ሲሉ ከዚህ በኋላ ጥንቃቄ ቢያደርጉ መልካም ነው በማለት ስምምነቱን የተካፈሉ ይናገራሉ። የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ በኋላ ማንኛውንም ዓይነት ከፋፋይና ደም አፋሳሽ ተግባር መሸከም የሚችልበት ትከሻ የለውም። በኦሮሞ ስም ሊያበረክቱት የሚፈልጉት ካለ ሕዝባቸውን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል ብቻ ነው፤ እንደ ኦቦ ኃይሌ ገብሬ ዓይነቱን ጨዋና አገር ወዳድ እጅግ ያበርክትልን በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: haile gebre, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    January 23, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    የሕዝባችንን ደም ሲያፈስና ሲያስፈስስ የነበረው ሰይጣንና ሰይጣን የጠየቃቸውን ደም በመፍረስ አብት ያካበቱ በጠንቋይ እየተመሩ መንግስን ስልጣን ቆንጥጠው የቆዩት የሰው ደም በአደባባይ በጥይት እያፈሰሱ በሰውር ደግሞ ደም እየገበሩ ኸሰይጣናዊ አይልና ጉልበት ሲቀበሉ ቆይተዋል። ፨መንፈሳዊ ነገር ያልነቃው ሕዝቤ ቤተሰቡን ልጆቹን መሬቱን ደም እያፈሰሱ ሲገዙና ሲያርዱት የነበረው ለሰይጣን ብለው ነበር። ሰይጣን የሰውና የፈጣሪም ኘላት ሰለሆነ በአጋንንት መንፈስ እየተነዱ አገርና ሕዝቡን የሚገድሉትን በሰይጣን የተሞሉ ሰዎችን ለይታችሁ ለማወቅ መቻል ያስፈልገናል ። የሰው ደም ለማፍሰስ የሚቸኩል ሁሉ በሰይጣን ቁጥጥር ስር ያለ የሰይጣን አገልጋይ እንጂ ሰው ብለን የምንጠራው ከተግባሩ ተቆጥቦ ለሰው ሁሉ መራራት ሲጀመር ብቻ ነው። በ27 የቀለብነው ሰይጣን ከእባብ ወደ ዘንዶ ከዘንዶ ወደ ተምዘግዛጊ ሻርክ ተለዋውጠዋል። አሁን ግን ታላቁ እባብ ሌዋታን የሰው ልጅ ሁሉ ጠላት ጥላቻ፣ ዘረኝነት ፣ ድንቁርና፣ ቅናት፣ ፍርሃት፣ የበታችነት አመለካከት ፣ ነቀትና ትዕቢት ወደ ጉድጓድ ገብተዋል የኢትዮጵያ ሕዝብ በጉድጓዱ ላይ አፈር በመመለስ ለመጨረሻ ጊዜ መቀበር አለበት። ሰላም ለኢትዮጵያውያን እንዱሁም ሰላም ለሰው ልጅ በመሉ። ፈጣሪ አንድ ነው የሰው ዘርም አንድ ነው። ግርማ

    Reply
  2. Tesfa says

    January 23, 2019 11:26 pm at 11:26 pm

    በአለፉት 40 ዓመታት ገደማ የኦሮሞ ህዝብ መብት ተሟጋች ኦነግ እንደነበር ህዝባችን ጠንቅቆ ያውቃል። ኦነግ የራሱን ባንዲራ ያውለበለበ ኦሮሚያ የምትባል ሃገር እንመሰርታለን በማለት ይበልጥ ዘመኑን በአስመራ የመሸጎ የኖረ ድርጅት ነው። በአንጻሩ በእየዓለማቱ በልዪ ልዮ ምክንያት ከሃገር የወጡ ቆራጥና ለኦሮሞ ህዝብ የሚታገሉ ለመኖራቸው እኔ የዓይን ምሥክር ነኝ። ከእነዚህም ቀዳሚውና በመገናኛ አውታሮች ጎልቶ የሚታየው ጆዋር መሃመድ ነው። ጀዋር ባለፉትና በቅርብ ጊዜ ከጀርባችን ላይ ከወረደው የወያኔ አገዛዝ ጭምር የኦሮሞ ህዝብ ግፍ ሲፈጸምበት ያየ እና ለዚህ ህዝብ ነጻነትና እፎይታ በትጋት የታገለ ወገናችን ነው። ያው የእኛው ሃገር ፓለቲካ እድሜ ለወያኔ ሁሉንም በየወገንህ በማለቱ ሰው በፊት ካሳለፍናቸው መንግሥታት ይልቅ በወያኔው አሻጥር ክልልና ቋንቋን ተገን ማድረግ ሲገልና ሲጋደል እንደኖረና አሁንም እንዳለ የየእለቱ የዜና ዘገባዎች ያስረዳሉ።
    የሃገሬ ሰው የሚለው አንድ አባባል አለ ” በየወገንህ ቢሉት የመቶ ዓመት ቆዳ ገቢያ ወጥቶ ቆመ” ይላሉ። ወገንተኝነት አፈረሰን እንጂ አልሰራንም። ዛሬ ለኦሮሞ ህዝብ እንቆረቆራለን የሚሉ ወደ 17 የሚጠጉ ድርጅቶች አሉ። ከእነዚህ ሁሉ የሚከፋው ኦነግ ነው። በወለጋ ህዝባችንን ሲገድል ሲዘርፍ መሪው አቶ ከተማ ተቀምጦ ነጻ አውጣሃለሁ የሚለውን ህዝብ ወታደሮቹ ሲገድሉ የሚያምታታ የፓለቲካ መግለጫ ለዜና አውታሮች በመስጠት የወያኔ የሰውርና የገሃድ ተላላኪ መሆኑ አስነዋሪ ነው። ትጥቅ አልፈታም ማለት ምን ማለት ነው? ኦነግ ትጥቅ ታጥቆ የነበረው የኦሮሞ ህብን ሰቆቃ ለማስታገስ ከሆነ ዛሬ ዝርፊያውና ግድያው ለምንድን ነው? ኦነግ አንድ ማወቅ ያለበት ትልቅ ነጥብ አለ? የኦሮሞን ህዝብ የዛሬ 40 ዓመት በተተለመ አላማ ዛሬ መምራት አይቻልም። ጊዜው ተለውጦአል። ኦነግና ወታደሮቹም ጠበንጃቸውን አስቀምጠው ጠኔና ችጋር ያልተለየውን ህዝባችንን ከድህነት ለማውጣት አፈሙዝ የለሽ ፓለቲካን መከተል አለባቸው። ከዚህ አንጻር ጀዋር መሃመድ በየጊዜው የሚሰጣቸው ወቅታዊና ሃገራዊ እይታዎቹን እጋራለሁ። በርታ አይዞህ እንላለን። ሌሎችም ለምሳሌ ያህል እንደ ዶ/ር አለሙ፤ ዶ/ር መራራና ሌሎች ለኢትዮጵያ አንድነትና ለኦሮሞ ህዝብ ሰላም በፊትም ዛሬም በመታገል ላይ ይገኛሉ። የኦነግ አመራሮች/ደጋፊዎች ያለፈን የጥይት ፓለቲካ በመተው ለህዝባችንና ለሃገራችን በአንድነት እንስራ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule