• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

January 23, 2019 12:15 pm by Editor 2 Comments

በኦሮሞ የባሕል ማዕከል ኦዴፓ ከኦነግ ጋር ስምምነት ባደረገበት ወቅት ዕርቀ ሰላሙን ከመሩት የአገር ሽማግሌዎች መካከል ኦቦ ኃይሌ ገብሬ እጅግ ጥልቅ ንግግር አድርገው ነበር። ይህ በአፋን ኦሮሞ እያለቀሱ የተናገሩት ልብ የሚነካ ንግግር ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ የሚል ነበር፤

“ዕርቀ-ሰላም በሚሆንበት ጊዜ እንዲሳካ ከብት ማረድ ካስፈለገ ገዝተን እናርዳለን፤ አይ ከብት አይደለም ሰው ይታረድልን የምትሉ ከሆነ ይኸው የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ”።

ይህንን ዓይነት መስዋዕትነት የተከፈለበት ዕርቀ-ሰላም አንቀበልም የሚሉ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኃይሎች ለራሳቸው ሲሉ ከዚህ በኋላ ጥንቃቄ ቢያደርጉ መልካም ነው በማለት ስምምነቱን የተካፈሉ ይናገራሉ። የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ በኋላ ማንኛውንም ዓይነት ከፋፋይና ደም አፋሳሽ ተግባር መሸከም የሚችልበት ትከሻ የለውም። በኦሮሞ ስም ሊያበረክቱት የሚፈልጉት ካለ ሕዝባቸውን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል ብቻ ነው፤ እንደ ኦቦ ኃይሌ ገብሬ ዓይነቱን ጨዋና አገር ወዳድ እጅግ ያበርክትልን በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: haile gebre, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    January 23, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    የሕዝባችንን ደም ሲያፈስና ሲያስፈስስ የነበረው ሰይጣንና ሰይጣን የጠየቃቸውን ደም በመፍረስ አብት ያካበቱ በጠንቋይ እየተመሩ መንግስን ስልጣን ቆንጥጠው የቆዩት የሰው ደም በአደባባይ በጥይት እያፈሰሱ በሰውር ደግሞ ደም እየገበሩ ኸሰይጣናዊ አይልና ጉልበት ሲቀበሉ ቆይተዋል። ፨መንፈሳዊ ነገር ያልነቃው ሕዝቤ ቤተሰቡን ልጆቹን መሬቱን ደም እያፈሰሱ ሲገዙና ሲያርዱት የነበረው ለሰይጣን ብለው ነበር። ሰይጣን የሰውና የፈጣሪም ኘላት ሰለሆነ በአጋንንት መንፈስ እየተነዱ አገርና ሕዝቡን የሚገድሉትን በሰይጣን የተሞሉ ሰዎችን ለይታችሁ ለማወቅ መቻል ያስፈልገናል ። የሰው ደም ለማፍሰስ የሚቸኩል ሁሉ በሰይጣን ቁጥጥር ስር ያለ የሰይጣን አገልጋይ እንጂ ሰው ብለን የምንጠራው ከተግባሩ ተቆጥቦ ለሰው ሁሉ መራራት ሲጀመር ብቻ ነው። በ27 የቀለብነው ሰይጣን ከእባብ ወደ ዘንዶ ከዘንዶ ወደ ተምዘግዛጊ ሻርክ ተለዋውጠዋል። አሁን ግን ታላቁ እባብ ሌዋታን የሰው ልጅ ሁሉ ጠላት ጥላቻ፣ ዘረኝነት ፣ ድንቁርና፣ ቅናት፣ ፍርሃት፣ የበታችነት አመለካከት ፣ ነቀትና ትዕቢት ወደ ጉድጓድ ገብተዋል የኢትዮጵያ ሕዝብ በጉድጓዱ ላይ አፈር በመመለስ ለመጨረሻ ጊዜ መቀበር አለበት። ሰላም ለኢትዮጵያውያን እንዱሁም ሰላም ለሰው ልጅ በመሉ። ፈጣሪ አንድ ነው የሰው ዘርም አንድ ነው። ግርማ

    Reply
  2. Tesfa says

    January 23, 2019 11:26 pm at 11:26 pm

    በአለፉት 40 ዓመታት ገደማ የኦሮሞ ህዝብ መብት ተሟጋች ኦነግ እንደነበር ህዝባችን ጠንቅቆ ያውቃል። ኦነግ የራሱን ባንዲራ ያውለበለበ ኦሮሚያ የምትባል ሃገር እንመሰርታለን በማለት ይበልጥ ዘመኑን በአስመራ የመሸጎ የኖረ ድርጅት ነው። በአንጻሩ በእየዓለማቱ በልዪ ልዮ ምክንያት ከሃገር የወጡ ቆራጥና ለኦሮሞ ህዝብ የሚታገሉ ለመኖራቸው እኔ የዓይን ምሥክር ነኝ። ከእነዚህም ቀዳሚውና በመገናኛ አውታሮች ጎልቶ የሚታየው ጆዋር መሃመድ ነው። ጀዋር ባለፉትና በቅርብ ጊዜ ከጀርባችን ላይ ከወረደው የወያኔ አገዛዝ ጭምር የኦሮሞ ህዝብ ግፍ ሲፈጸምበት ያየ እና ለዚህ ህዝብ ነጻነትና እፎይታ በትጋት የታገለ ወገናችን ነው። ያው የእኛው ሃገር ፓለቲካ እድሜ ለወያኔ ሁሉንም በየወገንህ በማለቱ ሰው በፊት ካሳለፍናቸው መንግሥታት ይልቅ በወያኔው አሻጥር ክልልና ቋንቋን ተገን ማድረግ ሲገልና ሲጋደል እንደኖረና አሁንም እንዳለ የየእለቱ የዜና ዘገባዎች ያስረዳሉ።
    የሃገሬ ሰው የሚለው አንድ አባባል አለ ” በየወገንህ ቢሉት የመቶ ዓመት ቆዳ ገቢያ ወጥቶ ቆመ” ይላሉ። ወገንተኝነት አፈረሰን እንጂ አልሰራንም። ዛሬ ለኦሮሞ ህዝብ እንቆረቆራለን የሚሉ ወደ 17 የሚጠጉ ድርጅቶች አሉ። ከእነዚህ ሁሉ የሚከፋው ኦነግ ነው። በወለጋ ህዝባችንን ሲገድል ሲዘርፍ መሪው አቶ ከተማ ተቀምጦ ነጻ አውጣሃለሁ የሚለውን ህዝብ ወታደሮቹ ሲገድሉ የሚያምታታ የፓለቲካ መግለጫ ለዜና አውታሮች በመስጠት የወያኔ የሰውርና የገሃድ ተላላኪ መሆኑ አስነዋሪ ነው። ትጥቅ አልፈታም ማለት ምን ማለት ነው? ኦነግ ትጥቅ ታጥቆ የነበረው የኦሮሞ ህብን ሰቆቃ ለማስታገስ ከሆነ ዛሬ ዝርፊያውና ግድያው ለምንድን ነው? ኦነግ አንድ ማወቅ ያለበት ትልቅ ነጥብ አለ? የኦሮሞን ህዝብ የዛሬ 40 ዓመት በተተለመ አላማ ዛሬ መምራት አይቻልም። ጊዜው ተለውጦአል። ኦነግና ወታደሮቹም ጠበንጃቸውን አስቀምጠው ጠኔና ችጋር ያልተለየውን ህዝባችንን ከድህነት ለማውጣት አፈሙዝ የለሽ ፓለቲካን መከተል አለባቸው። ከዚህ አንጻር ጀዋር መሃመድ በየጊዜው የሚሰጣቸው ወቅታዊና ሃገራዊ እይታዎቹን እጋራለሁ። በርታ አይዞህ እንላለን። ሌሎችም ለምሳሌ ያህል እንደ ዶ/ር አለሙ፤ ዶ/ር መራራና ሌሎች ለኢትዮጵያ አንድነትና ለኦሮሞ ህዝብ ሰላም በፊትም ዛሬም በመታገል ላይ ይገኛሉ። የኦነግ አመራሮች/ደጋፊዎች ያለፈን የጥይት ፓለቲካ በመተው ለህዝባችንና ለሃገራችን በአንድነት እንስራ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule