• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

January 23, 2019 12:15 pm by Editor 2 Comments

በኦሮሞ የባሕል ማዕከል ኦዴፓ ከኦነግ ጋር ስምምነት ባደረገበት ወቅት ዕርቀ ሰላሙን ከመሩት የአገር ሽማግሌዎች መካከል ኦቦ ኃይሌ ገብሬ እጅግ ጥልቅ ንግግር አድርገው ነበር። ይህ በአፋን ኦሮሞ እያለቀሱ የተናገሩት ልብ የሚነካ ንግግር ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ የሚል ነበር፤

“ዕርቀ-ሰላም በሚሆንበት ጊዜ እንዲሳካ ከብት ማረድ ካስፈለገ ገዝተን እናርዳለን፤ አይ ከብት አይደለም ሰው ይታረድልን የምትሉ ከሆነ ይኸው የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ”።

ይህንን ዓይነት መስዋዕትነት የተከፈለበት ዕርቀ-ሰላም አንቀበልም የሚሉ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኃይሎች ለራሳቸው ሲሉ ከዚህ በኋላ ጥንቃቄ ቢያደርጉ መልካም ነው በማለት ስምምነቱን የተካፈሉ ይናገራሉ። የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ በኋላ ማንኛውንም ዓይነት ከፋፋይና ደም አፋሳሽ ተግባር መሸከም የሚችልበት ትከሻ የለውም። በኦሮሞ ስም ሊያበረክቱት የሚፈልጉት ካለ ሕዝባቸውን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል ብቻ ነው፤ እንደ ኦቦ ኃይሌ ገብሬ ዓይነቱን ጨዋና አገር ወዳድ እጅግ ያበርክትልን በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: haile gebre, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    January 23, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    የሕዝባችንን ደም ሲያፈስና ሲያስፈስስ የነበረው ሰይጣንና ሰይጣን የጠየቃቸውን ደም በመፍረስ አብት ያካበቱ በጠንቋይ እየተመሩ መንግስን ስልጣን ቆንጥጠው የቆዩት የሰው ደም በአደባባይ በጥይት እያፈሰሱ በሰውር ደግሞ ደም እየገበሩ ኸሰይጣናዊ አይልና ጉልበት ሲቀበሉ ቆይተዋል። ፨መንፈሳዊ ነገር ያልነቃው ሕዝቤ ቤተሰቡን ልጆቹን መሬቱን ደም እያፈሰሱ ሲገዙና ሲያርዱት የነበረው ለሰይጣን ብለው ነበር። ሰይጣን የሰውና የፈጣሪም ኘላት ሰለሆነ በአጋንንት መንፈስ እየተነዱ አገርና ሕዝቡን የሚገድሉትን በሰይጣን የተሞሉ ሰዎችን ለይታችሁ ለማወቅ መቻል ያስፈልገናል ። የሰው ደም ለማፍሰስ የሚቸኩል ሁሉ በሰይጣን ቁጥጥር ስር ያለ የሰይጣን አገልጋይ እንጂ ሰው ብለን የምንጠራው ከተግባሩ ተቆጥቦ ለሰው ሁሉ መራራት ሲጀመር ብቻ ነው። በ27 የቀለብነው ሰይጣን ከእባብ ወደ ዘንዶ ከዘንዶ ወደ ተምዘግዛጊ ሻርክ ተለዋውጠዋል። አሁን ግን ታላቁ እባብ ሌዋታን የሰው ልጅ ሁሉ ጠላት ጥላቻ፣ ዘረኝነት ፣ ድንቁርና፣ ቅናት፣ ፍርሃት፣ የበታችነት አመለካከት ፣ ነቀትና ትዕቢት ወደ ጉድጓድ ገብተዋል የኢትዮጵያ ሕዝብ በጉድጓዱ ላይ አፈር በመመለስ ለመጨረሻ ጊዜ መቀበር አለበት። ሰላም ለኢትዮጵያውያን እንዱሁም ሰላም ለሰው ልጅ በመሉ። ፈጣሪ አንድ ነው የሰው ዘርም አንድ ነው። ግርማ

    Reply
  2. Tesfa says

    January 23, 2019 11:26 pm at 11:26 pm

    በአለፉት 40 ዓመታት ገደማ የኦሮሞ ህዝብ መብት ተሟጋች ኦነግ እንደነበር ህዝባችን ጠንቅቆ ያውቃል። ኦነግ የራሱን ባንዲራ ያውለበለበ ኦሮሚያ የምትባል ሃገር እንመሰርታለን በማለት ይበልጥ ዘመኑን በአስመራ የመሸጎ የኖረ ድርጅት ነው። በአንጻሩ በእየዓለማቱ በልዪ ልዮ ምክንያት ከሃገር የወጡ ቆራጥና ለኦሮሞ ህዝብ የሚታገሉ ለመኖራቸው እኔ የዓይን ምሥክር ነኝ። ከእነዚህም ቀዳሚውና በመገናኛ አውታሮች ጎልቶ የሚታየው ጆዋር መሃመድ ነው። ጀዋር ባለፉትና በቅርብ ጊዜ ከጀርባችን ላይ ከወረደው የወያኔ አገዛዝ ጭምር የኦሮሞ ህዝብ ግፍ ሲፈጸምበት ያየ እና ለዚህ ህዝብ ነጻነትና እፎይታ በትጋት የታገለ ወገናችን ነው። ያው የእኛው ሃገር ፓለቲካ እድሜ ለወያኔ ሁሉንም በየወገንህ በማለቱ ሰው በፊት ካሳለፍናቸው መንግሥታት ይልቅ በወያኔው አሻጥር ክልልና ቋንቋን ተገን ማድረግ ሲገልና ሲጋደል እንደኖረና አሁንም እንዳለ የየእለቱ የዜና ዘገባዎች ያስረዳሉ።
    የሃገሬ ሰው የሚለው አንድ አባባል አለ ” በየወገንህ ቢሉት የመቶ ዓመት ቆዳ ገቢያ ወጥቶ ቆመ” ይላሉ። ወገንተኝነት አፈረሰን እንጂ አልሰራንም። ዛሬ ለኦሮሞ ህዝብ እንቆረቆራለን የሚሉ ወደ 17 የሚጠጉ ድርጅቶች አሉ። ከእነዚህ ሁሉ የሚከፋው ኦነግ ነው። በወለጋ ህዝባችንን ሲገድል ሲዘርፍ መሪው አቶ ከተማ ተቀምጦ ነጻ አውጣሃለሁ የሚለውን ህዝብ ወታደሮቹ ሲገድሉ የሚያምታታ የፓለቲካ መግለጫ ለዜና አውታሮች በመስጠት የወያኔ የሰውርና የገሃድ ተላላኪ መሆኑ አስነዋሪ ነው። ትጥቅ አልፈታም ማለት ምን ማለት ነው? ኦነግ ትጥቅ ታጥቆ የነበረው የኦሮሞ ህብን ሰቆቃ ለማስታገስ ከሆነ ዛሬ ዝርፊያውና ግድያው ለምንድን ነው? ኦነግ አንድ ማወቅ ያለበት ትልቅ ነጥብ አለ? የኦሮሞን ህዝብ የዛሬ 40 ዓመት በተተለመ አላማ ዛሬ መምራት አይቻልም። ጊዜው ተለውጦአል። ኦነግና ወታደሮቹም ጠበንጃቸውን አስቀምጠው ጠኔና ችጋር ያልተለየውን ህዝባችንን ከድህነት ለማውጣት አፈሙዝ የለሽ ፓለቲካን መከተል አለባቸው። ከዚህ አንጻር ጀዋር መሃመድ በየጊዜው የሚሰጣቸው ወቅታዊና ሃገራዊ እይታዎቹን እጋራለሁ። በርታ አይዞህ እንላለን። ሌሎችም ለምሳሌ ያህል እንደ ዶ/ር አለሙ፤ ዶ/ር መራራና ሌሎች ለኢትዮጵያ አንድነትና ለኦሮሞ ህዝብ ሰላም በፊትም ዛሬም በመታገል ላይ ይገኛሉ። የኦነግ አመራሮች/ደጋፊዎች ያለፈን የጥይት ፓለቲካ በመተው ለህዝባችንና ለሃገራችን በአንድነት እንስራ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule