• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ” ኦቦ ኃይሌ ገብሬ

January 23, 2019 12:15 pm by Editor 2 Comments

በኦሮሞ የባሕል ማዕከል ኦዴፓ ከኦነግ ጋር ስምምነት ባደረገበት ወቅት ዕርቀ ሰላሙን ከመሩት የአገር ሽማግሌዎች መካከል ኦቦ ኃይሌ ገብሬ እጅግ ጥልቅ ንግግር አድርገው ነበር። ይህ በአፋን ኦሮሞ እያለቀሱ የተናገሩት ልብ የሚነካ ንግግር ወደ አማርኛ ሲመለስ እንዲህ የሚል ነበር፤

“ዕርቀ-ሰላም በሚሆንበት ጊዜ እንዲሳካ ከብት ማረድ ካስፈለገ ገዝተን እናርዳለን፤ አይ ከብት አይደለም ሰው ይታረድልን የምትሉ ከሆነ ይኸው የኔን ደም አፍስሱና ኦሮሞን አስታርቁልኝ”።

ይህንን ዓይነት መስዋዕትነት የተከፈለበት ዕርቀ-ሰላም አንቀበልም የሚሉ በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኃይሎች ለራሳቸው ሲሉ ከዚህ በኋላ ጥንቃቄ ቢያደርጉ መልካም ነው በማለት ስምምነቱን የተካፈሉ ይናገራሉ። የኦሮሞ ሕዝብ ከዚህ በኋላ ማንኛውንም ዓይነት ከፋፋይና ደም አፋሳሽ ተግባር መሸከም የሚችልበት ትከሻ የለውም። በኦሮሞ ስም ሊያበረክቱት የሚፈልጉት ካለ ሕዝባቸውን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል ብቻ ነው፤ እንደ ኦቦ ኃይሌ ገብሬ ዓይነቱን ጨዋና አገር ወዳድ እጅግ ያበርክትልን በማለት ለጎልጉል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: News Tagged With: haile gebre, Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. gi Haile says

    January 23, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    የሕዝባችንን ደም ሲያፈስና ሲያስፈስስ የነበረው ሰይጣንና ሰይጣን የጠየቃቸውን ደም በመፍረስ አብት ያካበቱ በጠንቋይ እየተመሩ መንግስን ስልጣን ቆንጥጠው የቆዩት የሰው ደም በአደባባይ በጥይት እያፈሰሱ በሰውር ደግሞ ደም እየገበሩ ኸሰይጣናዊ አይልና ጉልበት ሲቀበሉ ቆይተዋል። ፨መንፈሳዊ ነገር ያልነቃው ሕዝቤ ቤተሰቡን ልጆቹን መሬቱን ደም እያፈሰሱ ሲገዙና ሲያርዱት የነበረው ለሰይጣን ብለው ነበር። ሰይጣን የሰውና የፈጣሪም ኘላት ሰለሆነ በአጋንንት መንፈስ እየተነዱ አገርና ሕዝቡን የሚገድሉትን በሰይጣን የተሞሉ ሰዎችን ለይታችሁ ለማወቅ መቻል ያስፈልገናል ። የሰው ደም ለማፍሰስ የሚቸኩል ሁሉ በሰይጣን ቁጥጥር ስር ያለ የሰይጣን አገልጋይ እንጂ ሰው ብለን የምንጠራው ከተግባሩ ተቆጥቦ ለሰው ሁሉ መራራት ሲጀመር ብቻ ነው። በ27 የቀለብነው ሰይጣን ከእባብ ወደ ዘንዶ ከዘንዶ ወደ ተምዘግዛጊ ሻርክ ተለዋውጠዋል። አሁን ግን ታላቁ እባብ ሌዋታን የሰው ልጅ ሁሉ ጠላት ጥላቻ፣ ዘረኝነት ፣ ድንቁርና፣ ቅናት፣ ፍርሃት፣ የበታችነት አመለካከት ፣ ነቀትና ትዕቢት ወደ ጉድጓድ ገብተዋል የኢትዮጵያ ሕዝብ በጉድጓዱ ላይ አፈር በመመለስ ለመጨረሻ ጊዜ መቀበር አለበት። ሰላም ለኢትዮጵያውያን እንዱሁም ሰላም ለሰው ልጅ በመሉ። ፈጣሪ አንድ ነው የሰው ዘርም አንድ ነው። ግርማ

    Reply
  2. Tesfa says

    January 23, 2019 11:26 pm at 11:26 pm

    በአለፉት 40 ዓመታት ገደማ የኦሮሞ ህዝብ መብት ተሟጋች ኦነግ እንደነበር ህዝባችን ጠንቅቆ ያውቃል። ኦነግ የራሱን ባንዲራ ያውለበለበ ኦሮሚያ የምትባል ሃገር እንመሰርታለን በማለት ይበልጥ ዘመኑን በአስመራ የመሸጎ የኖረ ድርጅት ነው። በአንጻሩ በእየዓለማቱ በልዪ ልዮ ምክንያት ከሃገር የወጡ ቆራጥና ለኦሮሞ ህዝብ የሚታገሉ ለመኖራቸው እኔ የዓይን ምሥክር ነኝ። ከእነዚህም ቀዳሚውና በመገናኛ አውታሮች ጎልቶ የሚታየው ጆዋር መሃመድ ነው። ጀዋር ባለፉትና በቅርብ ጊዜ ከጀርባችን ላይ ከወረደው የወያኔ አገዛዝ ጭምር የኦሮሞ ህዝብ ግፍ ሲፈጸምበት ያየ እና ለዚህ ህዝብ ነጻነትና እፎይታ በትጋት የታገለ ወገናችን ነው። ያው የእኛው ሃገር ፓለቲካ እድሜ ለወያኔ ሁሉንም በየወገንህ በማለቱ ሰው በፊት ካሳለፍናቸው መንግሥታት ይልቅ በወያኔው አሻጥር ክልልና ቋንቋን ተገን ማድረግ ሲገልና ሲጋደል እንደኖረና አሁንም እንዳለ የየእለቱ የዜና ዘገባዎች ያስረዳሉ።
    የሃገሬ ሰው የሚለው አንድ አባባል አለ ” በየወገንህ ቢሉት የመቶ ዓመት ቆዳ ገቢያ ወጥቶ ቆመ” ይላሉ። ወገንተኝነት አፈረሰን እንጂ አልሰራንም። ዛሬ ለኦሮሞ ህዝብ እንቆረቆራለን የሚሉ ወደ 17 የሚጠጉ ድርጅቶች አሉ። ከእነዚህ ሁሉ የሚከፋው ኦነግ ነው። በወለጋ ህዝባችንን ሲገድል ሲዘርፍ መሪው አቶ ከተማ ተቀምጦ ነጻ አውጣሃለሁ የሚለውን ህዝብ ወታደሮቹ ሲገድሉ የሚያምታታ የፓለቲካ መግለጫ ለዜና አውታሮች በመስጠት የወያኔ የሰውርና የገሃድ ተላላኪ መሆኑ አስነዋሪ ነው። ትጥቅ አልፈታም ማለት ምን ማለት ነው? ኦነግ ትጥቅ ታጥቆ የነበረው የኦሮሞ ህብን ሰቆቃ ለማስታገስ ከሆነ ዛሬ ዝርፊያውና ግድያው ለምንድን ነው? ኦነግ አንድ ማወቅ ያለበት ትልቅ ነጥብ አለ? የኦሮሞን ህዝብ የዛሬ 40 ዓመት በተተለመ አላማ ዛሬ መምራት አይቻልም። ጊዜው ተለውጦአል። ኦነግና ወታደሮቹም ጠበንጃቸውን አስቀምጠው ጠኔና ችጋር ያልተለየውን ህዝባችንን ከድህነት ለማውጣት አፈሙዝ የለሽ ፓለቲካን መከተል አለባቸው። ከዚህ አንጻር ጀዋር መሃመድ በየጊዜው የሚሰጣቸው ወቅታዊና ሃገራዊ እይታዎቹን እጋራለሁ። በርታ አይዞህ እንላለን። ሌሎችም ለምሳሌ ያህል እንደ ዶ/ር አለሙ፤ ዶ/ር መራራና ሌሎች ለኢትዮጵያ አንድነትና ለኦሮሞ ህዝብ ሰላም በፊትም ዛሬም በመታገል ላይ ይገኛሉ። የኦነግ አመራሮች/ደጋፊዎች ያለፈን የጥይት ፓለቲካ በመተው ለህዝባችንና ለሃገራችን በአንድነት እንስራ!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule