• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦነግ በአማርኛ መግለጫ ባወጣ ጥቂት ቀን “ትጥቃችንን ለኦሮሞ ሕዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” አለ

January 23, 2019 12:30 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያን “አቢሲኒያ ኢምፓዬር” በማለት ሲጠራ የኖረውና ራሱን የኦሮሞ ነጻአውጪ ግምባር ብሎ የሰየመው “ኦነግ” አቢሲኒያ ከሚላት ኢትዮጵያ ለመገንጠል ብቻ ሳይሆን አማርኛንም እንደ ጨቋኝ ቋንቋ በመቁጠር በዚያ ከመጠቀም ተቆጥቦ መኖሩ የሚታወቅ ነው። ለአብነት ያህል በቅርቡ ወዳገር ቤት የገቡት ገላሳ ዲልቦ እነ መለስ በጠሩት የሽግግር መንግሥት ምሥረታ ወቅት በእንግሊዝኛ ሲናገሩ ሌንጮ ለታ ከጎናቸው በመሆን በኦሮሚኛ ያስተረጉሙ ነበር። አሁን ደግሞ እኚሁ ገላሳ ዲልቦ በየሚዲያው በአማርና ቃለምልልስ ብቻ ሳይሆን ቅኔም ሲዘርፉ ሰምተናል።

በግሩም የአማርኛ ብሒል የታጀበውና “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር በሚል ርዕስ የወጣው የኦነግ መግለጫ ያተኮረው መንግሥት ምዕራብ ወለጋን በአየር ስለመደብደቡ የጠ/ሚ/ሩ ፕሬስ ክፍል (እንግሊዝኛ) ቢልለኔ ስዩም ማስተባበላቸውን ተከትሎ ነው።

አራርሳ ቢቂላ

ከዚህ የኦነግ መግለጫ በኋላ ማክሰኞ በአዲስ አበባ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከል በተካሄደው ዕርቀ ሰላም ጉባዔ ላይ ዳውድ ኢብሳ “ከዛሬ ጀምሮ ትጥቃችንን ለኦሮሞ ህዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” ማለታቸው ተሰምቷል።

በሌላ በኩል የዳውድ ኢብሣ ምክትል ናቸው የሚባሉት አራርሳ ቢቂላ ደግሞ ይህንን ሲሉ በኦኤምኤን ላይ ተደምጠዋል፤ “ጦራችን ህዝቡን ብሎ ፍራፍሬ እና የእንጨት ልጣጭ እየተመገበ ብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፏል። አሁን ዝለናል። ከዚህ በኋላ ጦርነት የሚባል ነገር አያስፈልግም። ከዚህ በኋላ ለኦሮሞ ህዝብ የሚያስፈልገው ሰላም ነው። ትብብር ነው። ጦሩ በሰላም ከህዝቡ ጋር እንዳይቀላቀል የሚያደርጉ ኃይሎችን ከዚህ በኋላ በዘመቻ መልክ ልንከላከላቸው ያስፈጋል። እኛ ሥልጣን ብለን አልመጣንም። እኛ ምን መደረግ እራሱ እንዳለብን ገና ከህዝባችን ጋር በደንብ አልተነጋገርንም። እኛ የምንፈልገው ወንበር አይደለም። እኛ የምንፈልገው ይሄ በሕዝባችን መሰዋዕትነት የተገኘው ለውጥ እንዳይቀለበስ ነው። ይህ ለውጥ እንዲቀለበስ ብዙ ኃይሎች ይፈልጋሉ። ስለዚህ እኛ የምንፈልገው ይህ ለውጥ እንዳይቀለበስና እውነተኛ ዲሞክራሲ በሀገራችን እንዲሰፍን ከመንግሥት እና ከሌሎች ኃይሎች ጋር በሰላምና በትብብር መሥራት ነው።”

በዕርቀ ሰላም መድረኩ ላይ በአባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች፣ የተለያዩ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ግለሰቦች ተሳትፈዋል።

አባገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች በመድረክ ላይ በአንድነት በመቆም በፓርቲዎች መካከል ዕርቅ እንዲሰፍንና ሰላም እንዲወርድ ያቀረቡት ጥያቄ በሁሉም አካላት ተቀባይነት አገኝቷል።

በጉባዔው ላይ የተገኙት የኦዴፓ ዋና ፀሀፊ አለሙ ስሜ በበኩላቸው እኛ የምንፈልገው ሰላምን ማስፈን አንድነትን ማጠናከር እንጂ ከኦነግ ጋር ምንም ችግር እንደሌለባቸው ተናግረዋል።

ኦነግ ቃሉን ከጠበቀና እንዳለውም ትጥቁን ለአባ ገዳዎች ያስረከበ ከሆነ “ተደረገብኝ” ከሚለው የአየር ድብደባ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም ከሚደርስበት ከባድ ሽንፈት ራሱን ያድናል። “ነጻ አወጣዋለሁ” ለሚለው ሕዝብም የተሻለ አማራጭ ለማምጣት የሚችልበትን መንገድ ማመቻቸት ይችላል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ እንደ ደብረጽዮን 45 ደቂቃ ለሰላም 45 ደቂቃ ደግሞ ለትጥቅ ትግል እጫወታለሁ ብሎ የሚያስብ ከሆነ “እታገልለታለሁ” በሚለው በራሱ ሕዝብ ይተፋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


በአማርኛ የወጣው የኦነግ መግለጫ ሙሉቃል እንዲህ ይነበባል፤

“ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር

(የኦነግ መግለጫ – ጥር 09 2011)

የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት በትናንትናው ዕለት (ጥር 09 2011) በቃል-ኣቀባዩ ወይዘሪት ብልለኔ ስዩም በኩል በምዕራብ ኦሮሚያ ጦሩ ያካሄደዉን የአየር ድብደባ ለማስተባበል በማሰብ ለተለያዩ የዜና አዉታሮች የሰጠዉ መግለጫ እጅጉን ከእዉነት የራቀ ነዉ። ይህ የአየር ድብደባ ለሁለት ተከታታይ ቀናት (ጥር 4 እና 5 2011) በቄሌም ወለጋ ዞን በጊዳሚ ወረዳ በቄሌም ከተማና አካባቢዋ በሶስት የተላያዩ ቦታዎች ለይ ነዉ የተካሄደዉ።

በዚህ ደረጃ የተካሄደዉን የአየር ድብደባ ለመካድ መሞከር ማለት “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” እንደሚባለዉ ኣይነት ልደበቅ የማይቻለዉን እዉነታ ለመደበቅ የሚደረግ ከንቱ ልፋት ነው።

ከዚሁ የአየር ድብደባ በተጨማሪም የኢሕአዴግ እግረኛ ጦር ሠራዊት በዚሁ ኣካባቢ ሰላማዊዉን ሕዝብ በመግደል፣ መኖሪያ ቤቶቹን በማቃጠል፣ ንግድ ቤቶቹን በማፈራረስና ንብረት በመዝረፍ እንድሁም ሰዎችን በጅምላ በማሰርና በማሰቃየት እኩይ ድርጊቶች ላይ ተጠምደዋል። በጊዳሚ ወረዳ ዉስጥ በአየር ሓይልና በእግረኛ ጦር በተካሄደዉ በዚህ ጥቃት እስካሁን የተረጋገጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የሰባት (7) ሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ዜጎች ሕይወት ማለፉ ታዉቋል። ከሞቱት መካከል ኣንዷ ከአየር ወደ መሬት በሚወረወሩ ቦምቦች የፍንዳታ ድምጽ ልቧ ቆሞ የሞተች የሁለት ወር ሕጻን እንደሆነችም ታዉቋል። 8 የሕዝቡ መኖሪያ ቤቶች በእሳት ጋይቷል። 20 ንግድ ቤቶችም በኢሕአዴግ ወታደሮች ተዘርፎ ተፈራርሷል። እነዚህ በጊዳሚ ወረዳ ዉስጥ የአየር ጥቃቱ በተካሄደበት ኣካባቢ ብቻ የተፈጸሙ ናቸዉ። ግድያና ጦርነት እየተካሄደባቸዉ ባሉት በኣራቱ የወለጋ ዞኖችም በነዚሁ የኢሕአዴግ ወታደሮች የተገደሉት ሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ሰዎች የተቃጠሉ ቤቶች፣ የተዘረፉና የወደሙ ንብረቶች ዝርዝራቻዉ በርካታ ስሆን ለወደፊቱ ተጣርቶ እንደሚዘገቡ እናሳዉቃለን።

ይህ የጠቅላይ ሚንስቴሩ ጽ/ቤት መግለጫ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) መንገድ መዝጋቱን፣ ባንኮችን መዝረፉን፣ ሕዝብን ማሰቃየቱን፣ እና ሌሎችም ፀረ-ሰላም ድርጊቶችን መፈጸሙን በማተት ለዚህ ጥቃት እንደምክንያት ያቀርባል። ይህ የመንግስት ክስ ፍጹም ከእዉነት የራቀ ነዉ። ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ብቻ የተጀመረዉን የለዉጥ ሂደት ለማሳካት በሙሉ ልቡ እየሰራ ባለበት ሁኔታ የተላያዩ እንቅፋቶችን በመፍጠር የስምምነታችን መንፈስ እንድደፈርስና ስምምነቱን ተግባራዊ የማድረጉ ሂደት እንድጓተት እያደረገ ያለዉ ኦነግ ሳይሆን እራሱ ኢሕአዴግ ነው። ይህ ጦርነት ኢሕአዴግ በስመ ሃገር መከላከያ ሠራዊት ለራሱ ጥቅም ያደራጀዉና እስከዛሬም ሕዝባዊ ኣለኝታነትን ያልተላበሰዉን ጦሩን ተጠቅሞ ኦነግንና የግንባሩን የፖለቲካ አመለካከት ያላቸዉን ወገኖች ለማዳከም የሚያካሄድ ጦርነት መሆኑ ለማንም ግልጽ መሆን ኣለበት።

ኦነግ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተደረሰበት ስምምነት በሰላማዊ መንገድ ተግባራዊ ሆኖ ሃገርና ሕዝቦችም ሰላም ያግኙ ዘንድ ይህ ጦርነት በኣፋጣኝ መቆም ኣለበት ብሎ ያምናል። ከዚያም በመቀጠል በመንግስት በኩል እየቀረቡብን ያሉና እኛም በበኩላችን በእኛና በሕዝባችን ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ግፎች ናቸዉ የሚንላቸዉ (የሁለቱም ወገን) ስሞታና ቅሬታዎች በገለልተኛ ወገን ተመርምሮና ተጣርቶ ሓቁ እንድወጣ/እንድታይ ኦነግ ኣጥብቆ ይጠይቃል።

ድል ለኦሮሞ ሕዝብ!
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር
ጥር 09, 2011

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule