• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦነግ በአማርኛ መግለጫ ባወጣ ጥቂት ቀን “ትጥቃችንን ለኦሮሞ ሕዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” አለ

January 23, 2019 12:30 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያን “አቢሲኒያ ኢምፓዬር” በማለት ሲጠራ የኖረውና ራሱን የኦሮሞ ነጻአውጪ ግምባር ብሎ የሰየመው “ኦነግ” አቢሲኒያ ከሚላት ኢትዮጵያ ለመገንጠል ብቻ ሳይሆን አማርኛንም እንደ ጨቋኝ ቋንቋ በመቁጠር በዚያ ከመጠቀም ተቆጥቦ መኖሩ የሚታወቅ ነው። ለአብነት ያህል በቅርቡ ወዳገር ቤት የገቡት ገላሳ ዲልቦ እነ መለስ በጠሩት የሽግግር መንግሥት ምሥረታ ወቅት በእንግሊዝኛ ሲናገሩ ሌንጮ ለታ ከጎናቸው በመሆን በኦሮሚኛ ያስተረጉሙ ነበር። አሁን ደግሞ እኚሁ ገላሳ ዲልቦ በየሚዲያው በአማርና ቃለምልልስ ብቻ ሳይሆን ቅኔም ሲዘርፉ ሰምተናል።

በግሩም የአማርኛ ብሒል የታጀበውና “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር በሚል ርዕስ የወጣው የኦነግ መግለጫ ያተኮረው መንግሥት ምዕራብ ወለጋን በአየር ስለመደብደቡ የጠ/ሚ/ሩ ፕሬስ ክፍል (እንግሊዝኛ) ቢልለኔ ስዩም ማስተባበላቸውን ተከትሎ ነው።

አራርሳ ቢቂላ

ከዚህ የኦነግ መግለጫ በኋላ ማክሰኞ በአዲስ አበባ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከል በተካሄደው ዕርቀ ሰላም ጉባዔ ላይ ዳውድ ኢብሳ “ከዛሬ ጀምሮ ትጥቃችንን ለኦሮሞ ህዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” ማለታቸው ተሰምቷል።

በሌላ በኩል የዳውድ ኢብሣ ምክትል ናቸው የሚባሉት አራርሳ ቢቂላ ደግሞ ይህንን ሲሉ በኦኤምኤን ላይ ተደምጠዋል፤ “ጦራችን ህዝቡን ብሎ ፍራፍሬ እና የእንጨት ልጣጭ እየተመገበ ብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፏል። አሁን ዝለናል። ከዚህ በኋላ ጦርነት የሚባል ነገር አያስፈልግም። ከዚህ በኋላ ለኦሮሞ ህዝብ የሚያስፈልገው ሰላም ነው። ትብብር ነው። ጦሩ በሰላም ከህዝቡ ጋር እንዳይቀላቀል የሚያደርጉ ኃይሎችን ከዚህ በኋላ በዘመቻ መልክ ልንከላከላቸው ያስፈጋል። እኛ ሥልጣን ብለን አልመጣንም። እኛ ምን መደረግ እራሱ እንዳለብን ገና ከህዝባችን ጋር በደንብ አልተነጋገርንም። እኛ የምንፈልገው ወንበር አይደለም። እኛ የምንፈልገው ይሄ በሕዝባችን መሰዋዕትነት የተገኘው ለውጥ እንዳይቀለበስ ነው። ይህ ለውጥ እንዲቀለበስ ብዙ ኃይሎች ይፈልጋሉ። ስለዚህ እኛ የምንፈልገው ይህ ለውጥ እንዳይቀለበስና እውነተኛ ዲሞክራሲ በሀገራችን እንዲሰፍን ከመንግሥት እና ከሌሎች ኃይሎች ጋር በሰላምና በትብብር መሥራት ነው።”

በዕርቀ ሰላም መድረኩ ላይ በአባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች፣ የተለያዩ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ግለሰቦች ተሳትፈዋል።

አባገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች በመድረክ ላይ በአንድነት በመቆም በፓርቲዎች መካከል ዕርቅ እንዲሰፍንና ሰላም እንዲወርድ ያቀረቡት ጥያቄ በሁሉም አካላት ተቀባይነት አገኝቷል።

በጉባዔው ላይ የተገኙት የኦዴፓ ዋና ፀሀፊ አለሙ ስሜ በበኩላቸው እኛ የምንፈልገው ሰላምን ማስፈን አንድነትን ማጠናከር እንጂ ከኦነግ ጋር ምንም ችግር እንደሌለባቸው ተናግረዋል።

ኦነግ ቃሉን ከጠበቀና እንዳለውም ትጥቁን ለአባ ገዳዎች ያስረከበ ከሆነ “ተደረገብኝ” ከሚለው የአየር ድብደባ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም ከሚደርስበት ከባድ ሽንፈት ራሱን ያድናል። “ነጻ አወጣዋለሁ” ለሚለው ሕዝብም የተሻለ አማራጭ ለማምጣት የሚችልበትን መንገድ ማመቻቸት ይችላል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ እንደ ደብረጽዮን 45 ደቂቃ ለሰላም 45 ደቂቃ ደግሞ ለትጥቅ ትግል እጫወታለሁ ብሎ የሚያስብ ከሆነ “እታገልለታለሁ” በሚለው በራሱ ሕዝብ ይተፋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


በአማርኛ የወጣው የኦነግ መግለጫ ሙሉቃል እንዲህ ይነበባል፤

“ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር

(የኦነግ መግለጫ – ጥር 09 2011)

የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት በትናንትናው ዕለት (ጥር 09 2011) በቃል-ኣቀባዩ ወይዘሪት ብልለኔ ስዩም በኩል በምዕራብ ኦሮሚያ ጦሩ ያካሄደዉን የአየር ድብደባ ለማስተባበል በማሰብ ለተለያዩ የዜና አዉታሮች የሰጠዉ መግለጫ እጅጉን ከእዉነት የራቀ ነዉ። ይህ የአየር ድብደባ ለሁለት ተከታታይ ቀናት (ጥር 4 እና 5 2011) በቄሌም ወለጋ ዞን በጊዳሚ ወረዳ በቄሌም ከተማና አካባቢዋ በሶስት የተላያዩ ቦታዎች ለይ ነዉ የተካሄደዉ።

በዚህ ደረጃ የተካሄደዉን የአየር ድብደባ ለመካድ መሞከር ማለት “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” እንደሚባለዉ ኣይነት ልደበቅ የማይቻለዉን እዉነታ ለመደበቅ የሚደረግ ከንቱ ልፋት ነው።

ከዚሁ የአየር ድብደባ በተጨማሪም የኢሕአዴግ እግረኛ ጦር ሠራዊት በዚሁ ኣካባቢ ሰላማዊዉን ሕዝብ በመግደል፣ መኖሪያ ቤቶቹን በማቃጠል፣ ንግድ ቤቶቹን በማፈራረስና ንብረት በመዝረፍ እንድሁም ሰዎችን በጅምላ በማሰርና በማሰቃየት እኩይ ድርጊቶች ላይ ተጠምደዋል። በጊዳሚ ወረዳ ዉስጥ በአየር ሓይልና በእግረኛ ጦር በተካሄደዉ በዚህ ጥቃት እስካሁን የተረጋገጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የሰባት (7) ሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ዜጎች ሕይወት ማለፉ ታዉቋል። ከሞቱት መካከል ኣንዷ ከአየር ወደ መሬት በሚወረወሩ ቦምቦች የፍንዳታ ድምጽ ልቧ ቆሞ የሞተች የሁለት ወር ሕጻን እንደሆነችም ታዉቋል። 8 የሕዝቡ መኖሪያ ቤቶች በእሳት ጋይቷል። 20 ንግድ ቤቶችም በኢሕአዴግ ወታደሮች ተዘርፎ ተፈራርሷል። እነዚህ በጊዳሚ ወረዳ ዉስጥ የአየር ጥቃቱ በተካሄደበት ኣካባቢ ብቻ የተፈጸሙ ናቸዉ። ግድያና ጦርነት እየተካሄደባቸዉ ባሉት በኣራቱ የወለጋ ዞኖችም በነዚሁ የኢሕአዴግ ወታደሮች የተገደሉት ሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ሰዎች የተቃጠሉ ቤቶች፣ የተዘረፉና የወደሙ ንብረቶች ዝርዝራቻዉ በርካታ ስሆን ለወደፊቱ ተጣርቶ እንደሚዘገቡ እናሳዉቃለን።

ይህ የጠቅላይ ሚንስቴሩ ጽ/ቤት መግለጫ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) መንገድ መዝጋቱን፣ ባንኮችን መዝረፉን፣ ሕዝብን ማሰቃየቱን፣ እና ሌሎችም ፀረ-ሰላም ድርጊቶችን መፈጸሙን በማተት ለዚህ ጥቃት እንደምክንያት ያቀርባል። ይህ የመንግስት ክስ ፍጹም ከእዉነት የራቀ ነዉ። ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ብቻ የተጀመረዉን የለዉጥ ሂደት ለማሳካት በሙሉ ልቡ እየሰራ ባለበት ሁኔታ የተላያዩ እንቅፋቶችን በመፍጠር የስምምነታችን መንፈስ እንድደፈርስና ስምምነቱን ተግባራዊ የማድረጉ ሂደት እንድጓተት እያደረገ ያለዉ ኦነግ ሳይሆን እራሱ ኢሕአዴግ ነው። ይህ ጦርነት ኢሕአዴግ በስመ ሃገር መከላከያ ሠራዊት ለራሱ ጥቅም ያደራጀዉና እስከዛሬም ሕዝባዊ ኣለኝታነትን ያልተላበሰዉን ጦሩን ተጠቅሞ ኦነግንና የግንባሩን የፖለቲካ አመለካከት ያላቸዉን ወገኖች ለማዳከም የሚያካሄድ ጦርነት መሆኑ ለማንም ግልጽ መሆን ኣለበት።

ኦነግ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተደረሰበት ስምምነት በሰላማዊ መንገድ ተግባራዊ ሆኖ ሃገርና ሕዝቦችም ሰላም ያግኙ ዘንድ ይህ ጦርነት በኣፋጣኝ መቆም ኣለበት ብሎ ያምናል። ከዚያም በመቀጠል በመንግስት በኩል እየቀረቡብን ያሉና እኛም በበኩላችን በእኛና በሕዝባችን ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ግፎች ናቸዉ የሚንላቸዉ (የሁለቱም ወገን) ስሞታና ቅሬታዎች በገለልተኛ ወገን ተመርምሮና ተጣርቶ ሓቁ እንድወጣ/እንድታይ ኦነግ ኣጥብቆ ይጠይቃል።

ድል ለኦሮሞ ሕዝብ!
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር
ጥር 09, 2011

 

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule