• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦነግ በአማርኛ መግለጫ ባወጣ ጥቂት ቀን “ትጥቃችንን ለኦሮሞ ሕዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” አለ

January 23, 2019 12:30 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያን “አቢሲኒያ ኢምፓዬር” በማለት ሲጠራ የኖረውና ራሱን የኦሮሞ ነጻአውጪ ግምባር ብሎ የሰየመው “ኦነግ” አቢሲኒያ ከሚላት ኢትዮጵያ ለመገንጠል ብቻ ሳይሆን አማርኛንም እንደ ጨቋኝ ቋንቋ በመቁጠር በዚያ ከመጠቀም ተቆጥቦ መኖሩ የሚታወቅ ነው። ለአብነት ያህል በቅርቡ ወዳገር ቤት የገቡት ገላሳ ዲልቦ እነ መለስ በጠሩት የሽግግር መንግሥት ምሥረታ ወቅት በእንግሊዝኛ ሲናገሩ ሌንጮ ለታ ከጎናቸው በመሆን በኦሮሚኛ ያስተረጉሙ ነበር። አሁን ደግሞ እኚሁ ገላሳ ዲልቦ በየሚዲያው በአማርና ቃለምልልስ ብቻ ሳይሆን ቅኔም ሲዘርፉ ሰምተናል።

በግሩም የአማርኛ ብሒል የታጀበውና “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር በሚል ርዕስ የወጣው የኦነግ መግለጫ ያተኮረው መንግሥት ምዕራብ ወለጋን በአየር ስለመደብደቡ የጠ/ሚ/ሩ ፕሬስ ክፍል (እንግሊዝኛ) ቢልለኔ ስዩም ማስተባበላቸውን ተከትሎ ነው።

አራርሳ ቢቂላ

ከዚህ የኦነግ መግለጫ በኋላ ማክሰኞ በአዲስ አበባ በሚገኘው የኦሮሞ ባህል ማዕከል በተካሄደው ዕርቀ ሰላም ጉባዔ ላይ ዳውድ ኢብሳ “ከዛሬ ጀምሮ ትጥቃችንን ለኦሮሞ ህዝብና ለአባ ገዳዎቻችን አስረክበናል” ማለታቸው ተሰምቷል።

በሌላ በኩል የዳውድ ኢብሣ ምክትል ናቸው የሚባሉት አራርሳ ቢቂላ ደግሞ ይህንን ሲሉ በኦኤምኤን ላይ ተደምጠዋል፤ “ጦራችን ህዝቡን ብሎ ፍራፍሬ እና የእንጨት ልጣጭ እየተመገበ ብዙ ውጣ ውረድ ውስጥ አልፏል። አሁን ዝለናል። ከዚህ በኋላ ጦርነት የሚባል ነገር አያስፈልግም። ከዚህ በኋላ ለኦሮሞ ህዝብ የሚያስፈልገው ሰላም ነው። ትብብር ነው። ጦሩ በሰላም ከህዝቡ ጋር እንዳይቀላቀል የሚያደርጉ ኃይሎችን ከዚህ በኋላ በዘመቻ መልክ ልንከላከላቸው ያስፈጋል። እኛ ሥልጣን ብለን አልመጣንም። እኛ ምን መደረግ እራሱ እንዳለብን ገና ከህዝባችን ጋር በደንብ አልተነጋገርንም። እኛ የምንፈልገው ወንበር አይደለም። እኛ የምንፈልገው ይሄ በሕዝባችን መሰዋዕትነት የተገኘው ለውጥ እንዳይቀለበስ ነው። ይህ ለውጥ እንዲቀለበስ ብዙ ኃይሎች ይፈልጋሉ። ስለዚህ እኛ የምንፈልገው ይህ ለውጥ እንዳይቀለበስና እውነተኛ ዲሞክራሲ በሀገራችን እንዲሰፍን ከመንግሥት እና ከሌሎች ኃይሎች ጋር በሰላምና በትብብር መሥራት ነው።”

በዕርቀ ሰላም መድረኩ ላይ በአባገዳዎች፣ ሃደ ሲንቄዎች፣ የተለያዩ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶችና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ግለሰቦች ተሳትፈዋል።

አባገዳዎች እና ሃደ ሲንቄዎች በመድረክ ላይ በአንድነት በመቆም በፓርቲዎች መካከል ዕርቅ እንዲሰፍንና ሰላም እንዲወርድ ያቀረቡት ጥያቄ በሁሉም አካላት ተቀባይነት አገኝቷል።

በጉባዔው ላይ የተገኙት የኦዴፓ ዋና ፀሀፊ አለሙ ስሜ በበኩላቸው እኛ የምንፈልገው ሰላምን ማስፈን አንድነትን ማጠናከር እንጂ ከኦነግ ጋር ምንም ችግር እንደሌለባቸው ተናግረዋል።

ኦነግ ቃሉን ከጠበቀና እንዳለውም ትጥቁን ለአባ ገዳዎች ያስረከበ ከሆነ “ተደረገብኝ” ከሚለው የአየር ድብደባ ብቻ ሳይሆን ወደፊትም ከሚደርስበት ከባድ ሽንፈት ራሱን ያድናል። “ነጻ አወጣዋለሁ” ለሚለው ሕዝብም የተሻለ አማራጭ ለማምጣት የሚችልበትን መንገድ ማመቻቸት ይችላል። ይህ ሳይሆን ቀርቶ እንደ ደብረጽዮን 45 ደቂቃ ለሰላም 45 ደቂቃ ደግሞ ለትጥቅ ትግል እጫወታለሁ ብሎ የሚያስብ ከሆነ “እታገልለታለሁ” በሚለው በራሱ ሕዝብ ይተፋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


በአማርኛ የወጣው የኦነግ መግለጫ ሙሉቃል እንዲህ ይነበባል፤

“ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” ኣይደበቅ ነገር

(የኦነግ መግለጫ – ጥር 09 2011)

የኢትዮጵያዉ ጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት በትናንትናው ዕለት (ጥር 09 2011) በቃል-ኣቀባዩ ወይዘሪት ብልለኔ ስዩም በኩል በምዕራብ ኦሮሚያ ጦሩ ያካሄደዉን የአየር ድብደባ ለማስተባበል በማሰብ ለተለያዩ የዜና አዉታሮች የሰጠዉ መግለጫ እጅጉን ከእዉነት የራቀ ነዉ። ይህ የአየር ድብደባ ለሁለት ተከታታይ ቀናት (ጥር 4 እና 5 2011) በቄሌም ወለጋ ዞን በጊዳሚ ወረዳ በቄሌም ከተማና አካባቢዋ በሶስት የተላያዩ ቦታዎች ለይ ነዉ የተካሄደዉ።

በዚህ ደረጃ የተካሄደዉን የአየር ድብደባ ለመካድ መሞከር ማለት “ግመል ሰርቆ ኣጎምብሶ” እንደሚባለዉ ኣይነት ልደበቅ የማይቻለዉን እዉነታ ለመደበቅ የሚደረግ ከንቱ ልፋት ነው።

ከዚሁ የአየር ድብደባ በተጨማሪም የኢሕአዴግ እግረኛ ጦር ሠራዊት በዚሁ ኣካባቢ ሰላማዊዉን ሕዝብ በመግደል፣ መኖሪያ ቤቶቹን በማቃጠል፣ ንግድ ቤቶቹን በማፈራረስና ንብረት በመዝረፍ እንድሁም ሰዎችን በጅምላ በማሰርና በማሰቃየት እኩይ ድርጊቶች ላይ ተጠምደዋል። በጊዳሚ ወረዳ ዉስጥ በአየር ሓይልና በእግረኛ ጦር በተካሄደዉ በዚህ ጥቃት እስካሁን የተረጋገጡ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የሰባት (7) ሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ዜጎች ሕይወት ማለፉ ታዉቋል። ከሞቱት መካከል ኣንዷ ከአየር ወደ መሬት በሚወረወሩ ቦምቦች የፍንዳታ ድምጽ ልቧ ቆሞ የሞተች የሁለት ወር ሕጻን እንደሆነችም ታዉቋል። 8 የሕዝቡ መኖሪያ ቤቶች በእሳት ጋይቷል። 20 ንግድ ቤቶችም በኢሕአዴግ ወታደሮች ተዘርፎ ተፈራርሷል። እነዚህ በጊዳሚ ወረዳ ዉስጥ የአየር ጥቃቱ በተካሄደበት ኣካባቢ ብቻ የተፈጸሙ ናቸዉ። ግድያና ጦርነት እየተካሄደባቸዉ ባሉት በኣራቱ የወለጋ ዞኖችም በነዚሁ የኢሕአዴግ ወታደሮች የተገደሉት ሰላማዊ (ትጥቅ-ኣልባ) ሰዎች የተቃጠሉ ቤቶች፣ የተዘረፉና የወደሙ ንብረቶች ዝርዝራቻዉ በርካታ ስሆን ለወደፊቱ ተጣርቶ እንደሚዘገቡ እናሳዉቃለን።

ይህ የጠቅላይ ሚንስቴሩ ጽ/ቤት መግለጫ የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት (ኦነሠ) መንገድ መዝጋቱን፣ ባንኮችን መዝረፉን፣ ሕዝብን ማሰቃየቱን፣ እና ሌሎችም ፀረ-ሰላም ድርጊቶችን መፈጸሙን በማተት ለዚህ ጥቃት እንደምክንያት ያቀርባል። ይህ የመንግስት ክስ ፍጹም ከእዉነት የራቀ ነዉ። ኦነግ በሰላማዊ መንገድ ብቻ የተጀመረዉን የለዉጥ ሂደት ለማሳካት በሙሉ ልቡ እየሰራ ባለበት ሁኔታ የተላያዩ እንቅፋቶችን በመፍጠር የስምምነታችን መንፈስ እንድደፈርስና ስምምነቱን ተግባራዊ የማድረጉ ሂደት እንድጓተት እያደረገ ያለዉ ኦነግ ሳይሆን እራሱ ኢሕአዴግ ነው። ይህ ጦርነት ኢሕአዴግ በስመ ሃገር መከላከያ ሠራዊት ለራሱ ጥቅም ያደራጀዉና እስከዛሬም ሕዝባዊ ኣለኝታነትን ያልተላበሰዉን ጦሩን ተጠቅሞ ኦነግንና የግንባሩን የፖለቲካ አመለካከት ያላቸዉን ወገኖች ለማዳከም የሚያካሄድ ጦርነት መሆኑ ለማንም ግልጽ መሆን ኣለበት።

ኦነግ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተደረሰበት ስምምነት በሰላማዊ መንገድ ተግባራዊ ሆኖ ሃገርና ሕዝቦችም ሰላም ያግኙ ዘንድ ይህ ጦርነት በኣፋጣኝ መቆም ኣለበት ብሎ ያምናል። ከዚያም በመቀጠል በመንግስት በኩል እየቀረቡብን ያሉና እኛም በበኩላችን በእኛና በሕዝባችን ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ግፎች ናቸዉ የሚንላቸዉ (የሁለቱም ወገን) ስሞታና ቅሬታዎች በገለልተኛ ወገን ተመርምሮና ተጣርቶ ሓቁ እንድወጣ/እንድታይ ኦነግ ኣጥብቆ ይጠይቃል።

ድል ለኦሮሞ ሕዝብ!
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር
ጥር 09, 2011

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule