ማን ነው እሱ አንበሳ ፤ ክህደትን ከሀዲ በመላ ምርኮ ጣይ ፤ የሐበሻ ጋንዲ ታሪክ ሠሪ አርበኛ ፤ ልበ ሙሉ ጀግና ምርጥ ብርቅ ዜጋ ፤ ኮስታራ ቆፍጣና በንስር ክንፎቹ ፤ አየር ላየር ሔዶ ሽው ባይ እንደ ነፋስ ፤ ዱብ እንደ በረዶ ምርኮን በዓይነት ይዞ ፤ ጠፍንጎ ቀፍድዶ መቸ ይህ ብቻ ነው ፤ ቆራጡ ሳተና ከእኛ ጋር የሆኑ ፤ አሉን ብዙ ገና እውነት መሰላቹህ? ፤ ቢመስል ደናና ምንም እንዳልከፋው ፤ ቢታይ ብሎ ዘና ልክ እንደተመቸው ፤ ቢስቅ በገናና ሀገር ሕዝብ የጠላ ፤ ከጦር ማን አለና ለማን ሲል ገባና ፤ አይደል ለጅል ዝና ለእናት ሀገሩ እንጅ ፤ ላለበት አደራ ለወገኑ እንጅ ፤ ሊያድን ከመከራ አይደለም ለቡድን ፤ ለጎጥ ለደንባራ ለጠባብ ጥርቅም ፤ ለቅጥረኛ ጎራ ከነ አካይስት በቀር ፤ ከነ ሕልመ … [Read more...] about ጀግና!
Literature
ጽፈኪን
አገሬ!
የኔነት መለያ ~ የናት ያባቴ አገር ~ የተወለድኩባት፣ ስረ መሰረቴ ~ ቅርንጫፍ ሀረጌ ~ እትብቴ ያለባት፣ ተስፋዬ : ውጥነኔ ~ ህልሜ ሚፈታባት፣ ሀገሬ የኔ ናት~ ፣ ሀገሬ እርስቴ ናት~። አፈሩን ፈጭቼ ፣ ውሀ ተራጥቼ ፣ ዘልዬ ቦርቄ ~ ያደኩበት መንደር ፣ በሀሳብ በርሬ ~ በምናብ ከንፌ~ የማርፍባት ሰፈር ፣ የማንነቴ ምንጭ ~ መመኪያ አገሬ፣ አድባሬ አውጋሬ ፣ የዘወትር ህልሜ ~ የድካሜ እፎይታ ~ ማረፊያዬ ጎጆዬ፣ የትም የትም ዞሬ ~ ማሳረጊያ ቤቴ ~ አንገት ማስገቢያዬ፣ አገሬ እማማዬ ። ቀየሩት ይሉኛል ~ አፈረሱት አሉኝ ~ ለወጡት ባዱኛ፣ የኛ ሰፈርማ ፣ ሜዳው ሸንተሩ ~ መቦረቂያ መስኩ ~ አሁን የት አለና፣ ተሸጠ ለሌላ ~ የነሱን ኪስ ሞላ። ይህው በቀደም ለት ፣ ደውዬ ልጠይቅ ~ የወዳጅ ደህንነት፣ ስልኩ ጠርቶ ጠርቶ ~ "• • … [Read more...] about አገሬ!
ዘመን ሞቷል – ኃይሉ አትበሉ
ማስታወሻው ጠፍቶ ምስሉ ተገርስሶ ወድቆ አካሉ ተሰርዞ ቃለ ውሉ ዘመን ሞቷል ኃይሉ አትበሉ። ታሪክ የለም አምልጦናል ዘመን ቆመን ሞቶብናል ሁሉም አልቆ ተጠቃሏል ጋሼ ኃይሉ ይዞት ሄዷል ለዘመን ነው እንባ ማፍሰስ ለታሪክ ነው ከል መልበስ ለጊዜ ነው ፊት መከስከስ ለጋሽ ኃይሉ ይብቃን ማልቀስ የዘመንን በሞት ማምለጥ የጊዜውን መገላበጥ ገና በፊት ጋሼ ኃይሉ ተናግሮታል በአፉ ሙሉ መጣ ብለን ሚሊኒየም በክብሩ ላይ ልንታደም ወዲያ ወዲህ ስንሯሯጥ ምድር ስንቀድ ሰማይ ስንፈልጥ ከረምንና አገር ወጥቶ ተበልቶና ተጠጥቶ ጋሼ ኃይሉ ብቻ ቀርቶ ምነው ጠፋህ? በዚህ በዓል አንተ ብቻ ብሎ ሲባል ያልኖርኩትን አላከብርም ይሄ በዓል የኔ አይደለም መች ኖሬ ነው የማከብረው የኔ ዘመን ሞቷል ተወው ብሎ ነበር መልስ የሰጠው ጋሼ ኃይሉ እንዲህ … [Read more...] about ዘመን ሞቷል – ኃይሉ አትበሉ
“ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…”፤ [“የቲፎዞነት” ዘመን]
እንዴት ሰነበታችሁሳ! ሀሳብ አለን … ስብስባዎች ሁሉ … አለ አይደል… “እንዴት ሰነበታችሁ…” በሚል ብቻ ይከፈትና ወደ ጉዳዩ ይገባ! አሀ … “ክቡር እከሌ እከሌ፣” “ክብርት እከሊት እከሌ፣” “የተከበሩ እከሌ እከሌ” … ምናምን ሲባል የስብሰባው ሲሦ እያለቀ ነዋ! ለነገሩ … (“ለምን ይዋሻል!” የሚሉት ነገር ነበረ አይደል!) ብዙ ስብሰባዎች ላይ “እንትንህን እንደ ዳናኪል እንፋሎት እንዳላቦንልህ!” አይነት “የጉልበት ግማሹ ምላስ ነው…” ነገር በዝቷላ! (እኔ የምለው … አንዳንዱ መድረክ ላይ ወጥቶ እንዴት ነው እንዲህ ‘ልክ ልክ ማጠጣት’ የሚዋጣለት!) አንድ ወዳጃችን ሲነግረን አለቅየው ‘መጠመቁን’ ለበላዮቹ ለማስመስከር የማይሞክረው ነገር የለም፡፡ በተለይ ስብሰባዎች ላይ የሚናገረው ‘ቦተሊካ’ ነክ ንግግር ካርል ማርክስን ጢሙንና ጸጉሩን አርግፎለት ‘አይ ሮቦት’ ነገር … [Read more...] about “ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…”፤ [“የቲፎዞነት” ዘመን]
የድል ፍሬ ፀሐይ
የሕይዎት ዋስትና ፤ የፍጥረቱ ሲሳይ ሃሌታዊ ጀምበር ፤ ለዚህች ማሕሌታይ የተስፋ ብርሃን ፤ የማለዳ ፀሐይ የድል በረከቱ ፤ መከራን ገላጋይ እፎይታን አስኮምኳኝ ፤ ሁሉንም አማላይ ኧረ ምን ነው ቀረሽ ፤ እባክሽ ቶሎ ነይ፡፡ አዝርቱን ውርጭ መታው ፤ ቀረ እንደ ጫጨ አውድማው ነጠፈ ፤ ዘር መክለፍት ተፈጨ ሁሉም በቁር ጠፋ ፤ ውሽንፍሩ አፋጨ ሕይዎት ያለው ፍጥረት ፤ በአጭሩ ተቀጨ የማለዳ ፀሐይ ፤ ሕይዎት መታደያ ምን ነው በአፍሪካ ፤ ምን ነው በኢትዮጵያ ሌሊቱ ረዘመ ፤ ምንድነው ምክንያቱ አትወጭም እንዴ! ፤ ገደለን ምኞቱ የድል ፍሬ ፀሐይ ፤ የፍጥረት ሕይዎቱ በነፍስ ድረሽልን ፤ ይንጋልን ሌሊቱ፡፡ ቁር የቀፈደደው ፤ ያስቀመጠው አስሮ ልሳኑ የተያዘ ፤ የደረቀው ከሮ በሙቀትሽ ይንቃ ፤ ይፈታ ሞት … [Read more...] about የድል ፍሬ ፀሐይ
ጎሞራው ሄደ አሉ ሳይሰናበተን
በገንዘብ ሲኮራ - ሰው በወርቅ ሲያጌጥ፤ ጎሞራው በቅኔ - ነበር ይንቆጠቆጥ፤ ኩታው ነበር ቃላት - ካባው ነበር ስንኝ፤ ጎሞራው ሲቋጥር - ለወገኑ ሲቀኝ:: ሄደ አሉ ጎሞራው - ሁሉን ነገር ንቆ፤ ሊቀኝ ቅኔ ሊዘርፍ - ከዚች ዓለም ርቆ:: (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ጎሞራው ሄደ አሉ ሳይሰናበተን
“ለነሱማ…”
ለሕዝቦች አርነት — ላገርህ አንድነት፣ አርቀህ ማለምህ — አሕዛብን ማንቃትህ፣ “..ጠጣሩ እንዲላላ..” ምክር መለገስህ፣ “በረከት” አድርገህ “ርግማን” ማውረድህ..፣ አቤት! “ለነሱማ” እጅግ ማስፈራትህ! እነ-ኮሎኒያሊስት — ደግሞ እነ-እምፔሪያሊስት...፣ ያገርህ ደመኞች፟- ህሊና የለሾች፣ የሞራል፣ የባህል፣ የታሪክ አልቦዎች፣ አጠገብህ መቆም ከቶ ሲሳናቸው፣ እሚያረጉት ሲያጡ — ወኔ ሲከዳቸው፣ ሃቅን ስለሚሸሹ፟- መበለጥን ስለማይሹ፣ ምኑ ነው እሚደንቅህ? “ዕብድ” ነውስ ቢሉህ! ለኛ እንጂ ጥበብህ — ባለቅኔነትህ፣ የታሪክ፣ የባህል፣..መምህርነትህ፣ የፍትህ፣ ያንድነት.. ዓርማ ቤዛነትህ..፣ “ለነሱማ” አስፈሪ — ልክ-ልኩን ነጋር፣ ቆጥቋጭ የግር-እሳት — ቀሳፊ የጎን ውጋት፣ ሾተላይ ጸሐፊ — ታሪክ አሳላፊ...፤ ጌታቸው አበራ ኅዳር 2007 … [Read more...] about “ለነሱማ…”
ዓለም በቃኝ አለ!
ግጥሙን በPDF ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ:: … [Read more...] about ዓለም በቃኝ አለ!
የልጆቻችን ሀገር
አያቶቻችን የልጆቻችን መሬት ነች ብለው ደማቸውን አፍስሰው ሀገራችንን ከወራሪ ፋሽት ታደጉልን አባቶቻችን በውርስ እርስ በእርስ ሲጣሉ ሳይኖሩበት ሳያኖሩበት ይኸው አሉ ። ልጆች የሚሆነው ሳይገባቸው ውሉ የጠፋባቸውን አባቶቻቸው እያዩ ነው፤ ግራ መጋባታቸውን እየወረሱ ግራ እየተጋቡ ነው ፤ ወይ በሽሽት ላይ ናቸው፤ ነገር ግን እትብታቸው የተቀበረባትን ቀዬ ከማዶ ሆነው እያዪ የጨው አምድ ሆነው ቆመዋል፤ ብቻ ልቦቻቸው ያነባሉ። እንዲህ እያሉ:- የአያቶቻችን ቀዬ - የአባቶቻችን የጦር አውድማ፣ ለኛማ ህልም ብቻነች -ያልተጨበጠች ከተማ፤ ቆመንባት የምትፋጅ- ስንርቃት የምትናፍቅ፣ የሆነች -ነች የቅርብ ሩቅ፤ እንዳንተዋት ማረፊችን፣ እንዳይዛት ማን ፈቅዶልን?፣ አያስነካን - የማይጠግበው አባታችን፣ ብቻ እዛ ማዶ ተገትርን፣ እዚህም ከግለቱ ላይ ተጥደን ፣ ለልጆቻችን አስቀሩልን … [Read more...] about የልጆቻችን ሀገር
ጎተራው ወዴት ነው?¡
ሀገር በብረት ሲታጠር — ‘ግንቦት ሃያህ’ ሲከበር፤ አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር — ዘመን በዘመን ሲቀየር፤ የስራ-ፈቶች ስብስብ መንጋ — ‘ፓርላማህ‘ሲከፈት ሲዘጋ..፤ ሱፍህን ገጥግጠህ — ከረባትህን ጠፍረህ፣ ወዝህን አሳምረህ — ካሜራ ፊት ቀርበህ፣ ጉሮሮህን..ጠርገህ — ፊትህ የከመርከውን ‘ሃያ ገጽ’ ገልብጠህ፣ ቁጥር እየቆጠርክ፣ አሃዝ እየጠራህ...፣ “ምናምን..ሺ.ቶን፣ ሚሊዮን ስልቻ፣ አምርተን አስገባን በዚህ ዓመት ብቻ...”፣ እያልክ ስትደሰኩር — ትንፋሽህ እስኪያጥር፣ ሰምቼህ ሳበቃ፣ የግርምት ጥያቄ እስኪማ ልሰንዝር፤ በልበ-ሙሉነት “ጠግብን በላን” ያልከው፣ ሕዝቡን ቆጥረህ ይሆን? ወይስ የቤትህን ያንተኑ ግሳት ነው?! ስርህ ተግተርትሮ፣ ላብ እያሰመጠህ፣ ያቀረብከው ‘ሪፖርት‘ እንዲያ ተውረግርገህ፣ የራስህን በጀት፣ የጓዳህን ወሬ፣ ወይስ የምስኪኗን … [Read more...] about ጎተራው ወዴት ነው?¡




![“ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…”፤ [“የቲፎዞነት” ዘመን]](https://www.goolgule.com/wp-content/uploads/2014/12/Birds-300x277.gif)





