• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…”፤ [“የቲፎዞነት” ዘመን]

December 4, 2014 10:15 am by Editor Leave a Comment

እንዴት ሰነበታችሁሳ!

ሀሳብ አለን … ስብስባዎች ሁሉ … አለ አይደል… “እንዴት ሰነበታችሁ…” በሚል ብቻ ይከፈትና ወደ ጉዳዩ ይገባ! አሀ … “ክቡር እከሌ እከሌ፣” “ክብርት እከሊት እከሌ፣” “የተከበሩ እከሌ እከሌ” … ምናምን ሲባል የስብሰባው ሲሦ እያለቀ ነዋ! ለነገሩ … (“ለምን ይዋሻል!” የሚሉት ነገር ነበረ አይደል!) ብዙ ስብሰባዎች ላይ “እንትንህን እንደ ዳናኪል እንፋሎት እንዳላቦንልህ!” አይነት “የጉልበት ግማሹ ምላስ ነው…” ነገር በዝቷላ! (እኔ የምለው … አንዳንዱ መድረክ ላይ ወጥቶ እንዴት ነው እንዲህ ‘ልክ ልክ ማጠጣት’ የሚዋጣለት!)

አንድ ወዳጃችን ሲነግረን አለቅየው ‘መጠመቁን’ ለበላዮቹ ለማስመስከር የማይሞክረው ነገር የለም፡፡ በተለይ ስብሰባዎች ላይ የሚናገረው ‘ቦተሊካ’ ነክ ንግግር ካርል ማርክስን ጢሙንና ጸጉሩን አርግፎለት ‘አይ ሮቦት’ ነገር ያስመስለው ነበር፡፡ እናላችሁ…በቅርብ ጊዜ ሚጢጢና የሰማይ ስባሪ አለቆችና አለቆች ነገሮችን ይሰበስብና … “እዚህ ክፍል ውስጥ የግንዛቤ ችግር ያለባችሁ ሰዎች እንዳላችሁ ይታወቃል፡፡ የኒኦ ሊበራሊዝም አስተሳሰብ መሥሪያ ቤታችን ውስጥ እንዲገባ መፍቀድ የለብንም…” ምናምን እያለ እሱ ራሱ ባልገባው ነገር ግራ እንዳጋባቸው ሲነግረን ነበር፡፡ ወዳጃችን በሆዳችን ግን ሁላችንም ቂ…ቂ… ብለናል…” ብሎናል፡፡

እንግዲህ ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…ለነገሩ በሆዳችን ቂ…ቂ… የሚያሰኙ ነገሮች መአት ናቸው፡፡ ጮክ ብለን ቂ…ቂ…ብንል አበሳ ነው፣ ዝም እንዳንል  እንዴት አስችሎን — በሆድ እንኳን እንሳቅ እንጂ!

እኔ የምለው…እንግዲህ ጨዋታም አይደል…ይቺን ስሙኝማ፡፡ ሰውየው ንግግር እያደረገ ነው አሉ… እናላችሁ …ሦስት አራቱ አንድ ላይ በመናገር በየመሀሉ ያቋርጡታል፡፡ ብሽቅ ይላል፡፡ ተራ በተራ እንዲናገሩ ለማድረግም ምን ይላል… “ዛሬ እዚህ አዳራሽ ውስጥ ብዙ ደደቦች አሉ፡፡ በአንድ ጊዜ አንድ ደደብ ብቻ ቢናገር አይሻልም…” ይላል፡፡

ተሰብሳቢዎቹ ምን ቢሉት ጥሩ ነው  “…እኮ ቀጥላ!” አሪፍ አይደል! ዘንድሮ በየቦታው “…እኮ ቀጥላ!” መባል የሚገባንን ቤቱ ይቁጠረን፡፡

ስሙኝማ…“ክቡራንና ክቡራት፣ ደህና  ሁኑ፣ አትሁኑ የእኔ ጉዳይ አይደለም… ምን አግብቶኝ ነው እንደምን አደራችሁ የምለው? አሁን ወደ ስበሰባችን እንገባ፣” የሚል የክብር እንግዳ የመጣ ቀን… ያኔ የምር ዘመኑ እየገባን ነው ማለት ነው፡፡ እንደምን ብንውል ብናድር ማንም ግዴለውማ! አይደለም የእኛ ቤጤ የዓለም ሰዎችን ቀርቶ አባቶች እና ምዕመናን እንደምን አደራችሁ!… እንደምን ዋላችሁ!… እንደምን አመሻችሁ…” ሲለን እንኳን አንዳንዴ እንደው ግድ ሆኖባቸው ነው እንላለን፡፡

እኔ የምለው…አርቲስቶች (እና ‘ሴሌብሪቲዎች’…) ምናምን … አለ አይደል…በሬድዮ፣ በቲቪ ምናምን ሲቀርቡ… “እወዳችኋለሁ…” የሚሏት ነገር አሁን፣ አሁን ቂ…ቂ…ቂ… ታሰኘን ጀምራለች፡፡ ልክ ነዋ… ከዘመድ፣ አዝማድ ጋር ሁሉ ተጠማምዶ “ሸንኮራ ጠበል ቢጠመቅ ይሻላል ወይስ አርሴማ ገዳም ቢገባ…” እየተባለ ምክክር እየተደረገበት… እኛን “እወዳችኋለሁ…” ሲለን አሪፍ አይደለም፡፡ እኔ የምለው…እግረ መንገዴን የሆነ ነገር ትዝ አለኝማ…አሁን አንድ አንድ ‘ቶክ ሾው’ ምናምን የሚባሉ ዝግጅቶች ላይ እየተለመደች የመጣች አባባል አለች፡፡ “እንዲህ ያሳመረኝ እንትን እንትን ቡቲክ ነው…” አይነት ነገር ይባላል፡፡ ደስ የሚል ዘመን ነው፡፡ ድሮ አፍ አውጥቶ “አምራለሁ…” ቢል የሰፈር ዕድር ሁሉ ባያድምበት ነው! ሀሳብ አለን…አንዳንድ ጊዜ… አለ አይደል… “ይህን የሚያምር ልብስ ያለበሰኝ…” ይባልልንማ! አሀ…እንደዛ ስናስብስ!  ቂ…ቂ…ቂ…

ስሙኝማ…ጨዋታን ጨዋታ ያነሳው የለ…ዘንድሮ የ‘ቲፎዞ ነገር’ አልበዛባችሁም! የምር አስቸጋሪ ነው…ጥሩ ነገር መሥራት ብቻውን በቂ ያልሆነበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡ “ስማ እንትን ኤፍ ኤም የምታውቀው ሰው የለህም!” መባባል ለመደብን፡፡ ምን ይደረግ!…‘ቲፎዞ’ ከሌለን ነገርዬው…አለ አይደል…“ከሌለህ የለህም…” አይነት ይሆናል፡፡

እናላችሁ…አሪፍ መጽሐፍ መጻፍ ብቻ፣ አሪፍ ዘፈን መዝፈን ብቻ፣ ብዙ የግጥም መድበል ማውጣት ብቻ፣ ጥሩ መተወን ብቻ ወዘተ. በቂ አይሆንም፡፡ በምላሳቸው “ወንድምና እህትን ማጋባት ይቻላል…” የሚባሉ አይነት ‘ሎቢይስቶች’ ያስፈልጋሉ፡፡

የምር ግን…አንዳንድ ሥራዎች ቆይተርው እናንተ ዘንድ ይደርሱና… አለ አይደል… “ይሄን ነገር እንዴት እስከ ዛሬ ድረስ አላየሁትም…” አይነት ነገር ትላላችሁ፡፡ መልሱ አጭር ነው… ‘ኖንቼ ቲፎዞ!’

ስሙኝማ… ብዙ ሠርግ ምናምን ላይ አይታችሁልኛል…ጠጁ ምናምኑ በ‘መሬት በታች መተላለፊያዎች’ (ቂ…ቂ…ቂ….) የሚሄደው ወደሚታወቁ ሰዎች፣ ወደ ሰፈር ሰዎች፣ ወደ መሥሪያ ቤት ባልደረቦች፡ ምናምን ነው፡፡ ዘመኑ የ‘ቲፎዞ’ ነዋ!

ደግሞላችሁ…አንዳንድ ቦታ የደረጃም ሆነ የደሞዝ እድገት የሚገኘውም በ‘ቲፎዞ’ ነው ይባላል፡፡ ዘንድሮ ደግሞ ለ‘ቲፎዞነት’ የሚያመቹ መመዘኛዎች በዝተዋል፡፡ ከሁሉ በላይ ግን ‘የአገር ልጅነት’ ዋናው ነው፡፡ እኔ እኮ አንዳንዶቹማ ከሰፊው ‘የአገር ልጅነት’ ወደ ሰፈርነት ሲወርዱ ስታዩ ነገ ደግሞ ‘በግቢ’ እንዳይሆን ትላላችሁ፡፡

ስሙኝማ…ዘንድሮ መንደሮች ‘መደብ’ የሚለይባቸው እየሆኑ አይደል… እዛም ለየት ያሉ ‘ቲፎዞነቶች’ ይኖራሉ ማለት ነው፡፡ ለመደብና! “ዘመድ ከዘመዱ…” ምናምን የሚባል ነገረ አለ አይደል፡፡ ይቺን ስሙኝማ… ሰውየው አንዱን ጎብኚ እያዟዟረ ኒው ዮርክን ያስጎበኘው ነበር፡፡ እናላችሁ… አንድ ቤተ መንግሥት የሚያክል መኖሪያ ቤት ይደርሳሉ፡፡

አስጎብኚውም እንዲህ ይላል… “ይህ በኒው ዮርክ እጅግ ሀብታም የሆነው ሰው መኖሪያ ቤት ነው፡፡ አብሳዩ ጀርመናዊት ነች፣ የቤት ሠራተኛዋ ፈረንሳዊት ነች፣ ዕቃ አመላላሹ ጃፓናዊ ነው፣ ሜካኒኩ ስኮትላንዳዊ ነው፣ የቤት ጽዳት ሠራተኛዋ ስዊድናዊት ነች፣  ፀሀፊው ደግሞ አሜሪካዊት ነች፡፡”ጎብኚው ሲመልስ ምን አለ መሰላችሁ… “ይሀ መኖሪያ ቤት ሳይሆን የዓለም ፍርድ ቤት ነው፡፡” ኧረ እዚህ በመጣ፣ ቤተ መንግሥት ሊያስንቁ ምንም የማይቀራቸው ቤቶች ባይኖሩ ነው! እንደውም አንዳንዶቹ እንዲህ አይነት ቤቶች ባሉባቸው አካባቢዎች ሲያልፉ የመኪና ጥሩምባ ማሰማት ክልክል እንደሆነ በቀደም ወዳጄ እየነገረኝ ነበር፡፡ “ገና ምን አይተሽ!” አለ ባል ሚስት ላይ ሲፎክር!

እኔ የምለው…እግረ መንገዴን…ደግሞ የት አካባቢ ነው…“ከጥራት በታች የተሠራ መንገድ እየፈረሰ ነው…” ምናምን ሲባል ሰማን ልበል! …‘ማፍረስ’ ቀላል የሆነባት አገር! ሀሳብ አለን… ለማፍረስ ጥቅም ላይ የሚውሉ ዲጂኖ ምናምን አይነት መሣሪያዎች ከውጪ ይገቡ እንደሆነም፣ እዚሁ ይመረቱ እንደሆነም ብዛታቸው ይቀነስልንማ! አሀ…ችግር የሚፈጥርው እኮ ‘እንደ ልብ’ የሚገኝ ነገር ነው፡፡ ለነገሩ ዲጂኖውም ቢጠፋ… አለ አይደል… “በጥፍሬ እየቧጠጥሁ ካላፈረስኵ ሞቼ እገኛለሁ…” የምንል አንጠፋም፡፡ ዘመኑ እንዲህ ነዋ!

እናላችሁ… ‘የቲፎዞነት’ ዘመን ነው፡፡ እኛ “የለም…” የተባልነው የለስላሳ መጠጥ አይነት እዛው በዛው ለ‘ቲፎዞ’ ሲሰጥ ያየንበት ሬስቶራንት ነገር አለ፡፡

ታዲያላችሁ…በየስብሰባውም የሚገጥማችሁ ነገር ‘የቲፎዞ’ ነገር ነው፡፡ ያው ያቺ ከድሮ ጀምሮ የተለመደች ‘በተንተን ብሎ የመቀመጥ’ ስትራቴጂ አለች አይደል… ሰበሳቢውም “አንድ ከዚህ ጫፍ፣ አንድ ከመሀል፣ አንድ ከወዲያኛው ጫፍ…” ምናምን ይልና ስትራቴጂያዊ ቦታቸውን የያዙ ‘የቲፎዞ ስብስቦች’ ….ይቆጣጠሩታል፡፡

እናላችሁ… ሰዉ ከሁሉ አስቀድሞ “እንትን መሥሪያ ቤት ሰው ታውቃለህ…” ምናምን የሚባለው ዘመኑ ‘የቲፎዞ’ ስለሆነ ነው፡፡

አሁን፣ አሁን የሆነ ነገር፣ በተለይ የጥበብ ሥራ፣ ሲያደንቁልን ከሥራው ይልቅ “ሰውዬዋ ፕሮፓጋንዳ እየነሰነሰች ነው እንዴ!” እንላለን፡፡

እናማ… “ሙሽራን ያላችሁ እስቲ እንያችሁ…” አይነት የመጠቃቀስ፣ በምስጢር የመጠራራት ‘ቲፎዞነት’… አለ አይደል… ‘በጨው ደንደስ በርበሬውን እያስወደሰ’ ስለሆነ ጦሳችንን ይዞ ይሂድልንማ!

ደህና ሰንብቱልኝማ!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule