• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ጎተራው ወዴት ነው?¡

November 4, 2014 05:29 pm by Editor Leave a Comment

ሀገር በብረት ሲታጠር — ‘ግንቦት ሃያህ’ ሲከበር፤
አዲስ ዓመት በመጣ ቁጥር — ዘመን በዘመን ሲቀየር፤
የስራ-ፈቶች ስብስብ መንጋ — ‘ፓርላማህ‘ሲከፈት ሲዘጋ..፤
ሱፍህን ገጥግጠህ — ከረባትህን ጠፍረህ፣
ወዝህን አሳምረህ — ካሜራ ፊት ቀርበህ፣
ጉሮሮህን..ጠርገህ — ፊትህ የከመርከውን ‘ሃያ ገጽ’ ገልብጠህ፣
ቁጥር እየቆጠርክ፣ አሃዝ እየጠራህ…፣
“ምናምን..ሺ.ቶን፣ ሚሊዮን ስልቻ፣
አምርተን አስገባን በዚህ ዓመት ብቻ…”፣
እያልክ ስትደሰኩር — ትንፋሽህ እስኪያጥር፣
ሰምቼህ ሳበቃ፣ የግርምት ጥያቄ እስኪማ ልሰንዝር፤
በልበ-ሙሉነት “ጠግብን በላን” ያልከው፣
ሕዝቡን ቆጥረህ ይሆን? ወይስ የቤትህን ያንተኑ ግሳት ነው?!

ስርህ ተግተርትሮ፣ ላብ እያሰመጠህ፣
ያቀረብከው ‘ሪፖርት‘ እንዲያ ተውረግርገህ፣
የራስህን በጀት፣ የጓዳህን ወሬ፣
ወይስ የምስኪኗን ኢትዮጵያ ሀገሬ?
እኮ ታዲያ የታል? የተትረፈረፈው፣
የእህል ዘር፣ የእህል ምርት..የት የተከተተው?
እባክህ ንገረን ጎተራው ወዴት ነው?!
እንደልቡ አፍሶ ሕዝብ የሚጠግብበት፣
የተትረፈረፈው…የተከማቸበት፣
ንጉስ አብዱላህ አገር ከሳዑዲ አረቢያ?
ከ’ካራቱሪ’ አገር ወይስ ከኢንዲያ?
ወይስ ከ’ሸራተን’ ከ’ሚድሮክ’ መጋዘን?
የት ይሆን ጎተራው? በነካካ አፍህ ጨክነህ ብትነግረን¡
አገር ያለውማ ሕዝቡን እሚያከብር፣
የራሱ አልበቃው ሲል ለመጥገብ ሲቸገር፣
ከሞኝ ደጃፍ ወርዶ፣ ሸጋ ሞፈር ቆርጦ፣
ባላድ፣ በስሙኒ..ጋሻ መሬት ገዝቶ፣
ያገር ደን መንጥሮ — የሰው-ሰው አባሮ፣
መሬት አለስልሶ፣ ውሃ ቦዩን ጠልፎ፣
ቀለቡን ይሰፍራል፤ ምርቱን አትረፍርፎ፤
እሱ ነው እሚያምርበት!
አደባባይ ቆሞ ለሕዝብ ቢያቀርብ ‘ሪፖርት’።
እንጂማ አንተማ፣ ክፋት-ምቀኝነት…
መቅኔህ ድረስ ዘልቆ፣ አጥንትህን ቦርቡሮ፣
መላ ሰውነትህ በጥላቻ-በእልህ..በቅንቅን ተወሮ፣
በዚያቹ በምስኪን ባዶ ጎጆው ቀንተህ፣
ያያት-ቅድማያቱን ርስት ቀዬ ነጥቀህ፣
በባዶ አንጀቱ በጥይት ቀጥቅጠህ፣
አገርህን ንቀህ፣ ወገንህን ጠልተህ፣
በ’ፌደራል ፖሊስ‘ ለባዕድ ዘብ ቆመህ..፣

ካሜራ ፊት ቀርበህ አረፋ እየደፈቅህ፣ “ጠግበን በላን” ያልከው፣
ምጸት ነው! ምጸት ነው! ለምስኪን ያገር ልጅ ሁለተኛ ሞት ነው!!

ጌታቸው አበራ
ጥቅምት 2007 ዓ/ም (ኦክቶበር 2014)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule