• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ለነሱማ…”

November 16, 2014 05:06 pm by Editor Leave a Comment

ለሕዝቦች አርነት — ላገርህ አንድነት፣
አርቀህ ማለምህ — አሕዛብን ማንቃትህ፣
“..ጠጣሩ እንዲላላ..” ምክር መለገስህ፣
“በረከት” አድርገህ “ርግማን” ማውረድህ..፣
አቤት! “ለነሱማ” እጅግ ማስፈራትህ!

እነ-ኮሎኒያሊስት — ደግሞ እነ-እምፔሪያሊስት…፣
ያገርህ ደመኞች፟- ህሊና የለሾች፣
የሞራል፣ የባህል፣ የታሪክ አልቦዎች፣
አጠገብህ መቆም ከቶ ሲሳናቸው፣
እሚያረጉት ሲያጡ — ወኔ ሲከዳቸው፣
ሃቅን ስለሚሸሹ፟- መበለጥን ስለማይሹ፣
ምኑ ነው እሚደንቅህ? “ዕብድ” ነውስ ቢሉህ!

ለኛ እንጂ ጥበብህ — ባለቅኔነትህ፣
የታሪክ፣ የባህል፣..መምህርነትህ፣
የፍትህ፣ ያንድነት.. ዓርማ ቤዛነትህ..፣
“ለነሱማ” አስፈሪ — ልክ-ልኩን ነጋር፣
ቆጥቋጭ የግር-እሳት — ቀሳፊ የጎን ውጋት፣
ሾተላይ ጸሐፊ — ታሪክ አሳላፊ…፤

ጌታቸው አበራ
ኅዳር 2007 ዓ/ም
(ኖቬምበር 2014)

ይህቺ ግጥም የተጫረችው የዛሬ 15 ዓመት ገደማ ነው። በወቅቱ በጀርመን አገር እየታተመች ትወጣ በነበረች “ራዕይ” በምትሰኝ መጽሔት ላይ፣ ጉምቱው ደራሲና ገጣሚ ጋሼ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው)በተከታታይ እጅግ አስደናቂ የሆነ ቃለ-ምልልስ አድርጎ በነበረበት ወቅት፣ ስላለበት አገር ኑሮ ሲጠየቅ የመንግስት አካላት ሳይቀሩ በኑሮው ላይ ጣልቃ እንደሚገቡና እንዲያውም “ዕብድ ነህ ይሉኛል” ብሎ ስለነበር፣ አንጀቴን በልቶት፣ “ለነሱማ ዕብድ ነህ” በሚል ርዕስ የጻፍኳት ነበረች። የግጥሟን ቅጂ በወቅቱ ለጋሼ ኃይሉ መላኬን አስታውሳለሁ።

ሌላ የማስታውሰውን አንድ ልጨምር፤ በምን ምክንያት እንደሆነ በውል ባላውቅም፣ ጋሼ ኃይሉ (ገሞራው)በስደት የሚኖርበት የስዊድን መንግሥት ባንድ ወቅት እንደ ቁም-እስረኛ አርጎት በነበረበት ወቅት፣ በሆላንድ የኢትዮጵያውያን ማኅበር የወቅቱ ሊቀ- መንበር የነበረው ግርማ አያሌው፣ የእውቁ ደራሲያችን ከቦታ ወደ ቦታ የመዘዋወር መብት እንዲከበር የሚጠይቅ ደብዳቤ በማኅበሩ ስም ለስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጻፍ፣ ደራሲያችን ወገን እንዳለው ከማስመስከሩም በላይ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለማኅበሩ የሰጠውን የደብዳቤ ምላሽ እንዳሳየኝ አስታውሳለሁ።

ጋሼ ኃይሉ፣ በችግርና በመከራ ሲከራተት ቢኖርምና በጣም የሚሳሳላትንና የሚወዳትን እናት አገሩን ዳግም ሳያይ ቢቀርም፣ ለምንም ሳይበገር ታላላቅ የጥበብ ስራዎቹን ለታሪክና ለትውልድ በህያውነት ከትቦና አስረክቦ አልፏል። የመኖርን ትርጉም በአርዓያነት ለማውረስ በብርቱ ጥሯል።

ጋሼ ኃይሉ!መልካም ዘልዓለማዊ ዕረፍት !!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule