• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ለነሱማ…”

November 16, 2014 05:06 pm by Editor Leave a Comment

ለሕዝቦች አርነት — ላገርህ አንድነት፣
አርቀህ ማለምህ — አሕዛብን ማንቃትህ፣
“..ጠጣሩ እንዲላላ..” ምክር መለገስህ፣
“በረከት” አድርገህ “ርግማን” ማውረድህ..፣
አቤት! “ለነሱማ” እጅግ ማስፈራትህ!

እነ-ኮሎኒያሊስት — ደግሞ እነ-እምፔሪያሊስት…፣
ያገርህ ደመኞች፟- ህሊና የለሾች፣
የሞራል፣ የባህል፣ የታሪክ አልቦዎች፣
አጠገብህ መቆም ከቶ ሲሳናቸው፣
እሚያረጉት ሲያጡ — ወኔ ሲከዳቸው፣
ሃቅን ስለሚሸሹ፟- መበለጥን ስለማይሹ፣
ምኑ ነው እሚደንቅህ? “ዕብድ” ነውስ ቢሉህ!

ለኛ እንጂ ጥበብህ — ባለቅኔነትህ፣
የታሪክ፣ የባህል፣..መምህርነትህ፣
የፍትህ፣ ያንድነት.. ዓርማ ቤዛነትህ..፣
“ለነሱማ” አስፈሪ — ልክ-ልኩን ነጋር፣
ቆጥቋጭ የግር-እሳት — ቀሳፊ የጎን ውጋት፣
ሾተላይ ጸሐፊ — ታሪክ አሳላፊ…፤

ጌታቸው አበራ
ኅዳር 2007 ዓ/ም
(ኖቬምበር 2014)

ይህቺ ግጥም የተጫረችው የዛሬ 15 ዓመት ገደማ ነው። በወቅቱ በጀርመን አገር እየታተመች ትወጣ በነበረች “ራዕይ” በምትሰኝ መጽሔት ላይ፣ ጉምቱው ደራሲና ገጣሚ ጋሼ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው)በተከታታይ እጅግ አስደናቂ የሆነ ቃለ-ምልልስ አድርጎ በነበረበት ወቅት፣ ስላለበት አገር ኑሮ ሲጠየቅ የመንግስት አካላት ሳይቀሩ በኑሮው ላይ ጣልቃ እንደሚገቡና እንዲያውም “ዕብድ ነህ ይሉኛል” ብሎ ስለነበር፣ አንጀቴን በልቶት፣ “ለነሱማ ዕብድ ነህ” በሚል ርዕስ የጻፍኳት ነበረች። የግጥሟን ቅጂ በወቅቱ ለጋሼ ኃይሉ መላኬን አስታውሳለሁ።

ሌላ የማስታውሰውን አንድ ልጨምር፤ በምን ምክንያት እንደሆነ በውል ባላውቅም፣ ጋሼ ኃይሉ (ገሞራው)በስደት የሚኖርበት የስዊድን መንግሥት ባንድ ወቅት እንደ ቁም-እስረኛ አርጎት በነበረበት ወቅት፣ በሆላንድ የኢትዮጵያውያን ማኅበር የወቅቱ ሊቀ- መንበር የነበረው ግርማ አያሌው፣ የእውቁ ደራሲያችን ከቦታ ወደ ቦታ የመዘዋወር መብት እንዲከበር የሚጠይቅ ደብዳቤ በማኅበሩ ስም ለስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጻፍ፣ ደራሲያችን ወገን እንዳለው ከማስመስከሩም በላይ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለማኅበሩ የሰጠውን የደብዳቤ ምላሽ እንዳሳየኝ አስታውሳለሁ።

ጋሼ ኃይሉ፣ በችግርና በመከራ ሲከራተት ቢኖርምና በጣም የሚሳሳላትንና የሚወዳትን እናት አገሩን ዳግም ሳያይ ቢቀርም፣ ለምንም ሳይበገር ታላላቅ የጥበብ ስራዎቹን ለታሪክና ለትውልድ በህያውነት ከትቦና አስረክቦ አልፏል። የመኖርን ትርጉም በአርዓያነት ለማውረስ በብርቱ ጥሯል።

ጋሼ ኃይሉ!መልካም ዘልዓለማዊ ዕረፍት !!

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
Copyright © 2026 · Goolgule