• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ለነሱማ…”

November 16, 2014 05:06 pm by Editor Leave a Comment

ለሕዝቦች አርነት — ላገርህ አንድነት፣
አርቀህ ማለምህ — አሕዛብን ማንቃትህ፣
“..ጠጣሩ እንዲላላ..” ምክር መለገስህ፣
“በረከት” አድርገህ “ርግማን” ማውረድህ..፣
አቤት! “ለነሱማ” እጅግ ማስፈራትህ!

እነ-ኮሎኒያሊስት — ደግሞ እነ-እምፔሪያሊስት…፣
ያገርህ ደመኞች፟- ህሊና የለሾች፣
የሞራል፣ የባህል፣ የታሪክ አልቦዎች፣
አጠገብህ መቆም ከቶ ሲሳናቸው፣
እሚያረጉት ሲያጡ — ወኔ ሲከዳቸው፣
ሃቅን ስለሚሸሹ፟- መበለጥን ስለማይሹ፣
ምኑ ነው እሚደንቅህ? “ዕብድ” ነውስ ቢሉህ!

ለኛ እንጂ ጥበብህ — ባለቅኔነትህ፣
የታሪክ፣ የባህል፣..መምህርነትህ፣
የፍትህ፣ ያንድነት.. ዓርማ ቤዛነትህ..፣
“ለነሱማ” አስፈሪ — ልክ-ልኩን ነጋር፣
ቆጥቋጭ የግር-እሳት — ቀሳፊ የጎን ውጋት፣
ሾተላይ ጸሐፊ — ታሪክ አሳላፊ…፤

ጌታቸው አበራ
ኅዳር 2007 ዓ/ም
(ኖቬምበር 2014)

ይህቺ ግጥም የተጫረችው የዛሬ 15 ዓመት ገደማ ነው። በወቅቱ በጀርመን አገር እየታተመች ትወጣ በነበረች “ራዕይ” በምትሰኝ መጽሔት ላይ፣ ጉምቱው ደራሲና ገጣሚ ጋሼ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው)በተከታታይ እጅግ አስደናቂ የሆነ ቃለ-ምልልስ አድርጎ በነበረበት ወቅት፣ ስላለበት አገር ኑሮ ሲጠየቅ የመንግስት አካላት ሳይቀሩ በኑሮው ላይ ጣልቃ እንደሚገቡና እንዲያውም “ዕብድ ነህ ይሉኛል” ብሎ ስለነበር፣ አንጀቴን በልቶት፣ “ለነሱማ ዕብድ ነህ” በሚል ርዕስ የጻፍኳት ነበረች። የግጥሟን ቅጂ በወቅቱ ለጋሼ ኃይሉ መላኬን አስታውሳለሁ።

ሌላ የማስታውሰውን አንድ ልጨምር፤ በምን ምክንያት እንደሆነ በውል ባላውቅም፣ ጋሼ ኃይሉ (ገሞራው)በስደት የሚኖርበት የስዊድን መንግሥት ባንድ ወቅት እንደ ቁም-እስረኛ አርጎት በነበረበት ወቅት፣ በሆላንድ የኢትዮጵያውያን ማኅበር የወቅቱ ሊቀ- መንበር የነበረው ግርማ አያሌው፣ የእውቁ ደራሲያችን ከቦታ ወደ ቦታ የመዘዋወር መብት እንዲከበር የሚጠይቅ ደብዳቤ በማኅበሩ ስም ለስዊድን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመጻፍ፣ ደራሲያችን ወገን እንዳለው ከማስመስከሩም በላይ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለማኅበሩ የሰጠውን የደብዳቤ ምላሽ እንዳሳየኝ አስታውሳለሁ።

ጋሼ ኃይሉ፣ በችግርና በመከራ ሲከራተት ቢኖርምና በጣም የሚሳሳላትንና የሚወዳትን እናት አገሩን ዳግም ሳያይ ቢቀርም፣ ለምንም ሳይበገር ታላላቅ የጥበብ ስራዎቹን ለታሪክና ለትውልድ በህያውነት ከትቦና አስረክቦ አልፏል። የመኖርን ትርጉም በአርዓያነት ለማውረስ በብርቱ ጥሯል።

ጋሼ ኃይሉ!መልካም ዘልዓለማዊ ዕረፍት !!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule