ዛሬ ጊዜ መቼም ሳጥን የሚወዱ ዓይነታቸው ብዙ ነው። አንድ ዓይነት ሁሉንም የሚያደርጋቸው ግን አንድ ጉዳይ አለ። ሳጥን ውስጥ መቅረት ስለሚፈልጉ፣ ሁሉም ከኔ ወዲያ ባዮች መሆናቸው ነው። እስቲ አማርኛችንም ወደ ሳጥን (1 ከመላኩ በፊት፣ የለም እንዳውም እንዳይላክ ስንል እንናገርበት፥ * ከኔ ወዲያ ነጋ ጠባ እኔ ማለት ትልቅ ምንጩ ፍርሃት ሆኖ እኮ ነው ብቸኝነት፤ የሚ-ኖረው ለጥፋት፣ በጥፋት፤ በድክመት፣ ያለምነት፤ ላይቀር ሞት። ከኔ ወዲያ ማ-ይሙት እየማለ ሲገዘት ምኑን አወቆ ስለ መብት፤ ግማሽ ጽዋው የሚ-ሞላው መች ባወቀው ይኸኛው፣ ለመሆኑ በዛ ማዶው በ-ዚያ ሌ-ላው። መች አ-ርቆ አሰበው፣ ከኔ ባዩ የጎደለው ግማሽ ጎኑ አምላኩ ነው፤ ባምባው ብቻ የማይገነው፤ ከኔ ወዲያ የማ-ይለው፣ በሁሉም ቤት … [Read more...] about ከኔ ወዲያ
Opinions
የኔ ሃሳብ
A Short Note on Ethiopian Political Change in Systemic Thinking
Social relations and the nature of conflict in a community (family, community or state etc.) are, according to Alexander Wendt, characterized by the sense of perception as enemies (Hobbesian), rivals (Lockean) & friends (Kantian). But I would add "the other", which has to be utterly "new" or should look like substantially different from the perspective of all the formers. I.e. it, the subject in the social dynamics looks like neither an enemy nor a rival or a friend. There lies the wisdom … [Read more...] about A Short Note on Ethiopian Political Change in Systemic Thinking
Ethiopia: another false prophet from the north?
Is it Abune Matias or Abune Samuel? “The church is Noah’s ark and he who is not found in it shall perish when the flood overwhelms all…” (The Cappadocia fathers, 376 AD) (Read More) … [Read more...] about Ethiopia: another false prophet from the north?
ህወሃት ሊወድቅ ነው
ገዢው ፓርቲ ለጥገናዊ ለውጥ ምንም አይነት ቦታ የማይሰጥ መሆኑን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ጉዳይ አስምረውበታል። ከዚህ የተነሳ ከገዢው ፓርቲ ጋር የነበረው የምርጫ ትግል በአጠቃለይ መክኗል። ዛሬ አገራችን ሙሉ በሙሉ ወደ ነጻነት ትግል ምዕራፍ ገብታለች። ፓለቲካ አይነት ፡ አይነት አለው። የምርጫ ፓለቲካ እና የነጻነት ፓለቲካ አንድ አይደሉም። የምርጫ ፓለቲካ ንጹህ ነው ፡ ጭምት ነው። የነጻነት ፓለቲካ ግን ይጨክናል ፡ ይቆሽሻል። የአገራችን ዘመናዊ የፓለቲካ ታሪክ ሲቃኝ በተደጋጋሚ የሚታየው ፡ ባለፉት 40 ዓመታት አብይ ለውጥ አራማጆች ከየዋህነታቸው እና ከንጹህ የፓለቲካ ስልታቸው የተነሳ ለአገራቸው የነበራቸው ራዕይ ተጨናግፏል ፡ መክኗል ፤ ኢትዮጵያ ያፈራቻቸው ብዙ ታላላቅ ሊሂቃኖቻችንም በከንቱ ጠፍተዋል። ካለፉት ያልተሳኩ የነጻነት ሙከራዎች … [Read more...] about ህወሃት ሊወድቅ ነው
“አህያውን ፈርቶ ዳውላውን!”
ኢትዮጵያን ዛሬ ማን ነው የሚያስተዳድራት ? ኢህአዴግ በአሜሪካና በምእራብ አውሮፓ፣ አንድ ምሁር እንዳሉት፣ በሚተነፍሰው ኦክሲጂን ካልተደገፈ አንድ ቀን ኣያድርም። ግፋ ቢል የቻይና ጉያ ውስጥ ገብቶ ይለይለታል። ያኔ ደግሞ ቻይናን የማይወዷት እዚሁ አካባቢ ጉድ ጉድ ማለታቸው አይቀርም! ይህ ሆኖ ሳለ ፣ በተለይ ከውጭ ሆነው ኢህአዴግን የሚታገሉት የፖለቲካ ሃይሎች ዋናው ትግላቸው ፣ ኢህአዴግን በህይወት የሚያቆዩት እነዚህ ሃይሎች ላይ ለምን እንደማያቶኩር በመገረም የተፈለገ ምሳሌ ነው። “አህያውን ፈርቶ ዳውላውን!” እንዳው ለምሳሌ ያህል፣ ሰሞኑን ካራቱሪ የሚባለውን በሃገራችን መሬት ከተስፋፉት የባእድ ባለጸጎች ውስጥ አንዱ፣ የሚፈጽመውን በደል ለማጋለጥ የማደንቀው የነጻነት ታጋይ ኦባንግ ሜቶ ይህ እንዴት እንደሚደረግ፣ አሳይቶናል። ውጤት የሚሰጥ የዚህ ዓይነት የማያቋርጥ ዘመቻ … [Read more...] about “አህያውን ፈርቶ ዳውላውን!”
መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል
በአለፉት ሠላሳ አምስት ዓመታት ኢትዮጵያ ችግሮችን መፈልፈያ መሣሪያ ሆናለች፤ ለብዙ ምዕተ-ዓመታት ይዘናቸው (ምናልባትም አቅፈናቸው ማለት ይሻል ይሆናል) ስንንከባለል የቆዩ ችግሮች ሞልተውናል፤ እያሰብን እነዚያን የቆዩ ችግሮቻችንን በመፍታት ፋንታ ሌሎች አዳዲስ ችግሮችን እየፈለፈልን የተቆላለፉና የተወሳሰቡ፣ ውላቸው የጠፋ ችግሮችን ፈጥረናል፤ እየፈጠርንም ነው፤ አሁን በመፈጠር ላይ ያለው አዲስ ችግር እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ የሚል ነው፤ እስቲ እንመልከተው፡፡ (Photo: mesfinwoldemariam.wordpress.com) በሩቁ እንጀምር፤ እስላማዊ መንግሥታት ያቋቋሙ አገሮች አሉ፤ አንዳቸውም ሰላም የላቸውም፤ እስላማዊ ቡድኖች በምርጫ አሸንፈው ሥልጣን የያዙ አሉ፤ ለምሳሌ በቅርቡ በአረብ አገሮች በተጀመረው የፖሊቲካ እድገት ለውጥ በቱኒስያና በግብጽ እስላማዊ ቡድኖች … [Read more...] about መርዝ ከውጭ ይረጫል ወይም ከውስጥ ይመነጫል
“ጭንጋፍ (ምቱር) ፓትርያርክ”
የካቲት ፳፩ ስለሚወለደው ፓትርያርክ ስናስብ ከአቡነ ጳውሎስ የተለየ ሆኖ እናገኘዋለን። አቡነ ጳውሎስን ይህ መንግስት ከሜዳ አግኝቶ በማደጎ አሳደጋቸው እንጅ ጸንሶ የወለዳቸው አይመስሉም። ይህን ለማለት ያስገደደኝ፤ እርቁ እንዲጀመር በፈቀዱት በአቡነ ጳውሎስ ላይ አቶ ስብሀት ነጋ “እርቁ እንዲጀመር በመስማማታቸው ተሳስተዋል” ብለው በወረወሩባቸው ትችት እራሱ የወያኔ መንግስት አቡነ ጳውሎስን የጉዲፈቻ ልጅ አድርጓቸዋል። የኢ.ህ.ዴ.ግ. ልጅ መስለው የተገኙት በቦታው ከተሰየሙ በኋላ ነውና ማደጎ ነበሩ ማለት ነው። ይህ ዛሬ ሊወለድ ነው ተብሎ የተነገረን ፓትርያርክ ከአቡነ ጳውሎስ ለየት ያለ ኢ.ህ.ዴ.ግ.ን በጫካ በነበረበት ጊዜ በአካሉ በሥጋውና በነፍሱ አስመሎ ይወልደው ዘነድ የጸነሰ ነው። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል) … [Read more...] about “ጭንጋፍ (ምቱር) ፓትርያርክ”
Ethiopia: Family and friends of hero lawyer worry about his safety
Although it is widely condemned and denounced across the political spectrum, since the minority Tigre junta aired the hateful diatribe titled Jihadawi Harekat against a religion called Islam, which was seen by millions as an open declaration of war on the children of Billal, Ethiopians are worried about the safety of some prominent Muslims such as the much loved young lawyer Temam Ababulga (pictured). (Read more) … [Read more...] about Ethiopia: Family and friends of hero lawyer worry about his safety
በጂሃድ ሃረካት ፊልም ላይ ከ33ቱ ፔቲሺን ፈራሚዎች የተሰጠ መግለጫ
ንብረትነቱ የሕዝብ ቢሆንም አገልግሎቱ የኢህአዴግ የፕሮፓጋንዳ መሣሪያ የሆነው ኢቲቪ በሰሞኑ የፍርድ ቤት ዕግድ ወደጎን በመግፋት ከተለያዩ ፊልሞች በመቀነጫጨብ ‹‹ጂሃዳዊ ሃረካት›› በማለት ጉዳያቸው በፍርድቤት እየታየ ባለው በእሥር ላይ የሚገኙት የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ያነጣጠረ ፊልም በተደጋጋሚ አሰራጭቶ ተከታትለናል፡፡ (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ) … [Read more...] about በጂሃድ ሃረካት ፊልም ላይ ከ33ቱ ፔቲሺን ፈራሚዎች የተሰጠ መግለጫ
የኦርቶዶክሱ “ክሩሴድ”/ “Crusade” የሚባል መርዝስ መች ይሆን የሚረጨው?
በታላቁ ኢትዮጵያዊያችን አንደበት፣ ኢትዮጵያ ዛሬም ያለችበትን ከፍተኛ የሕልውና አደጋን ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ያገናዝብ! እንደ ግራዝያኑ፣ ማለትም ያቃጣል! የዛሬው የኢትየጵያ መንግሥት ርሕራሄ የሌለውን በትሩን ያነሳው የተቃዋሚ የፖለቲካ ተቀናቃኞቹ ብቻ ላይ ሳይሆን፣ ሃይማኖት ኃይል ፖለቲካ፣ ለሰብዓዊ መብታቸው የቆሙ ሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ ነው። ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር የቆየ ዕምነታቸውን ይዘው፣ ለሃይማኖት መብታቸው የሚሟገቱ ሙስሊም ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሆኑ፣ ከኢትዮጵያ ታሪክ ጋር የተያያዘው የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ምዕመናኖችም ጭምር ነው። ትላንት /05.02.13/ ጀሃዳዊ ሃረካት በሚል ስም ሃገር፣ ህግና ወገን የሚያሰድብ፣ የሚያሳፍር፣ ለዘመናት ተቻችለው የኖሩትን ትላልቅ ሃይማኖቶችን ለማጋጨት የቅስቀሳ መርዙን በረጨ ማግስት፣ ዛሬ /13.02.13/ ደግሞ ከያን ሰሞን ሳይታሰሩ … [Read more...] about የኦርቶዶክሱ “ክሩሴድ”/ “Crusade” የሚባል መርዝስ መች ይሆን የሚረጨው?










