
የካቲት ፳፩ ስለሚወለደው ፓትርያርክ ስናስብ ከአቡነ ጳውሎስ የተለየ ሆኖ እናገኘዋለን። አቡነ ጳውሎስን ይህ መንግስት ከሜዳ አግኝቶ በማደጎ አሳደጋቸው እንጅ ጸንሶ የወለዳቸው አይመስሉም። ይህን ለማለት ያስገደደኝ፤ እርቁ እንዲጀመር በፈቀዱት በአቡነ ጳውሎስ ላይ አቶ ስብሀት ነጋ “እርቁ እንዲጀመር በመስማማታቸው ተሳስተዋል” ብለው በወረወሩባቸው ትችት እራሱ የወያኔ መንግስት አቡነ ጳውሎስን የጉዲፈቻ ልጅ አድርጓቸዋል። የኢ.ህ.ዴ.ግ. ልጅ መስለው የተገኙት በቦታው ከተሰየሙ በኋላ ነውና ማደጎ ነበሩ ማለት ነው። ይህ ዛሬ ሊወለድ ነው ተብሎ የተነገረን ፓትርያርክ ከአቡነ ጳውሎስ ለየት ያለ ኢ.ህ.ዴ.ግ.ን በጫካ በነበረበት ጊዜ በአካሉ በሥጋውና በነፍሱ አስመሎ ይወልደው ዘነድ የጸነሰ ነው። (ሙሉው ጽሁፍ እዚህ ላይ ይገኛል)
ውድ ጎልጉል፦ ይቺን ጽሑፍ አግኝቼ ስለ ገረመኝ ለምን ይህ ሁሉ ጣጣ ቀርቶ ምርጫው በዕጣ አይሆንም ማለት ጀመርኩ። አዜብ ነኝ ከዳላስ። አመሰግናለሁ http://www.ethiopianchurch.org/essay1/150-%E1%8D%93%E1%89%B5%E1%88%AD%E1%8B%AB%E1%88%AD%E1%8A%AD-%E1%89%A0%E1%8B%95%E1%8C%A3.html