• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት ሊወድቅ ነው

February 25, 2013 02:53 am by Editor 1 Comment

ገዢው ፓርቲ ለጥገናዊ ለውጥ ምንም አይነት ቦታ የማይሰጥ መሆኑን በተደጋጋሚ ግልጽ አድርጓል። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም ይህንኑ ጉዳይ አስምረውበታል። ከዚህ የተነሳ ከገዢው ፓርቲ ጋር የነበረው የምርጫ ትግል በአጠቃለይ መክኗል። ዛሬ አገራችን ሙሉ በሙሉ ወደ ነጻነት ትግል ምዕራፍ ገብታለች።

ፓለቲካ አይነት ፡ አይነት አለው። የምርጫ ፓለቲካ እና የነጻነት ፓለቲካ አንድ አይደሉም። የምርጫ ፓለቲካ ንጹህ ነው ፡ ጭምት ነው። የነጻነት ፓለቲካ ግን ይጨክናል ፡ ይቆሽሻል።

የአገራችን ዘመናዊ የፓለቲካ ታሪክ ሲቃኝ በተደጋጋሚ የሚታየው ፡ ባለፉት 40 ዓመታት አብይ ለውጥ አራማጆች ከየዋህነታቸው እና ከንጹህ የፓለቲካ ስልታቸው የተነሳ ለአገራቸው የነበራቸው ራዕይ ተጨናግፏል ፡ መክኗል ፤ ኢትዮጵያ ያፈራቻቸው ብዙ ታላላቅ ሊሂቃኖቻችንም በከንቱ ጠፍተዋል።

ካለፉት ያልተሳኩ የነጻነት ሙከራዎች ተምረን ፡ አሁን ያለውን ትልቅ የነጻነት ዕድል በተሳካ መልኩ ለመጠቀም ከፈለግን ፡ ለነጻነታችን መጨከን እና መቆሸሽ አማራጭ የሌለው መንገድ ሆኗል።

ሙከራ 1፦ መንግስቱ እና ገርማሜ ነዋይ

አፄ ኃይለስላሴ ላይ ተደርጎ የነበረው የ1953 ዓ.ም የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አራማጆች ፡ ወንድማማቾቹ መንግስቱ ነዋይ እና ገርማሜ ነዋይ ፡ ውጥናቸው ለምን እንደ መከነ ሲመረመር ዋናው ምክንያቱ ንጹህና ጭምት የፓለቲካ ስልት ነው።

የንጉሳዊው ስርዓት በኢትዮጵያ ጭሰኛ ላይ ያደርግ የነበረውን ጭቆና ችላ ማለት ያልቻሉት ወንድማማቾች ፡ ንጉሱን ከስልጣን አስወግደው ፍትሃዊ የመንግስት እና የምጣኔ ሃብት ስርዓት ለመቅረጽ መመኘታቸው ድንቅ ነበር።

ሆኖም ግን እቅዳቸው ያልበሰለ ፡ ያልጨከነና ለመቆሸሽ ያልደፈረ ነበር። ከዚያም የተነሳ መፈንቅለ መንግስቱ ከሸፈ። መግደል የነበረባቸውን በጊዜው አለመግደላቸው ፡ ማሳተፍ የነበረባቸውን ባለማሳተፋቸው ፡ መቅደም የነበረባቸውን ባለመቅደማቸው የተነሳ የነበራቸው ራዕይ ተኮላሽቷል። የመፈንቅለ መንግስቱ ጠንሳሾች የዋህነታቸውና ፡ ንጹህነታቸው አስበልቷቸዋል።

ሙከራ 2፦ ጄኔራል መርድ ፡ ጄኔራል አምሃ እና ጄኔራል ፋንታ

በ1980 ዓ.ም የደርግን ስርዓት የተቃወሙ ጄኔራሎች ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪያምን ከስልጣን አንስተው ፡ በጊዜው ከነበሩ አማጽያን ጋር ተወያይተው አገራዊ ሰላም እና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመፍጠር መፈንቅለ መንግስት ሞክረው ነበር። ሙከራው አልተሳካም ነበር። ያልተሳካበትም ምክንያት ያው ንጹህና ጭምት ስልት ነበር።

የመፈንቅለ መንግስቱ ሙከራ የተከሰተው ኮ/ል መንግስቱ ወደ ምስራቅ ጀርመን ለጉብኝት ሲሄዱ ነበር። በዚህ ወቅት የጠንሳሾቹ ትልቁ ስህተት ተፈጸመ። ስህተቱም “ኮ/ሉ ይበሩበት የነበረውን አውሮፕላን አየር ላይ እንዳለ ይመታ” የሚለውን ሃሳብ አለመቀበላቸው ነው።

“አውሮፕላኑ የህዝብ ንብረት ነው” ፡ “በአውሮፕላኑ ውስጥ ፡ ከኮ/ል መንግስቱ ሌላ ፡ የሌሎችን ሰዎች ህይወት ማጥፋት የለብንም” ከሚሉ ንጹህና ጭምት የፓለቲካ ስልቶች የተነሳ ኮ/ሉ ምስራቅ ጀርመን በሰላም ደረሱ።  መፈንቅለ መንግስቱም መከነ።

የግንቦት 1980ው ሙከራ ከየዋህነት እና ከገርነት የተነሳ ከሸፈ። ያኔ ጄነራሎቹ ጨክነው እና ቆሽሸው ቢሆን ኖሮ ፡ አሁን አገራችን የትግራይ ጠባብ ብሄርተኞች ግዛት ከመሆን ይልቅ ፡ የህዝባዊና ዴሞክራሲያዊ መንግስት የመመስረት አጋጣሚያችን ሰፊ ይሆን ነበር።

ሙከራ 3፦ አዲስ አጋጣሚ

አገራችን ላለፉት 21 ዓመታት ስታምጥ ኖራ አሁን ከምጧ የምትገላገልበት ወቅት ላይ ደርሳለች። ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ሊወጣበት የማይችለው አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ህወሃት እንደ ቀድሞው ተመልሶ ሊያንሰራራ አይችልም።

ሆኖም ግን ካለፉት ሁለት የነጻነት ሙከራዎች ተምረን አሁን ያገኘነውን አጋጣሚ በመጠቀም የስልጣንን ልጓም ለህዝብ ካላስጨበጥን ፡ ከጭምት እና ከንጹህ የፓለቲካ ስልት የተነሳ ፡ አዱሱ አጋጣሚ ሊያመልጠን ይችላል።

ስለሆነም ፓለቲካችን የምርጫ ፓለቲካ ሳይሆን የነጻነት ፓለቲካ ስልትን መጠቀሙ ቁልጭ ያለ ጉዳይ ነው። ሳንጨክንና ሳንቆሽሽ ነጻነት አይኖርም። በፍጹም አይኖርም። በጭራሽ አይኖርም። ልብ በሉ! ካለፈው ተምረን የተለየ ስልት ካልተጠቀምን ወደ ባርነት እና ወደ ጭቆና ተመልሰን እንዳረጋለን።

ምን እናድርግ? እንጨክን ፡ እንቆሽሽ!

ግልጽና ቁልጭ ያለ የነጻነት ትግል አማራጭ የሌለው ስልት ነው። በዚህ ወቅት “የትግራይ ህዝብ ወያኔ ነው ወይስ አይደለም?” የሚለውን የሞኝ ዘፈን ትተን ነገሩን ቀለል ማድረግ ነው። የትኛው ትግሬ ‘ነቅዟል’ ፡ የትኛው ትግሬ ‘አልነቀዘም’ የሚለው የሚታወቀው ከነጻነት በኋላ ብቻ ነው።

በነጻነት ትግል ወቅት ንጹሃን ሰዎች ሰለባ መሆናቸው የማይቀር ነው። ለዚያ ህሊናችንን እናስፋ።

ህወሃት በስብሶ እንደ ተነቃነቀ ጥርስ ሆኗል ፡ የሚመነግለውና የሚነቅለው የህዝብ መስዋዕትነት ብቻ ነው።

በዚህ ወቅት ፡ ጽዋው እስኪሞላ እና የሃይል ሚዛኑ እስኪያዘነብል ድረስ ፡ ቢያንስ እንደ ግብጽ አብዮት 1 ሺ ሰማዕታት ፡ ቢበዛ ደግሞ እነደ ሶርያ የነጻነት ትግል ከ30 እስከ 60 ሺ ሰዎች ሊሰዉ እንደሚችል በመገንዘብ ህሊናችንን እናዘጋጅ። የሚሰዉ ይሰዋሉ።

ጥቂቶች ተሰውተው 80 ሚሊዮኖች ነጻ ይሆናሉ።

አዎ! የሚሰዉ ይሰዋሉ። “ለምን የድሃ ልጅ ይሙት?” “ለምን ዲያስፓራ አይዋጋም?” ለሚሉት የሰነፎችና የቱልቱላዎች ንትርክ አሁን ቦታና ጊዜው አይደለም። ህወሃት የትግራይን ህዝብ በዘፈን እና በከንቱ ሽንገላ አታሎ የእሳት ራት አድርጐ ስልጣን ላይ ተንፈራጥጧል። ዛሬ ለአገራችን ነጻነት የሚሰዉ ወገኖቻችን ይሰዋሉ።

ደም ሳይፈስ ነጻነት አይኖርም! ይህንን መራራ እውነታ እንቀበል። እንቆሽሽ። ከነጻነት በኋላ እንጸዳለን ፡ እንቀደሳለን።

ሌላው ጉዳይ ፡ የገዢው ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ ፡ በተለይም በትግራያን ላይ ሊደርስ የሚችለውን ጥቃት መገንዘብ ነው። በህብረተሰባችን ውስጥ ትግራያን አበይት የስርዓቱ ተጠቃሚና ‘ባለጊዜ’ ናቸው ፡ የሚለው እምነት በሰፊው ስላለ በልዩ ልዩ ክልሎች የሚኖሩ ትግራያን ላይ ጥቃት ሊደርስ ይችላል። ያ አይነቱ ክስተት ሊያስደነግጠንም ፡ ከነጻነት ትግላችን ሊያደናቅፈንም አይገባም።

የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች እና ‘ባለጊዜዎች’ ቢኮረኮሙ ፡ ኩርኩሙን ታሪክ ሚመዘግበው ለነጻነት ትግል ከሚከፈለው ዋጋ ጋር ደምሮ ነው። እግረ መንገዳችንን እነርሱንም ነጻ እናወጣቸዋለን።

ያም ሆነ ይህ፦ “ጅብ ከሚበላህ ፡ ጅብ በልተህ ተቀደስ።” ‚…

——-

ፌብሩዋሪ 20፡2013 – በያሬድ አይቼህ

አድራሻ፦ yared_to_the_point@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. andnet berhane says

    March 2, 2013 04:06 am at 4:06 am

    ወያኔ ከነ ሎሌዎቹ ተንዶ መውደቁ የታመነ ቢሆንም? ለዚህ የነጻነት ትግል ዋነኛው መሰረት ምን ይሆን ብለን ራሳችንን ስንጠይቅ?በተወሰኑ ሳይሆን በነጻነት ፍላጎት ያላቸው ሁሉም የሕብረተሰቡ ክፍሎች የሚጠይቅ አብይ ምእራፍ፡ በግልጽነትና በሁለንትና አጋርነት ያለው ሆኖ መቀረጽ ይገባዋል፡
    ነጻነትን ለማግኘት ዋጋ መክፈል እንዳለ የታመነ ቢሆንም ረጅምና መራራም እንድሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡
    ሁሉንም ያሳተፈ ነጻና ፍትሃዊነት ያዘለ የልዩነት የጎሳነት ስነልቦና እንድይኖር የጠራአ የነጸር ሆኖ መዋቀር ይኖርበታል፡
    የህዝቦችን አንድነት ለማምጣት የትግል አንድነት የነጻነት ጮራን ይፍነጥቃል
    በንቃት ለመታገል የሚያስችለው ፍርሃትን በትባት መቀየር ዋነኛው ነው
    ያለ ትግል ወያነን ለመጣል እድሜውን ማራዘም በመሆኑ ሁሉም ባለው አቅምና ችሎታ ይህን ታላቅ አላማ ለማሳከት በአንድ ሆኖ የሚነሳበት ሕዝባዊ የክተት አዋጅ መደረግና ለትግሉ የሚያስፈልጉትን የስንቅ የትጥቅ ተሟልተውና በሞያው ልምድና የእቅድና የስልት ተሞክሮ ያላቸው ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ማድረግ፡
    በትግል ላይ ያሉ ሁሉም ወገኖች በተናጠል የሚያደርጉትን ወደ ጥምራዊ በማድረግ በዚህ የታቀደው በመቀናጀት ስራቱን ለምገርሰስ ግምባር በመፍጠር እንዲሰሩና ትግሉ እየተካሄደ ሁሉም አንድ ወጥ ሰራዊት እንዲሆን የሚስችል ጥናታዊና ተግባራዊ የሆነ ሃገራዊ ሕግ በመንደፍ ያላችቸውን መመርያና የመተዳደርያ ሕግ በመቻቻል ወደአንድ የመመርያ ህግ ለማካተት በግልጽና በመተማመን እንዲሰራ ሲደረግ
    በትግሉ ወቅት ለሚከሰቱት ማንኛውም ጉድቶች ለመርዳት የሚያስችል የአደጋ መከላከያና መርጃ ከዓለም አቀፍ ማሕበራትና በጎአድራጊ ድርጅቶች የሚሰራ አንድ ግብረ ኃይል ማቋቋም ፡
    በተለይ ሕጻናት ሽማግሌዎች ሴቶች በተመለከተ በውሀ በመብራት በምግብ የተቻለውን ለማሟላት የሚያስችል አንድ ተንካራና በህዝብረተሰቡ ውስጥ መስራት እሚችል ግብረኃይል ማዘጋጀት
    ጦርነት በቀላሉ የሚነገር ሳይሆን ብዙ መስዋእተነት የሚጠይቅ በመሆኑ ተጀምሮ እስኪያልቅ በንብረትም ሆነ በሰው ህይወትላይ እሚያደርሰው ጥፋት ቀላል ባለመሆኑ ግምቱን በቀላሉ ማየት አያስችልም ፡
    በትግሉም መሳርያ አንግቶ በግምባር መዋጋት እውነተኛ ሀገራዊ ፍቅርና ዓላማ መኖር ያስፈልጋል ምምክንያቱም ርሃብ ጥማት እንድለና ጦርነቱም በሰዓትና በቀናት የሚቆጠር ስለሚሆን ይህንና ለለውንም ከግምት በማስገባት በመረዳት ወደትግል መግባት
    በዚህ እቅድና ትናት ከተስማማን ተግባራዊ እንዲሆን ሁሉም ለሃገሩና ለሕዝቡ በጎ አሳቢና ያለመወላወል ሁሉም ውወደ ጦር ግምባር ለማድረግ ሁላችንም በፈጣሪያችን በሀገራችን ቃል እንግባ

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule