ኤርትራ ውስጥ ያለው የፖለቲካ ሁኔታና ወቅታዊው የፕሬዚዳንት ኢሳያስ ልዕልና መላላት ተከትሎ የፖለቲካ ጨዋታው ጦዟል። በበርካቶች ዘንድ ኢሳያስ እንዳበቃላቸው ተደርጎም እየተወሰደ ነው። ኤርትራ ውስጥ ለውጥ ከተካሄደ ምን ሊከሰት ይችላል የሚለው አጓጊ ጉዳይ የሁሉንም ትኩረት የሳበ አጀንዳ ሆኗል። ኢሳያስ ያሉበት የ"ፖለቲካ ኮማ" ድብታ ውስጥ የከተታቸውም ጥቂት አይደሉም። ኢሳያስን የደረሱበት የኮማ ጣጣ መቀመጫቸውን ኤርትራ ያደረጉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚ የፖለቲካ ሃይሎችና ወታደሮቻቸው የመጨረሻ እድል ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል የጠራ መረጃ ባይሰጥም ሌላውና ዋናው የጡዘቱ አካል እንደሚሆን በርካቶች ይስማማሉ። በቅድሚያ ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት የሚጠቁሙም አሉ። ግን ምን አይነት ጥንቃቄ መደረግ እንዳለበት መፍትሄ የሚያቀርቡ የሉም። ዙሪያው ዝግ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኤርትራ ውስጥ … [Read more...] about “በኤርትራ መፈንቅለ መንግስት ይገመታል!”
News
ዜና
ከእሁድ እስከ እሁድ
“ጁነዲን ሳዶ ሳዑዲ ገብተዋል” የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩትና በቅርቡ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው የተነሱት አቶ ጁነዲን ሳዶ ወደ አረብ አገር ማምራታቸውን አውቃለሁ ሲሉ አንድ ጎልጉል ተከታታይ ተናግረዋል። ነዋሪነታቸው ሳዑዲ አረቢያ የሆነው እኚሁ ሰው ላቀረቡት ጥቆማ ማረጋገጫ አላቀረቡም። የሆነ ሆኖ አቶ ጁነዲን ኬንያ የፖለቲካ መጠየቃቸውን ኢትዮቻናል የሚባለው የመንግስት አንደበት የሆነው ጋዜጣ ይፋ አድርጓል። ኢትዮቻናልን በመጥቀስ ዜናውን በርካታ ሚዲያዎች የዘገቡት ሲሆን እስካሁን ድረስ ማስተባበያ አልቀረበም። አቶ ጁነዲን በትክክል ኬንያ የሚገኙ ከሆነ ኢህአዴግ ሊይዛቸው ስለሚችል ወደ ሌላ አገር ባስቸኳይ እንደሚያመሩ ከግምት በላይ አስተያየት ተሰጥቷል። ወደ አውሮፓና አሜሪካ ለማምራት አስቸጋሪ ሁኔታ ስለሚገጥማቸው ምን አልባትም የደንበኛችን ጥቆማ ትክክል … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
ጊዮን ሆቴል የተጠናቀቀው የኦህዴድ ድራማ!!
የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ወገኛ ድርጅት ነው። “ሲያደርጉ አይታ” እንደሚባለው እንደ ኤፈርት አይነት ታላቅ የንግድ ኢምፓየር ከፈተ። ስሙንም ቱምሳ ኢንዶውመንት አለው። ቱምሳ የድርጅት ቅርጽና መልክ ተበጅቶለት ስራ ጀመረ። በበረሃ ትግል ወቅት በነበረን ሃብት መሰረትነው ለማለት ቀዳሚዎቹ የኦህዴድ ምልምሎች ሳንቲም አዋጡና ወደ ተግባር ገቡ። ቱምሳ በስሩ ዲንሾ ትሬዲንግ፣ ዲንሾ ትራንስፖርት፣ አግሮ ኢንዱስትሪና የንግስ ድርጅቱ የጀርባ አጥንት የሆነውን ቢፍቱ ገነማ የሚባል የጫት ንግድ አቋቋመ። የትራንስፖርት ዘርፉን ይመሩ የነበሩት የአቶ ኩማ ደመቅሳ ወንድም እንክት አድርገው በሉትና ከሰረ። ዲንሾ ንግድ ማዳበሪያ እነግዳለሁ ብሎ ከ60 ሚሊዮን ብር በላይ ከንግድ ባንክ ተበደረና ታሪኩን በኪሳራ ደመደመው። ዲንሾ አግሮም ከእህት ኩባንያዎቹ እንደተማረው ኪሳራ ተከናንቦ መሬት … [Read more...] about ጊዮን ሆቴል የተጠናቀቀው የኦህዴድ ድራማ!!
ከእሁድ እስከ እሁድ
ቴዲ አፍሮ በስራው ተከብሮ ተሸለመ ታዋቂ የሚባሉት የኪነት ባለሙያዎች በአብዛኛው የህዝብ አንደበት ከመሆን ይልቅ "አጫፋሪነትን" መርጠዋል በሚል በሚዘለፉበት ወቅት ላይ ከየአቅጣጫው ምስጋና፣ ውዳሴና አድንቆት የሚዘንብበት ቴዲ አፍሮ በስራው ተከብሮ ተሸለመ። በካሊፎርኒያ ግዛት የሳን ሆዜ ከተማ (City of San Jose) በኢትዮጵያና በኤርትራ ወዳጆች ፎረም ስም ቴዲ አፍሮን የሸለመው ፌብሩዋሪ 15 ቀን 2013 ነው። የምስጋና ሽልማት /Commendation Award/ የተሰጠው ቴዲ አፍሮ ስለተሰጠው ሽልማት የቀረበው ምክንያት "ራሱን ለሰላምና ለመፈቃቀር አግልግሎት አሳልፎ ሰተ በጣም ተደናቂና ታዋቀቂ የሙዚቃ ሰው" በሚል ሙገሳ መሆኑን የቴዲ አፍሮ የፌስቡክ ገጽ ጠቁሞዋል። ቴዲ አፍሮ በኤርትራ አዲስ ትውልድ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት ያለው የጥበብ ሰው ነው። አርቆ በማስተዋልና ጊዜና … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
/ዜና ጎልጉል/ ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት "የአስተዋይነት" ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል። ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል። በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት … [Read more...] about “ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
በአልቃይዳ ሰበብ ቻይናን መቆጣጠር
የአገራቸውን አጠቃላይ ሁኔታ እና መጪው ጊዜ ምን እንደሚመስል፤ የአገራቸውን የወደፊት የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ የማኅበራዊ፣ … ሁኔታ እንዲሁም አሜሪካ በቀጣይ ዓመታት የምትከተለውን የአጭርና የረጅም ጊዜ የውጪ ፖሊሲ ዕቅድ በተመለከተ ለሁለተኛ ጊዜ ከተመረጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ማክሰኞ ምሽት ለምክርቤቱ ንግግር ያደረጉት ፕሬዚዳንት ኦባማ በርካታ ጉዳዮችን ዳስሰዋል፡፡ አፍሪካና ቻይናም የንግግራቸውን ሙሉ ቀልብ የሳቡ ነበሩ ባይባልም ሳይጠቀሱ አልታለፉም፡፡ በተለይ ስለአፍሪካ እንዲህ ብለዋል፤- ‹‹… የተለያዩ አፍቃሪ የአልቃይዳ ወኪሎችና አክራሪዎች ከአረብ ምድር እስከ አፍሪካ ብቅ እያሉ መጥተዋል፤ እነዚህ ቡድኖች ሊያመጡ የሚችሉት አደጋ እንደዚያው እያደገ መጥቷል፡፡ ይህንን አደጋ ለመቋቋምም በአስር ሺዎች የሚጠጉ ልጆቻችንን በመላክም ሆነ አገራትን መቆጣጠር አያስፈልገንም፡፡ ይልቁንም … [Read more...] about በአልቃይዳ ሰበብ ቻይናን መቆጣጠር
ከእሁድ እስከ እሁድ
“ኢትዮጵያን ቀስ ብለን ስሟን እንቀይራለን” Ethio Muslims Interfaith Dialogue for Justice በሚል ስያሜ በሚታወቀው የፓልቶክ ክፍል ውስጥ "አቡ ሃይደር" በሚል ቅጽል ስም የሚታወቁት ተናጋሪን በመጥቀስና ንግግራቸውን በቀጥታ በማሰማት የሙስሊሞች እንቅሰቃሴ የመጨረሻ ዓላማ ኢትዮጵያን የሙስሊም መንግስት ማድግ እንደሆነ በEthio Christians and Muslims discussion 4 solution የፓልቶክ ክፍል "ዘ ቤስት ሶሉሺን" በሚል የቅጽል መጠሪያ የሚታወቁት ተናጋሪ አስታወቁ። የአቡሃይደርን ንግግር በተደጋጋሚ በድምጽ ማስረጃነት ሲቀርብ ኢትዮጵያን የእስላማዊ መንግስት ከማድረግ ባሻገር አስፈላጊ ከሆነ መጠሪያ ስሟን እንደሚቀይሩ ሲናገሩ ተደምጧል። "አገሪቱ የእኛ ናት። ካፊሮች አገሪቱ የኛ ናት የሚል የታሪክ ምስክር ያላቸውም" ሲሉ የተናገሩትን … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
“የሰከነው ትግል” በጋንዲ ምድር ተዘራ
“መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው” የንግግሩ መግቢያ ነበር። “በጨለማ ውስጥ ነን። ከፍተኛ በደል እየተፈጸመብን ነው። ለመረጃ ሩቅ የሆኑ ሰዎች፣ የስልጣኔ ጮራ ያልበራላቸው ሰዎች፣ የመማር ዕድል ያላቸኙ ሰዎች፣ ግፍ እየተፈጸማባቸው ነው። መብታቸውና ሰብዓዊ ክብራቸው ተረግጧል። በጉልበት መሬታቸው እየተነጠቀ በልማት ስም እየተሸጠ ነው። ይህ ሁሉ የሚደረገው በህንድ ህዝብና መንግሥት ስም ነው። ይህ አሳዛኝ ተግባር በስማችሁ እየተከናወነ ነው። በናንተ ስም። ተቃወሙ። ታገሉ። አግዙን። ለዚህ ነው መጪው ጊዜ በእጃችሁ ነው የምለው” ይህ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ ንግግርና የትግል ጥሪ የቀረበው ህንድ ታዋቂው በሆነው ጃዋሃርላል ኔህሩ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፊትለፊት ነበር። “ትግል አርቆ ማሰብ ይጠይቃል፤ እቅድ ይፈልጋል። ትግል ህዝብን ማስተባበርና የረዥም ጊዜ … [Read more...] about “የሰከነው ትግል” በጋንዲ ምድር ተዘራ
እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ?
መለስ የሚሌኒየም ንግሥ እለት ተገኝተው ዘፈን ምረጡ ሲባሉ “የሱዳን ዘፈን ይሁንልኝ” ብለው ከባለቤታቸው ጋር የተምነሸነሹበት የሚሌኒየም አዳራሽ በአቶ አሊ አብዶ የከንቲባነት ዘመን ለመስጊድ ማሰሪያ ተጠይቆ እንደነበር ፣ አቶ አሊም ቦታውን ለተጠየቀው ዓላማ እንዲውል መፍቀዳቸውንና ውሳኔው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ኢህአዴግ ዘንድ መረጃው ደርሶ መታገዱን ውስጥ አዋቂዎች ያስታውሳሉ። ከምርጫ 97 በኋላ ደግሞ መላ ሰውነታቸውን የተሸፋፈኑ ሙስሊሞች እየበዙ በመሆኑ ጉዳዩ ሥር ሳይሰድ፣ ከጀርባው እነማን እንዳሉበት ክትትል እንዲደረግ በታዘዘው መስረት የብሔራዊ የመረጃና የደህንነት አገልግሎት አስገራሚ ሪፖርት አቅርቦ እንደነበር እነዚሁ ክፍሎች ይናገራሉ። በክትትሉ የተገኘው መረጃና የመጨረሻ ድምዳሜ ተሸፋፍነው የሚለብሱት እህቶች አብዛኞቹ ሴተኛ አዳሪዎችና የገንዘብ ችግር ያለባቸው የሌላ ሃይማኖት … [Read more...] about እስላማዊ መንግሥት በኢትዮጵያ?
Indian investors are forcing Ethiopians off their land
Ethiopia's leasing of 600,000 hectares (1.5 acres) of prime farmland to Indian companies has led to intimidation, repression, detentions, rapes, beatings, environmental destruction, and the imprisonment of journalists and political objectors, according to a new report. Research by the US-based Oakland Institute suggests many thousands of Ethiopians are in the process of being relocated or have fled to neighbouring countries after their traditional land has been handed to foreign investors … [Read more...] about Indian investors are forcing Ethiopians off their land










