There is a renewed hope in Ethiopia that the much awaited visit of Congressman Chris Smith to the severely tyrannized nation would help alleviate the plight of venerated political prisoner Andualem Arage who is serving a lengthy jail sentence for “terrorism.” (Read more) … [Read more...] about Ethiopia: call on Congressman Chris Smith to save life of the most revered young political prisoner.
News
ዜና
ከእሁድ እስከ እሁድ
ሻማ ማብራት ፣ ኤምባሲ መውረር በአብዛኛው የኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ሻማና ጧፍ ማብራት፣ በሰላማዊ ሰልፍ መጮህ፣ ፒቴሽን መፈራረም፣ በተለያዩ ማህበራዊ አውታሮችና ድሮች መሳደብና የመሳሰሉት ናቸው። ባለፈው ሳምንት የኤርትራ ተወላጆች ሎንዶን የሚገኘውን የኢሳያስ ኤምባሲ ጥሰው በመግባት የፈጸሙት የተቃውሞ ተግባር ከፍተኛ የሚዲያ ትኩረት ስቧል። “ኤምባሲው የእኛ ነው። ከኤምባሲያችን ወደ የትም አንሄድም” ያሉት የኤርትራ ተወላጆች የሚፈሩትን ኢሳያስን ያገኙ ያህል ፎቷቸውን ከግድግዳ በማውረድ መሬት ላይ በመከስከስ ረጋግጠው ተቃውሟቸውን ሲገልጹ ራሳቸው ፕሬዚዳንት ኢሳያስና ዓለም ተመልክቷል። ይህ ታላቅ የተቃውሞ መልዕክት ለሁሉም ባለስልጣናት መልዕክት ሲሆን በተለይም ስደት ልዩ መለያው ለሆነው የኤርትራ ህዝብ ባንድነት ይነሳሳ ዘንድ የሚቀሰቅስ ተግባር ሆኖ ተገኝቷል። የእኛ አገር ተቃዋሚዎችና … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
ለላሊበላስ ማን ይድረስ?
የላሊበላ ውቅር አብያተ ከርስቲያናት የመፍረስ አደጋ ውስጥ እንደሚገኙ መነገር የጀመረው ዛሬ አይደለም። ቢያንስ ላለፉት አስራ ሁለት ዓመታት ያካባቢው ነዋሪዎች፣ በወፍ ዘራሽ ወደዚያ ያቀኑ ጋዜጠኞችና ለልቦናቸው የቀረቡ የገዳማቱ አገልጋዮች አስጠንቅቀዋል። ማስጠንቀቂያው ግዙፍና ዕረፍት የሚከለክል ቢሆንም ተግቶ ምላሽ የሰጠ አካል ባለመኖሩ፣ ጉዳዩን በመያዝ የተከራከረና ገዢውን ፓርቲ ያስጨነቀ የህዝብና የቅርስ ጠበቃ ከአገር ውስጥም ሆነ ከውጭ ባለመገኘቱ “ለላሊበላ ኢህአዴግና ተቃዋሚዎች አንድ ናቸው” የሚል አስተያየት እየሰጡ ነው። ዛሬ ጥያቄው አንድ ነው፡- “ለላሊበላ ማን ይድረስለት?” የሚል! የኢትዮጵያዊያን ጉልህ ታሪክ የሆነው ላሊበላ በመፍረስ አደጋ ውስጥ ነው፤ እየተሰነጣጠቀም ይገኛል፤ ውሃ ዘልቆት እየገባው ነው። ላሊበላ አንድ ቀን ወደ አለመኖር ሲቀየር “ሰበር ዜና” ማለትና … [Read more...] about ለላሊበላስ ማን ይድረስ?
Ethiopia’s resettlement scheme leaves lives shattered and UK facing questions
Mr O twists his beaded keyring between his long fingers as he explains why he started legal action against Britain's international development department over its aid funding to Ethiopia. Three other refugees from the Gambella region listen as he speaks in a stifling room in north-eastern Kenya. All have a story to tell. The accounts are broadly similar, but the details reveal the individual tragedies that have shattered their lives: they say they were forced to leave their villages, beaten by … [Read more...] about Ethiopia’s resettlement scheme leaves lives shattered and UK facing questions
Coup Attempt by Rebel Soldiers Is Said to Fail in Eritrea
GARSEN, Kenya — Eritrea, a sliver of a nation in the Horn of Africa that is one of the most secretive and repressive countries in the world, was cast into confusion on Monday after mutinous soldiers stormed the Ministry of Information and took over the state-run television service, apparently in a coup attempt. According to several people with close contacts inside Eritrea, the coup attempt failed, with government troops quelling the would-be rebellion and no one rising up in the streets. But … [Read more...] about Coup Attempt by Rebel Soldiers Is Said to Fail in Eritrea
በኤርትራ መንግሥት አልተገለበጠም
“ኩዴታ ሲደረግ በቅድሚያ በቁጥጥር ስር ሊውል የሚገባው የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ጣቢያ ነው። በአስመራ ይህ ስለመሆኑ የተባለ ነገር የለም። ታዲያ እንዴት ነው ኩዴታ ተከናውኗል ሊባል የሚችለው? በርግጥ ገለልተኛና ነጻ የውጪ ሚዲያዎች አለመኖራቸው የመረጃውን መጠንና ጥራት ቢገድበውም እስካሁን የሚወጡት መረጃዎች እስረኞች እንዲፈቱ የሚጠይቅ እንጂ የማስገደድ አይመስልም። በዚህ መነሻ ኢሳያስ ሙሉ በሙሉ አደጋ ውስጥ ናቸው ማለት አይቻልም። ግን የመደራደር ነገር ሊኖር ይችላል” አውሮፓ የሚኖር ኤርትራዊ ለጎልጉል የተናገው ነው። አስር ሺህ የሚደርሱ የፖለቲካ እስረኞች እንዳሏት የሚነገርላት ኤርትራ ዛሬ አመሻሹ ላይ አዲስ ዜና አሰምታለች። የተቀየሙ የጦር ሃይሎች የማስታወቂያ ሚኒስቴርን ከበው የፖለቲካ እስረኞች እንዲለቀቁ በማስገደድ ላይ እንደሆኑ የተለያዩ የዓለም መገናኛዎች እየዘገቡ ነው። … [Read more...] about በኤርትራ መንግሥት አልተገለበጠም
ከእሁድ እስከ እሁድ
በደቡብ ኦሞ የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ ቁፋሮ ተጀመረ በደቡብ ኦሞ ጨው ባህር አካባቢ የነዳጅ ፍለጋ ሥራ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ታሎው ኦይል የተሰኘው የእንግሊዝ ኩባንያ የመጀመሪያው የሆነውን የፍለጋ ጉድጓድ ቁፋሮ ከትናንት በስቲያ ጀመረ፡፡ ቁፋሮው የተካሄደው በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በዳሰነች ወረዳ ከኦሞራቴ ከተማ 15 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ነው፡፡ የነዳጅ ፍለጋ ቁፋሮ የተጀመረው 18 ወራት የዘለቀ የሴይስሚክ (በመሬት የድምፅ ሞገድ በሚከናወን) ጥናትና 18,000 ኪሎ ሜትር በሸፈነ የአውሮፕላን የግራቪቲ ጥናት ከተከናወነ በኋላ እንደሆነ ኩባንያው ገልጿል፡፡ የአየር ጥናቱ በዓለም ላይ ከተከናወኑት ሰፊ ጥናቶች ውስጥ ይመደባል ተብሏል፡፡ ጥናቶቹ በደቡብ ኦሞ ዞን የመጀመሪያው የነዳጅ ፍለጋ ጉድጓድ የት አካባቢ መቆፈር እንዳለበት ያመላከቱ እንደሆነ ኩባንያው አስታውቋል ሲል የዘገበው … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
አሜሪካ በአፍሪካ ወታደራዊ የበላይነቷን ልታረጋግጥ ነው!
አዲስ በተያዘው የአውጳውያን ዓመት አሜሪካ በአፍሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ የበላይነትን ሊያረጋግጥላት የሚችል ፕሮግራም ነድፋለች፡፡ ከሦስት ሳምንታት በፊት ይፋ የሆነውን ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድረግ በሚያስችል ሁኔታ ላይ የተነደፈውን ዕቅድ የሚያስፈጽሙ 35 የአፍሪካ አገሮችም ተመርጠዋል፡፡ ምንም እንኳን ዜናው ይፋ ከሆነ የቆየ ቢሆንም የአሜሪካንን የመከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) እንዲመሩ የታሰቡት ሪፓብሊካኑ ቸክ ሔግል ቀዳሚ ተወዳዳሪ መሆናቸው እስከሚገለጽ ድረስ የብዙዎችን ቀልብ አልሳበም ነበር፡፡ የአሜሪካንን ጦር ሠራዊት በየአገሩ በማዝመት ጉዳይ ላይ ጽኑ የተቃውሞ አስተሳሰብ የሚከተሉት ሔግል እንዲህ ዓይነቱን ፕሮግራም ለማስፈጸም ገጣሚ ሚኒስትር እንደሚሆኑ በሰፊው እየተነገረ ነው፡፡ የመከላከያ ሚኒስቴር መ/ቤቱ ይፋ እንዳደረገው በአፍሪካ በየጊዜው እያገረሸ የሄደውን የአሸባሪዎች … [Read more...] about አሜሪካ በአፍሪካ ወታደራዊ የበላይነቷን ልታረጋግጥ ነው!
“በ2030 ከሚከሽፉ መንግሥታት አንዷ ኢትዮጵያ ነች”
የአሜሪካ የብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ2030 የሚከሽፉ 15 መንግሥታትን (failed states) ዝርዝር አውጥቷል፡፡ “በግጭት መብዛትና በአካባቢ ጥበቃ ቀውስ ምክንያት” ይከሽፋሉ ተብለው ከተተነበዩት የአፍሪካ፣ የእስያና የመካከለኛው ምስራቅ አገራት መካከል ኢትዮጵያ አንዷ ነች፡፡ እጅግ የነጠረ፣ ያልተዛባና የተጠና ዘገባ ለአሜሪካ የስለላ ተቋማት፣ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ አውጪዎችና ለዓለምዓቀፍ ግንኙነት ተመራማሪዎች በማውጣት የታወቀው የአሜሪካ ብሔራዊ የደኅንነት ምክርቤት ከተቋቋመ በርካታ ዓመታትን አስቆጥሯል፡፡ ምክርቤቱ በሚያወጣቸው ዘገባዎች የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ የተለያዩ መ/ቤቶች ተጽዕኖ እንደማያደርጉበት የሚናገር ሲሆን፤ ዘገባዎቹንም ከአድልዎ እና ከአሜሪካ መንግሥት አቋም ነጻ በመሆን እንደሚያዘጋጃቸው ይናገራል፡፡ የም/ቤቱ ዘገባ በተለይ ምርጫ … [Read more...] about “በ2030 ከሚከሽፉ መንግሥታት አንዷ ኢትዮጵያ ነች”
በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው
በደሴ ከተማ ግብር ከፋዩ ነጋዴና ግብር ሰብሳቢው ክፍል አልተስማሙም። የከተማዋ ሹመኞች፣ ነጋዴዎች፣ በአነስተኛና ጥቃቅን ንግድ የታቀፉና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ከንቲባውን ሲወቅሱ ተሰማ። በፓርላማ የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ርምጃ እንደሚወሰድ ጠቁሟል። በግምገማው ማብቂያ ከንቲባው ለፓርላማ አባላቱ ቢሯቸው ክፍት አድርገው እሳቸው ግን አልነበሩም። የጎልጉል ምንጮች እንደሚሉት ግምገማውን ተከትሎ የሚወሰድ ርምጃ ይኖራል። የዳቦ ግራም ቀንሰው የተገኙ ሶስት ዓመት ተፈርዶባቸዋል። የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት አየር ላይ ያዋለው ዜና በደሴ ከተማ ግምገማና የመስክ ምልከታ የተደረገበትን ዋና ምክንያት አልጠቆመም። በዘገባው እንደተጠቆመው የንግድ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባካሄደው የመስክ ምልከታ የከተማዋን ከንቲባ የሚያጋልጥ አቤቱታ ቀርቦላቸዋል። ከደሴ ምክር ቤት አባል አንዱ የሆኑት … [Read more...] about በደሴ የዳቦ ግራም የቀነሱ ሶስት ዓመት ተፈረደባቸው