• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢህአዴግ በኖርዌይ ገንዘብ ማሰባሰብ ተሳነው

April 29, 2013 01:36 am by Editor 1 Comment

በስደት አገራቸውን ለቀው የወጡ ሰዎች ያለመሰለል መብት አላቸው። በህግም የተደነገገ ነው። ከለላ የሰጣቸውም አገር ይህንን የመከላከልና የመቃወም ግዳጅም አለበት። ከለላ ያገኙ ስደተኞችም ሆኑ ከለላ እንዲሰጣቸው ያመለከቱ ወገኖች ስለመሰለላቸው ተጨባጭ ማስረጃ ማቅረብ ከቻሉ ህጉን ጠቅሰው የመከራከር መብት አለቸው። ለመብታቸው ሲከራከሩ በመደራጀት ቢሆን ይበልጥ ውጤታማ ሊሆኑ እንደሚችሉ አውሮፓ በስደት ያሉ ቀድሞ የውጪ ጉዳይ የዲያስፖራ ኢንጌጅመንት ዳይሬክቶሬት ዲፓርትመንት ኤክስፐርት ይናገራሉ።

እኚሁ ሰው እንደሚሉት ከ1997 ዓ ም ምርጫ በኋላ በአቶ መለስ ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተቋቋመው ይህ ዲፓርትመንት ለጠቅላይ ሚኒስትሩና ለወቅቱ የውጪጉዳይ ሚኒስትር አቶ ስዩም መስፍን ሪፖርት ያቀርብ ነበር። በጁላይ 2003 ስድስት አባላትን በመያዝ የተቋቋመው ዲፓርትመንት “ብዙሃን አድፋጭ” ዲያስፖራ ወይም “silent majority” የሚባሉትን ለመማረክና በስደት ውጪ አገር የሚኖሩትን የተቃዋሚ ድርጅት ዋና ደጋፊዎችንና አመራሮችን የሚከታተል ቻፕተሮች አሉት።

የአገዛዙ ደጋፊ ለሚባሉት ዲያስፖራዎች የቀረጥ ነጻ መብት በመስጠት፣ መሬት በማደል፣ በማህበራት በማደራጀት ቢቻል መታወቂያ በመስጠት፣ “ለአገር ግንባታ ደጋፊ ማድረግ” በሚል ሽፋን በያሉበት አገር ከኤምባሲ ጋር ግንኙነት እንዲፈጥሩ በማድረግ የተዘረጋው መዋቅር የአውሮፓውን የክትትል ስራ በግንባር ቀደምትነት እንዲመራ የመደበው የብራስልስ ኤምባሲን ነው። በቤልጂየም ኢትዮጵያ ኤምባሲ ካውንስለር በመሆን የሚያገለግሉት የቀድሞው የህወሃት ታጋይ ይህንኑ የአውሮፓ የክትትል ቻፕተር እንደሚመሩት የሚያስረዱት የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ሰራተኛ የቻፕተሩን ጠርናፊ “አቶ መለስ በታመሙበት ወቅት ብራስልስ ሆነው አስፈላጊውን ሁሉ ሲያደርጉ የነበሩ የስርዓቱ ታማኝ ሰው ናቸው” ሲሉ ይገልጹዋቸዋል።

በጥቅማ ጥቅም ዲያስፖራ ውስጥ ሆነው የክትትል ስራ በመስራት በያሉበት አገር ካለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጋር ግንኙነት በመፍጠር ስርዓቱን የሚያገለግሉ ስለመኖራቸው በውል የሚናገሩት እኚሁ ሰው “ስርዓቱን ሸሽተው ጥገኛነት የሚጠይቁ ኢትዮጵያውያን ስለ አገዛዙ የሚሰጡት መረጃ ስለሚያንገበግባቸው ዲያስፖራው ውስጥ ያለውን እንቅስቃሴ ለማኮላሸት ከፍተኛ በጀት ይመደባል። በዚሁ በጀት እጅግ ቀረቤታ ላላቸው ደጋፊዎቻቸው በሚኖሩበት አገር ተራ የጉልበት ሰራተኛ የሚያገኘው ክፍያ ተሰልቶ ይከፈላቸዋል” በማለት አገሩን፣ ቤተሰቡን፣ ንብረቱን፣ ቤተዘመዱን ጥሎ የሸሸውን ዜጋ እየተከታተሉ ሪፖርት ስለሚያቀርቡት ክፍሎች ይናገራሉ።

ሰፊ ማብራሪያ ያቀረቡት እማኝ የኢህአዴግ ደጋፊዎች የልማትና ድጋፍ ማሰባሰቢያ መድረኮችን በማመቻቸት ታማንነታቸውን እንደሚያሳዩ የሚገልጹት የቀድሞ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ባልደረባ “ይህ አሰራር የተኮረጀው ከቻይና ነው። የተለያዩ አገር አሰራሮችና የደህንነት መዋቅሮች የተጠኑ ቢሆንም የ  ቻይናው የተመረጠው ለስራውና ኢህአዴግ ለሚፈልገው አደረጃጀት አመቺ ሆኖ በመገኘቱ ነው” ሲሉ የመዋቅሩን ተፈጥሮ ያስረዳሉ።

ከሳምንት በፊት በኖርዌይ ስታቫንገር፣ ዛሬ ኤፕሪል 28/2013 ደግሞ በኦስሎ ስለተካሄደው የቁጣ ተቃውሞ አስተያየት የሰጡት እኚሁ ሰው “ኢህአዴግ ሊገለኝ ነው በማለት ሸሽተው ጥገኝነት የጠየቁ ወገኖች ከመንግስት ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የላቸውም። ሊኖራቸውም አይችልም ማስረጃ በማሰባሰብ ጉዳዩን ወደ ህግ ማቅረብ ይቻላል” ባይ ናቸው።

“ተሰደን አገር ለቀን ወጣን። አገራችን እንዳንኖር ተደረግን። በስደት በምንኖርበት አገር ድረስ መጥተው ገንዘብ ሊጠይቁን ማሰባቸው ይገርማል። እንደዚህ ገንዘብ የተጠሙበት ምክንያት ምን ይሁን? ኢህአዴግ አገሬ እንዳልኖር አደረገኝ፣ ህይወቴ አደጋ ላይ ነው በሚል ከለላ የጠየቀ ሰው እንዴት መንግስት ደጅ ይቀርባል። ይህ እኮ ህገወጥ ነው። ወንጀል ነው። ከለላ የሰጠው አገርም ሆነ ዋናው የስደተኞች ህግ አይደግፈውም” በሚል አንድ ጥግ ይዘው የሚነጋገሩና የሚወያዩም አጋጥመውኛል።

መከላከያው አክራሪንና አልሸባብን ይደመስሳል በሚል የማይነጥፍ ገበያ አላቸው። መሬት ይሸጣሉ። ንግዱን ተቆጣጥረውታል። ኢንቨስትመንቱን በጃቸው አድርገውታል። አስመጪና ላኪነቱን የግላቸው አድርገውታል። ባዕድ ሃይል የማያደርገውን የከፋ ተግባር እንመራዋለን በሚሉት ህዝብ ላይ ይፈጽማሉ። አገሪቱን በዘርና በጎሰኝነት አስተሳሰብ መርዝ በክለው እርስ በርስ እያጫረሱ ምድሪቱን የበቀል ቡቃያ አድርገዋታል። ታዲያ እነዚህ ሰዎች በየትኛው ሞራላቸው ነው ስደት የሚለበልባቸውን ዜጎች ሰብስበው ገንዘብ የሚጠይቁት? የሁሉም ጥያቄ ነው።

በተጠቀሰው ቀን ለአባይ ግድብ የገንዘብ ማሰባሰቢያ ለማካሄድ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ አጭር የስልክ መልዕክት (የኤስ ኤም ኤስ) ጥሪና በተለያዩ አደረጃጀቶች ጥሪ ተበትኖ ነበር። ኦስሎ የሚኖሩ የስርዓቱ ሰለባዎች ራሳቸውን አደራጅተውና ግብረኃይል አቋቁመው በስብሰባው ለመገኘት ዝግጅታቸውን አስቀድመው እንዳከናወኑ በስፍራው የነበሩ ለጎልጉል ዘጋቢ አመልክተዋል።

እንደተባለው ጠዋት ረፈድ ፈድ ሲል በስቶኮልም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሰው ስብሰባውን ለመምራት ወዳጆቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ያዘጋጁት መድረክ ላይ ለመቀመጥ Radisson Blue Scandinavia Hotel ሲደርሱ የጠበቃቸው ሌላ ነበር። በስብሰባው ለመገኘት የሚያስችል “የዜግነት” መብት ያላቸው ወገኖች ስብሰባውን ለመካፈል ጠየቁ። “አትገቡም” ሲባሉ ተቃውሟቸውን ከቁጣ ጋር አሰሙ። ባለስልጣኑ ማሽላ እያረረ ይስቃል እንደሚባለው ፈገግታ በማሳየት በምሬት በሚወርደው የተቃውሞ ቃል መገረፋቸውን ለመደበቅ ሞከሩ። ንዴታቸውን ለመደበቅ ሲታገሉ ጭራሹኑ ስብሰባውን ማድረግ በማይችሉበት ደረጃ ተቃውሞው ስለጨመረ ለአባይ ግድብ ብር ለማሰባሰብ የተወጠነው የኦስሎው ውጥን ስታቫንገር እንደሆነው ተኮላሸ። ፖሊስ ስብሰባው ሊካሄድ እንደማይችል አረጋገጠ።

በኖርዌይ ከሚታተሙትና ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ ዜና ካሰራጩት መካከል፣ ቬጌ የሚባለው ጋዜጣ አስራ አንድ ሰዎች ህገወጥ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል በሚል መታሰራቸውን አስነበበ። በስፍራው ቁጣቸውን የገለጹ ወገኖች ሳያስፈቅዱ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል በሚል ጋዜጣው የእስሩን ምክንያት ፖሊስን ጠቅሶ አስፍሯል። በስፍራው የተገኙም ሆኑ የዚህ ሪፖርት አቅራቢ እንደታዘበው ዜጎች አስቀድመው የጠየቁት በስብሰባው ላይ እንሳተፍ የሚል የዜግነት ጥያቄ ነበር። በጥያቄያቸው መሰረት ወደ ስብሰባው ቦታ ለመግባት ሳይችሉ መከልከላቸው እንደ ዜጋ የሞራልና የማንነት ጥያቄ በመሆኑ ቁጣቸው ከስርዐቱ ተፈጥሮ ጋር ተዳምሮ የነደደ ነበር።

ከፍተኛ ቁጥር የነበረው የፖሊስ ሃይል አስራ ሁለት ተሽከርካሪዎችን አሰልፎ የቁጣውን ሰልፍ “ለመቆጣጠር” እንደቻለ፣ የሰለጠኑ ውሾችና ከሆቴሉ በቅርብ ርቀት ሄሊኮፕተርም ተዘጋጅቶ እንደነበር ቬጌ አስነብቧል። የጎልጉል ሪፖርተር ባሰባሰበው መረጃ አባይ ቢገደብ የሚጠሉ ወገኖች የሉም። ቅድሚያ ሊከናወኑ የሚገባቸው ጉዳዮች እንዳሉ ግን ይስማማሉ። ቅድሚያ አፈናውና ያለ ህዝብ ውክልና በጠመንጃ ከህዝብ ጫንቃ ላይ መንሰራፋት ሊቆም ይገባዋል። የመብት ገደብም ሊቆም ግድ ነው። ይህ ሲሆን ገንዘብ ያለው በገንዘቡ፣ ገንዘብ የሌለው በጉልበቱ አድርግ የተባለውን ያደርጋል። አገርም በዜጎቿ ፍላጎትና እኩል ተሳትፎ ያለ ስጋት ትለማለች።

የታሰሩት ሰዎችን በተመለከተ ይህ ሪፖርት እስከተጠናከረበት ሰዓት ድረስ ስለመፈታታቸው የተሰማ ነገር የለም። በሳምንት ጊዜ ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ጠንካራ ሊባል የሚችል ተቃውሞ ያጋጠመው ኢህአዴግ፣ በኖርዌይ ተመሳሳይ ፕሮግራም ለማካሄድ ባይሞክር እንደሚሻለው ገለልተኛ ነን የሚሉ ወገኖች ተናግረዋል። አቶ መለስ በህይወት በነበሩበት ወቅት በኖርዌይ የገጠማቸው ተቃውሞ የከፋ እንደነበርና የመጡበትን ጉዳይ በወጉ ሳይጨርሱ መመለሳቸውን ያስታወሱት እነዚሁ ክፍሎች “አሜሪካ በዲቪ የተጓዙ ደጋፊዎች ሊኖሩ ይችላሉ። አውሮፓ ግን በትምህርት መጥተው የቀሩ ካልሆኑ በስተቀር ኢህአዴግ በግልጽ ሊደግፉት የሚችሉትን አባላት ለመግኘት አይቻለውምና አባይን እንደጀመረው ከቻይና ተበድሮ ቢያጠናቅቀው ይመረጣል” ብለዋል። ኢህአዴግ በተለያዩ የአውሮፓ ከተሞች፣ በሳዑዲ አረቢያ፣ በዱባይ፣ በደቡብ አፍሪካ ተመሳሳይ ተቃውሞ እንደገጠመው በተለያዩ ሚዲያዎች መዘገቡ የሚታወስ ነው። (ፎቶ: VG)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Teshale says

    April 29, 2013 05:58 pm at 5:58 pm

    Never heard of country, the leaders of which are humiliated, wherever they go overseas, by its own people in the diaspora in such an extent that spans from Europe, America, Africa, etc. Shame on Woyane.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule