• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦባማ አርፍደው ወደ ኢትዮጵያ?

April 27, 2013 07:01 am by Editor Leave a Comment

በአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ከሚገኙት የተለያዩ እንግዶችና ባለስልጣናት በተጨማሪ አራት ታላላቅ መሪዎች እንደሚገኙ እየተነገረ ነው። በዋናነት የሚጠቀሱት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ኦባማ ሲሆኑ፣ የቻይና አቻቸውም ዋናውና ታላቁ እንግዳ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።

የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ባለፈው ረቡዕ ለአሜሪካ ኮንግረንስ ኮሚቴ የተናገሩትን በመጥቀስ ዜናውን የላኩልን ክፍሎች እንዳሉት ኦባማ ወደ ኢትዮጵያ ሊያመሩ ይችላሉ።

ውጪ ጉዳይ ሚ/ሩ ኦባማ ኢትዮጵያ ስለመሄዳቸው ፍንጭ ቢሰጡም ስለጉዞው ዝርዝር አለመናገራቸው ታውቋል። የቻይና በአፍሪካ ሚና መጉላት ውሎ አድሮ የጠዘጠዛት አሜሪካ፣ በመጪው ወር በሚካሔደው የአህጉሩ 50ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ በፕሬዚዳንቷ ለመወከል መወሰኗ “ጉባኤ አድማቂ” አሰኝቷታል።

“በአፍሪካ ብዙ የምንሰራው ስራ አለን” ሲሉ የተናገሩት ኬሪ “በድግሱ” ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል። እየተጣጣመ የመጣው የአፍሪካና የቻይና ፍቅር እንዲሁም ቻይና በአፍሪካ ያላት ሰፋ ያለ ኢንቨስትመንት ለአሜሪካ አሳሳቢ ከመሆኑ ባሻገር ቻይና የምትከተለው የንግድ ስልት በአጠቃላዩ ሁኔታ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን ውጪ ጉዳይ ሚ/ር ኬሪ አልሸሸጉም፡፡ ዝርዝር ከመስጠት ቢቆጠቡም ጉቦ፣ ሙስና፣ አምባገነኖችን መርዳት በማለት የተወሰኑትን በግልጽ ከመጥቀስ አላለፉም፡፡

ኦባማም ወደ ኢትዮጵያ የሚያቀኑበት ጉዳይ አሜሪካ በአፍሪካ ለምትከተለው አዲስ እቅድ ማጠናከሪያ ካስማ ለመቸንከር እንደሆነ አብዛኞች ይስማሙበታል። “ቻይናን በቅርብ ሆኖ መቆጣጠር” በሚለው መርህ  የአፍሪካን አምባገነኖች ወታደራዊ ድጋፍ በመስጠት ልቡናቸውን የመስለብ እቅድ ይዛ እየሰራች ያለችው አሜሪካ፣ የቻይናና የአፍሪካ ግንኙነት “የፓለቲካ እባጭ” የሆነባት ቻይና ድፍን የአፍሪካ መሪዎችን ቤጂንግ ጋብዛ ወዳጅነቷን አደባባይ በማውጣት ጸሐይ ካስመታቸው በኋላ ነበር። በርካታ መረጃዎችም በዚሁ ዙሪያ ቀርበዋል።

በቤጂንጉ ጉባኤ ቻይና ዶላር ለሚናፍቁት የአፍሪካ መሪዎች ብድር ያለ አንዳች ቅድመ ሁኔታ፣ የንግድ፣ የኢንቨስትመንት፣ የቴክኖሎጂ፣ የመንገድ ግንባታ፣ የተለያዩ ርዳታዎች ለማድረግ፣ ከዚህም በላይ አምባገነኖች የስለላ መዋቅራቸውን እንዲያደራጁ የሚያስችላቸው በገሃድ እንዳይሰራጩ የተከለከሉ የአፈና መሳሪያዎችን ጭምር ለመስጠት ቃል ገብታ አፍሪካን የገበያዋ ሳሎን ስታደርግ አሜሪካና አውሮፓውያኖቹ ደነገጡ፤ ታመሙ።

በተመሳሳይ ቻይና ዘይትና የተለያዩ ማዕድኖችን ከአፍሪካ በመዛቅ የገበያ ድሯን ዘርግታ አፍሪካን ተጣባቻት። ዜጎቿንና የንግድ ተቋሞቿን አፍሪካ ምድር በትና ከላይም ከታችም ተቆጣጠረቻት። ከዚህ በኋላ ነበር መቀደሟ ያሳሰባት አሜሪካ ቻይናን በቅርብ መከታተል በሚል አዲስ ስልት የነደፈችው።

ባለሙያዎችና የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት አሜሪካ በኢኮኖሚና በገንዘብ ድጋፍ የአፍሪካን ሆዳም መሪዎች በማባበል ቻይናን ለመፎካከር በዛሬው ጊዜ አይቻላትም፤ በገሃድ እከተለዋለሁ የምትለውን ግብዝ ፖለቲካ ያበላሽባታል። እንደውም አታስበውም። ለዚህ ይመስላል የአፍሪካ አገሮችን ወታደራዊ ሃይል በማሰልጠን፣ በማደራጀት፣ በማስታጠቅ፣ የየአገራቱን ወታደራዊ እዝ ከበላይ ሆኖ በመምራት የቻይናን እንቅስቃሴ ለመበርበር የተንቀሳቀሰቸው። (ከዚህ በፊት “የኦባማ አስተዳደር መጪው የአፍሪካ ዕቅድ” በሚል የጻፍነውን እዚህ ላይ ይመልከቱ)

አምባገነኖች የመከላከያ ኃይላቸውን እንደ ብረት ለማጥበቅ ካላቸው የጸና ፍላጎት አንጻር አሜሪካ የነደፈችው ስልት የተዋጣለት እንደሆነ የሚናገሩ ክፍሎች “አሁን አሜሪካ ወታደራዊ ሃይልን ለማጠናከር በሚል ወደ አፍሪካ የገባችበት ስልት፤ ከአፍሪካ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች እውቅና ውጪ የሚፈጸም ተግባር ስለሌለ መረጃ የማግኘት አቅሟ የቻይናን መስኮት በርግዳ ሳሎኗን የማየት ያህል ነው” ይላሉ፡፡

አሜሪካ አሁን ባለችበት ደረጃ አፍሪካ 50ኛ ዓመት በዓል ስታከብር በይፋ ባይረጋገጥም ኦባማ የመገኘታቸው ሚስጥር ከፖሊሲያቸውና ቻይናን በቅርብ ሆኖ ከመቆጣጠር አዲሱ ስልታቸው በመነሳት እንደሆነ የማያሻማ ነው። በጉባኤው ላይ አራት ከፍተኛ የአገር መሪዎች እንደሚገኙ የኢህአዴግ አንደበት ፋና ጠቁሟል ግን ዝርዝር አላቀረበም። ጆን ኬሪ “ከአፍሪካ ጋር ባለን ግንኙነት ላይ ያሉ ክፍተቶችን በመሙላት ከአህጉሪቷ ጋር ያለንን ግንኙነት ለማሻሻል እንሰራለን” ማለታቸውን ፋና ምንጭ ሳይጠቅስ አስፍሯል።

ፋናም ሆነ ሌሎች የመንግስት ሚዲያዎች ይፋ ባያደርጉትም የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ባለስልጣናትና የአገሪቱ ፕሬዚዳንት የስብሰባው ታላቅ እንግዳ እንደሚሆኑ ፖለቲከኞች ቅድመ ግምታቸውን አኑረዋል። በኢህአዴግ ጉባኤዎች ላይ የክልል አንድ ልዩ ዞን ተወካይ እስኪመስል ልዑክ በመላክና የቻይንኛ ቀረርቶ በማሰማት ተሳትፎ ያላት ቻይና ለአፍሪካ ህብረት ታላቅ ስጦታ ማቅረቧ የሚታወስ ነው።

የአፍሪካ ኅብረትን ዘመናዊ ህንጻ በራስዋ ወጪ ያስገነባቸው ቻይና በቤቷ፤ ኦባማም ከተገኙ በእንግድነት የኅብረቱን የምስረታ ዘመን አስመልክቶ ቻይና በነጻ ገንብታ ባስረከበችው ህንጻ ውስጥ ሆነው ህንጻውን እያደነቁ ይደሰኩራሉ።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule