• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ባህርዳር አነባች!! ባህርዳር አነባች!!

May 15, 2013 05:11 am by Editor Leave a Comment

እለተ እሁድ 04/09/05 ከምሽቱ ሁለት ሰዓት በባህርዳር ከተማ አባይ ማዶ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር እንዲሁም የብአዴን ዋና ፅ/ቤት ከሚገኝበት “የሰማእታት ሀውልት” ተብሎ ከሚጠራው ቦታ አቅራቢያ አንድ የፌደራል ፖሊስ በንፁሐን ዜጐች ላይ በከፈተው የሩምታ ተኩስ 16 ሰዎችን ሲገድል በርካቶችን አቁስሏል ከሆስፒታል ምንጮች እንደሰማሁት የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል ገዳዩ የፌደራል ፖሊሱ ከግድያው በኋላ ምንም እንኳን ቦታው ብዙ ወታደሮች የሚንቀሳቀሱበት አካባቢ ቢሆንም ከቦታው ሊያመልጥ ችሏል።አገዛዙን የተቃወመ ንፁሐን ዜጋ ሁሉ የሽብር ሴራ አከሸፍኩ እያለ የአሸባሪነት ታርጋ እየለጠፈ ወደ እስር የሚያወርደው የወያኔ መንግስት ጉያው ውስጥ ደብቆ ያቆየው የአገዛዙ የመንፈስ ልጅ አሸባሪ ሕዝብን ጨርሶ ሲያመልጥ “ስንት የሽብር ጥንስስ አከሸፈ” የተባለለት ፀረሽብር ግብረ ሀይል በቦታው የለም። ለነገሩ የወያኔ ደህንነት፥ወታደር፥ፀረሽብር ግብረ ሀይል፥ ፖሊስ፥ፌደራል ፖሊስ ገለመሌ አገዛዙን ከሕዝባዊ ማዕበል እንዲጠብቁ እንጅ የሕዝብን ደህንነት የሚጠብቁበት ስልጠናውም ልምዱም የላቸውም ።

ጽሁፉ ሙሉ በሙሉ ከነፎቶው የተወሰደው ከ “Addisu Wond” ላይ ነው።

በባህር ዳር የ12 ሰዎችን ህይወት ያጠፋው ግለሰብ አስክሬን ተገኘ

አዲስ አበባ ፣ግንቦት 5 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በባህር ዳር ከተማ ልዩ ስሙ አባይ ማዶ በተባለ አከባቢ ከትናንት በስቲያ አንድ ግለሰብ 12 ሰዎችን መግደሉ ይታወሳል፡፡ ከስፍራው የደረሰን መረጃ ግለሰቡ ሰክሮ እንደነበር ነው የሚያመለክተው።

የባህር ዳር ከተማ ፖሊስ ኮሚሽን መምሪያ ሀላፊ ኮማንደር ደረጀ አቻምየለህ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለፁት ፥ ግለሰቡ በውል ባልታወቀ ምክንያት በመንገድ ላይ በከፈተው ተኩስ ከሞቱት 12 ሰዎች በተጨማሪ ሌሎች ሁለት ሰዎች ክፉኛ ቆስለዋል።tpicture

በሰዓቱም ግለሰቡን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ክትትል ሲያደርግ እንደነበርና በመጨረሻም ራሱን በወንዝ ውስጥ በመወርወር መሰወሩን ገልፀው ነበር ። በአሁኑ ወቅት የግለሰቡ አሰክሬን በአባይ ወንዝ ውስጥ መገኘቱን ፖሊስ ገልጿል።

ድርጊቱን የፈፀመው ግለሰብ የፖሊስ አባል መሆኑን የገለፁት ኮማንደሩ ፥ ድርጊቱን የፈፀመበት ምክንያት ግለሰባዊ እንደሆነ አመልክተዋል ። ትናንት ምሽት 2 ሰዓት ከ45 ላይ በተፈፀመው ድርጊት ከሞቱት መካከል ሴቶች ፣ ህፃናትና አዛውንቶች ይገኙበታል ።ከተገደሉት ግለሰቦች መካከልም የሰባቱ የቀብር ስነ ስርዓት በደብረ አባይ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስትያን በጋራ ተፈፅሟል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት ግድያውን አስነዋሪ የጭካኔ ተግባር ሲል አውግዞታል ፤ ለሟች ቤተሰቦችም መፅናናትን ተመኝቷል:: በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት የአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ አያሌው ጎበዜም የክልሉ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለፅ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል ።

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ በግለሰቡ ድርጊት ህይወታቸውን ባጡ ዜጎች ህልፈት የተሰማውን ሀዘን ገልጿል፡፡ በእንዲዚህ አይነቱ ወንጀልም በህብረተሰቡና በፖሊስ መካከል ለዓመታት የቆየው መልካም ግንኙነትም አይሻክርም ብሏል በመግለጫው ፡፡

የፖሊስነት ሙያዊ ዲስፕሊን በጎደላቸው መሰል ፖሊሶችም ይህ አይነት ክስተት ደግም እንዳይፈጠር እንደሚሰራም ያለውን ቁጥርጠኝነት አረጋግጧል ፡፡

ፖሊስ በጉዳዩ ላይ እያደረገ ያለውን ምርመራ እንዳጠናቀቀም ተጨማሪ መረጃ እንደሚሰጥ ነው ያስታወቀው :: አዲስ አበባ፣ ግንቦት 5 (ኤፍ.ቢ.ሲ)

“በባህር ዳር ንጹሃንን የጨፈጨፈው ፖሊስ አማርኛ ተናጋሪ አይደለም”

በባህር ዳር የንጹሃንን ህይወት ያጠፋው የፌደራል ፖሊስ አባል አማርኛ ቋንቋ በደንብ መናገር የማይችል፣ የክልል አንድ ተወላጅ መሆኑንን የአካባቢው ነዋሪዎች ለጎልጉል በላኩት የጽሁፍ መልዕክት ገለጹ። በመልዕክቱ እንደተገለጸው ንጹሃኑን የገደለው ፖሊስ ርምጃውን የወሰደው ወደ ቤቱ በመሄድ መንግስት ያስታጠቀውን የጦር ጠመንጃ በማምጣት ነው።

ከመልዕክቱ ጋር ተያያዥነት ያለው ውይይት ሲያካሂድ የነበው ደብተራ ሊቅ የተባለ የፓልቶክ ክፍልም ተመሳሳይ መረጃ ሲሰጥ ለማዳመጥ ተችሏል። በዚሁ ክፍል ውስጥ ፖሊሱ ራሱን አባይ ወንዝ ውስጥ ወርውሮ አጠፋ መባሉ ሲያከራክር ነበር። በድረገጽ ዜናውን የሚከታተሉ ይሀንኑ መቀበል እንዳቃታቸውና አንድ ሰው ይህንን ያህል ሰው እስኪጨርስና ራሱን ገደል ወርውሮ እስኪጥል “ህግ አስከባሪዎች” የት ነበሩ? ሲሉ ጠይቀዋል። በሌሎች አገሮች እንደሚደረገው ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስቸኳይ የሃዘን መግለጫ ለጉዳተኛ ቤተሰቦች አለማድረሳቸውና ወንጀሉን ተከትሎ ሊወሰድ ስለሚችለው የመንግስት አቋም አለመናገራቸው አስገራሚ ሆኗል። ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ዘንድም እስካሁን የተባለ ነገር የለም።

ሦስት የደኅንነት መሥርያ ቤቶችን 180 ሚሊዮን ብር ያለመረጃ አጠፉ

የአገር መከላከያ ሚኒስቴር፣ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲና ሌሎች የብሔራዊ ደኅንነት ጉዳይ የሚመለከታቸው መሥርያ ቤቶች የበጀት አፈጻጸምን በጥልቀት ኦዲት ማድረግ የሚቻልበት ሕጋዊ አሠራር እየተጠና ነው፡፡

ባለፈው ሳምንት የ2004 ዓ.ም. የመንግሥት መሥርያ ቤቶች የበጀት አፈጻጸምና የሥራ ክንውን በመመርመር ሪፖርት ያቀረበው የፌደራሉ ዋና ኦዲተር፣ መከላከያ ሚኒስቴር 3.2 ቢሊዮን ብር ለምን ጉዳዮች ወጪ እንዳደረገ ምንም ዓይነት ማስረጃ ማግኘት አለመቻሉን ገልጿል፡፡insa ethiopia

የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲም በምንም ዓይነት መረጃ ያልተደገፈ የ180 ሚሊዮን ብር በ2004 ዓ.ም. ማውጣቱን ሪፖርቱ ይገልጻል፡፡ ሁለቱ መሥርያ ቤቶችና ሌሎች ተመሳሳይ የብሔራዊ ደኅንነት የሚመለከታቸው መሥርያ ቤቶች በተደጋጋሚ የሚወቀሱበትን በማስረጃ ያልተደገፉ በቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጪዎችን አባክነዋል ማለት እንደማይቻል ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡

ችግሩ የሚመነጨው እነዚህ መሥርያ ቤቶች ኦዲት የመደረግ ግዴታ ያለባቸው መሆኑና ኦዲት በሚደረጉበት ወቅት መረጃዎችን እንዴት ማቅረብ ይኖርባቸዋል በሚሉ ጉዳዮች ላይ ክፍተት በመኖሩ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ ያወጡትንdefense ወጪ በመረጃ በማስደገፍ ለዋና ኦዲተሩ ማቅረብ ማለት የብሔራዊ የደኅንነት ሚስጥሮችን ለሦስተኛ ወገን አሳልፎ መስጠት እንደሆነ የሚያስረዱት ባለሙያዎቹ፣ ይህንን ያገናዘበ አሠራር መኖር እንደሚገባው ያስረዳሉ፡፡

በዚህ የመረጃ ልውውጥ ወቅት ሚስጥሮች ቢባክኑ የሚጠየቅበት ሕግ ባለመኖሩ፣ የደኅንነት መሥርያ ቤቶቹ ኦዲት የመደረግ ግዴታቸውን ቢያንስ መረጃውን በመደበቅ እየተወጡ መሆኑን የሚያብራሩት እነዚሁ ባለሙያዎች፣ ይህንን ችግር መቅረፍ የሚቻልበት ዓለም አቀፍ አሠራርን ያገናዘበ ጥናት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ዋና ኦዲተሩ አቶ ገመቹ ዱቢሶም ይህንኑ ያረጋገጡ ሲሆን፣ የእሳቸው መሥርያ ቤት የሚመራውና ሌሎች አካላትን ያካተተ ኮሚቴ ጥናት እየደረገ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በቀጣዩ ዓመት ጥናቱ ተጠናቆና ረቂቅ ሕጉ ተዘጋጅቶ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚቀርብም አስረድተዋል፡፡  (ዘገባው የሪፖርተር ነው)

ደቡብ ሱዳንና ኢህአዴግ በጋራ ፓርክ መሰረቱ

የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክን ደቡብ ሱዳን ውስጥ ከሚገኘው ቦማ ፓርክ ጋር በማቀናጀት ወጥ በሆነ መንገድ ‹‹ቦማ ጋምቤላ ድንበር ተሻጋሪ ፓርክ›› ለመመሥረት እንቅስቃሴ መጀመሩን፣ የኢትዮጵያ የዱር እንስሳትና ልማት ጥበቃ ባለሥልጣን ማስታወቁን ሪፖርተር አስታወቀ። ሪፖርተር ባይገልጸውም ውሳኔው ስጋት የፈጠረው እንደሆነ ተመልክቷል።

በሁለቱ አገሮች ስምምነት በሚመሠረተው ኩታ ገጠም የጋራ ፓርክ በየዓመቱ ከአንዱ ፓርክ ወደ ሌላኛው ፓርክ የሚደረገውን የዱር እንስሳት ወቅታዊ ፍልሰት ለቱሪስቶች ተደራሽ በማድረግ ጠቀም ያለ ገንዘብ ለማግኘት ታቅዷል፡፡

በጋምቤላ ክልል የነጭ ጆሮ ቆርኪና ናይል ለችዌናን ጨምሮ በርካታ የዱር እንስሳት ይገኛሉ፡፡ በተለይ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ነጭ ጆሮ ቆርኪዎች እንደየወቅቱ ሁኔታ በአንድ ጊዜ በርካታ ቡድኖችን እየፈጠሩ ወደ ደቡብ ሱዳን ቦማ ፓርክ ይጓዛሉ፡፡ ከቦማ ፓርክም ጊዜ ጠብቀው ወደ ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ ይመለሳሉ፡፡

haile kirrበኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ይህ የእንስሳት ፍልሰት እንዳለ ቢታወቅም፣ ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ ጥናት ተሠርቶ ስትራቴጂ ያልወጣለት በመሆኑ፣ የእንስሳቱ ጉዞ በኬንያና በታንዛኒያ መካከል እንደሚገኘው ሰረንጌቲ ፓርክ ለቱሪስቶች ተደራሽ ሳይሆን ቆይቷል፡፡

ባለሥልጣኑ ይህንን ሁኔታ በመቀየር በዘርፉ አንዳች ለውጥ ለማምጣት የሚያስችለውን ጥናት ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር እያካሄደ ይገኛል፡፡ የተካሄደው ጥናት ባይጠናቀቅም ፍልሰት መኖሩ በመረጋገጡ እንስሳቱ የሚፈልሱባቸውን ኮሪደሮችና የሚያቋርጧቸውን ወንዞች ለመለየት ለቱሪስት ግልጋሎት የሚሰጡ፣ ሎጆችና የመሳሰሉት መሠረተ ልማቶች እንዲሟሉ ይደረጋል ሲሉ የባለሥልጣኑ የኅብረተሰብ ባለሙያ አቶ ቸሬ ናውጋ ገልጸዋል፡፡

ጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ በ1966 ዓ.ም. ነው የተመሠረተው፡፡ ፓርኩ በአጠቃላይ 5,061 ካሬ ኪሎ ሜትር ስፋት አለው፡፡ ፓርኩ ከአዲስ አበባ 777 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ የጋምቤላ ብሔራዊ ፓርክ ከሰው ንክኪ ነፃ በመሆኑ በውስጡ ብዛት ያላቸው የዱር እንስሳት ይገኙበታል፡፡

የዱር እንስሳቱ የፍልሰት ሁኔታ ከተጠና በኋላ ፕሮጀክቱ ወዲያውኑ ወደትግበራ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ ከሰረንጌቲ ፓርክ በዓመት 100 ሚሊዮን ዶላር የሚገኝ ሲሆን፣ ከቦማ ጋምቤላ ድንበር ተሻጋሪ ፓርክም ይህን ያህል ገንዘብ የማይገኝበት ምክንያት የለም በሚል የባለሥልጣኑ ማኅበረሰብ በመንቀሳቀስ ላይ ነው፡፡ይህንኑ ፕሮጀክት እውን ለማድረግ ባለሥልጣኑ ከደቡብ ሱዳን አቻው ጋር በመጪው ሐምሌ አዲስ አበባ ላይ ስብሰባ እንደሚቀመጥ ግለጻ የዘገበው ሪፖረተር ነው። ስምምነቱ በአካባቢው ደን ውስጥ ይንቀሳቀሳሉ የሚባሉ ክፍሎችን ለመቆጣጠርና ምናልባትም ወደፊት ፈታኝ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል ከሚል ስጋት የተነሳ እንደሆነ ከግምት በላይ የሚናገሩ አሉ።

የፍትህ ሚኒስትሩ መባረር በይፋ መንስዔ በይፋ አልታወቀም

ፎርቹን የተሰኘው የእንግሊዝኛ ጋዜጣ ለንባብ ያበቃው ዜና እንደሚለው አቶ ብርሃን ሃይሉ ከፍትህ ሚኒስትርነታቸው የተባረሩት በብቃት ማነስ ነው። የማስታወቂያ ሚኒስትር ሲፈርስ ወደ ፍትህ ሚኒስትርነት የተሸጋገሩት አቶ ብርሃን ቀደም ሲል ድርጅታቸው ብአዴን ከነበራቸው የፓርቲ ሃላፊነት አንስቷቸው እንደነበር አመልክቷል። ፎርቹንን ጨምሮ የተለያዩ መገናኛዎች የህንን ቢሉም ዋናው የመባረሪያቸው ምክንያት ሚስጥር መደረጉን የሚናገሩ አሉ።

Brehan-Hailu
ብርሃን ሃይሉ (ፎቶ Fortune Addis)

አቶ ብረሃን ግንቦት 1 ቀን 2005 ዓ ም የመስሪያ ቤታቸውን የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት አቅርበው ነበር። ሪፖርትር እንዳለው የተወካዮች ምክር ቤት የህግ ቋሚ ኮሚቴ የሚኒስትሩን ሪፖርት አልወደደላቸው ነበር። ከአቶ መለስ ጀርባ ጥቁር መነጽር በማድረግ በመቀመጣቸው የሚታወቁት የኮሚቴው ሰብሳቢ ከሪፖርቱ በሁዋላ እሳቸው የሚመሩት መስሪያ ቤት መፋዘዙን ነግረዋቸው ነበር።

ሪፖርትር ምንጮቼ ጠቁመውኛል በማለት እንደገለጸው አቶ ብርሃን ሪፖርታቸውን ባቀረቡበት እለት ነው አቶ ሃይለማርያም የ” በቃዎት” ደብዳቤ የላኩላቸው። አቶ ብርሃን በቀጣይ የት እንደሚመደቡ ለጊዜው አልተገለጸም። በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ከታሰሩት ባለስልጣነት ጋር ግንኙነት ይኑራቸው አይኑራቸው እስካሁን  የተባለ ነገር የለም።ሚኒስትሩ በአቅም ችግር ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ ይታሙ ነበር።

አቶ ብርሃን ቀድሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ ከነበሩትና አሁን በኢህአዴግ ጽ/ቤት ውስጥ እንዲቀመጡ ከተደረጉት አቶ ብርሃኑ አዴሎ ጋር የስራ ግንኙነት እንደነበራቸው የሚያውቁ ተናግረዋል። አቶ ብርሃኑ አዴሎ ከሙስና ጋር በተያያዘ በከፍተኛ ደራጃ ክስ  የሚቀርብባቸው ባለስልጣን ነበሩ። አቶ ብርሃኑ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት ሃላፊ እያሉ አሁን በቁጥጥር ስር ከዋሉት ባለስልጣናት ጋር የታክስ ቅነሳና የቀረጥ ነጻ ደብዳቤ ለሚታወቁ ባለሃብቶች በመጻፍ የሚታወቁ ባለስልጣን ናቸው። አቶ ብርሃኑ በዶ/ር አሸብር ወ/ጊዮርጊስ ተሸንፈው ከፓርላማ የተወገዱ ብቸኛው የክልል የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለስልጣን ናቸው። በወቅቱ ደ/ር አሸብር በሚያሳትሙት “ቻሌንጅ” ጋዜጣ አቶ ብርሃኑ አዴሎን ገበና በስፋት አጋልጠው እንደነበር አይዘነጋም። ዶክተሩ አሁን ብቸኛ የግል ተወዳዳሪ የፓርላማ አባል ቢሆኑም በተደጋጋሚ ኢህአዴግን እንደሚደግፉ በመግለጽ ይታወቃሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule