• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ገቢ የማያስገኙ የዜና ርዕሶች

July 17, 2022 05:36 pm by Editor 2 Comments

የማኅበራዊ ሚዲያ ሰለባዎች ዓይነታቸው ብዙ ነው። ልጆቻቸው የማኅበራዊ ሚዲያ ተግዳሮቶችን (ቻሌንጅ) በመውሰድ እልህ ውስጥ ገብተው የሞቱባቸው ጥቂቶች አይደሉም። “Blackout Challenge” የተሰኘው የቲክቶክ ተግዳሮት ፉክክር ውስጥ የገቡ ሕጻናትና ወጣቶች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ሌሎች ጥቂት የማይባሉ ደግሞ የማኅበራዊ ሚዲያ ሱሰኛ ሆነው ሕይወታቸው የተበላሸ አሉ። የተጎጂው ቁጥር ሥፍር የለውም፤ የማኅበራዊ ሚዲያ አውታሮቹን የሚከስሱ ወላጆች ቁጥርም እንዲሁ እጅግ በርካታዎች ናቸው።

በማኅበራዊ ሚዲያ ዘገባ ምክንያት ሕይወታቸውን ከሚያጡት በተጓዳኝ አገራቸውንም እያጡ ያሉ ጥቂቶች አይደሉም። የዛሬ ስድስት ዓመት በቱርክ የተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት ሤራ የማክሸፍ ሥራ ላይ የማኅበራዊ ሚዲያ ትልቅ አስተዋጽዖ አለው። አገር ወዳድ ቱርካውያን የወሬ ሰለባ አንሆንም ብለው አገራቸውን ሲያድኑ ሤራው የተካሄደባቸው ፕሬዚዳንት ረሲፕ ኤርዶጋን ሤራውን ለማክሸፍ ስልካቸውንና ማኅበራዊ ሚዲያን መጠቀማቸው በዋናነት የሚጠቀስ ነው።

ከላይ እንደተባለው የማኅበራዊ ሚዲያ ሰለባዎች ሕይወታቸውን እስከማጣት የደረሱ ናቸው። ሌሎች ደግሞ አሉ ዓይናቸው እስኪያብጥ፣ ጆሮአቸው እስኪደማ የወሬ ሱስ ሰለባ የሆኑ። ጠዋት ሲነሱ (ተኝተው ካደሩ) “ዛሬ ምን አለ?” ብለው እንደ ነገረኛ ሰው በወሬ ቀናቸውን የሚጀምሩ። እነዚሀ ሰዎች ከጠዋቱ የመጸዳዳት ተግባራቸው በፊት በዜና ስም የሚለጠፍ ተራ ወሬና የመንደር አሉባልታ እንዲጸዳዳባቸው ራሳቸውን በፈቃዳቸው አሳልፈው የሰጡ ከንቱዎች ናቸው።

ከዚህ ዓይነት የቀን ጅማሮ በኋላ እንዲህ ዓይነቱ ሰው በልቡ ማኅደር ያለውም ሆነ ቀኑን ሙሉ ከአፉ የሚወጣው ጽድቅ ሳይሆን ርኩሰት፣ ነውር፣ ብልግና እና ውርደት ነው። ልቡን ለክፋትና ርኩሰት ባዘጋጀበት መጠን ቀኑን ሙሉ እያነፈነፈ አእምሮውን የሚሞላው ይህንን እየቀመሙ በሚግቱት ግጭት ጠማቂዎች፤ ክፋት ጠንሳሾችና አእምሮአቸው የላሸቀ የጭንቅላት ጉዳተኞች የወሬ መርዝ ነው። ከንጋት ጀምሮ ወደ ውስጡ ባስገባው መርዝ መጠን እርሱም በየፊናው መርዙን ሲተፋ ይውላል። ይህንን በማስፈጸም ማኅበራዊ ሚዲያ የተዋጣለት መሣሪያ ነው።

ባለፉት ሁለት ሦስት ቀናት በአገራችን መልካም የሚባሉ ሥራዎች ተከስተዋል። በወለጋ የተጨፈጨፉትን ወገኖቻችን ልባችንን እያደማ ሌቦችን ወደሚገባቸው ቦታ ማስገባት ወሳኝ ሥራ ሆኖ ተስተውሏል። መከላከያም ከሸኔ ጋር ሲፋለም፣ ሠልጣኞችን ሲያስመርቅና ሌሎች ለአገር ግንባታ ወሳኝ የሆኑ ተግባራትን ሲፈጽም ነው የሰነበተው።

በተለይ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ የተሰገሰጉ ሌቦች በቁጥጥር ሥር የዋሉበት ያለፉት ሁለት/ሦስት ቀናት የሁሉም ትኩረት ተመሳሳይ ተግባራት በሁሉም የሥልጣን ተዋረድ ይቀጥል የሚል ነበር። በኮንዶሚኒየምም ሆነ በዕርዳታ ጉዳይ ሕዝብን ከመዝረፍ አልፈው የትህነግን የፖለቲካ ዓላማ ለማሳካት የተቀናጀ ሤራ ሲፈጽሙ የነበሩ በተያዙ ቀን እየተናበቡ የሚሠሩት አጀንዳ ሰጪዎቻችን የወሬአቸው ቀዳሚ ዜና ያደረጉትን ጉዳይ ምን እንደነበር መመልከቱ ከማኅበራዊ ሚዲያ ሱስ ለመላቀቅ ዓይን ከፋች ነው።

የትህነግና የግብጽ ልሳን የሆነው 360 ዋና ርዕስ ያደረገው ይህንን ነው፤

የአማራ ተቆርቋሪ ነኝ የሚለው የቀድሞው እስክስታ ወራጅና የዳዊት ወልደጊዮርጊስ አጋፋሪ አበበ በለው ደግሞ ይህንን ነው ቀዳሚ መረጃ አድርጎ ያቀረበው፤

በአስከፊው የትህነግ የግፍ ዘመን የመዝናኛ ፕሮግራም ያዘጋጅ የነበረው ማየት የተሳነው ቴዎድሮስ ጸጋዬ በማኅበራዊ ሚዲያው ጠጅ ለሚያሰክራቸው ተከታታዮቹ ይህንን ነው ርዕሰ ጉዳዩ ያደረገው፤

ሲሻው ቀዳሽ ዲያቆን፣ ሲሻው አራጅ ወያኔ፣ ሲሻው ወታደር፣ ሲሻው ደግሞ የሚዲያና ፖለቲካ ተንታኝ የሆነው ለ360ውም የዩትዩብ ጡረተኞች የዕለቱን አጀንዳ የሚሰጣቸው ስታሊን ደግሞ ዋና አጀንዳው ይህ ነበር፤

እነዚህ እየተናበቡ አገር በማፍረስ አጀንዳ ላይ የተሰማሩ፤ የየዋሆችን ልብ ለመስለብ ኢትዮጵያዊ ስምና ሠንደቅ ከፊት ለፊታቸው የሚያደርጉ፤ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር” እያሉ የሚምሉ የኮንዶሚኒየም ሌቦች ሤራ በተጋለጠበትና፤ ከረሃብተኛ የዕርዳታ እህልና ገንዘብ እየነጠቀ ራሱን ሲያበለጽግ የነበረው ምትኩ በተያዘበት ዕለት ለእነርሱ ይህ ለዐቅመ አጀንዳ የደረሰ፤ ለትንታኔ የበቃ ጉዳይ አልነበረም። እንደ እውነቱ ከሆነ ብቁ ሳይሆን ቀርቶ አይደለም። ያልተጠበቀው ኩነት በተከታታይ ያቀዱትን አጀንዳ የእንቧይ ካብ ስላደረገባቸው ነው። ከእነዚህ ግን የተለየ ሌላ በወገኖቹ ደም የሚሸቅጥ አለ …   

በአምላክ ስም አማትቦ ጀምሮ የጥላቻ ቃላትን በመትፋት ሰይጣንን የሚያስንቀው፤ አእምሮው የተቃወሰ መሆኑን በራሱ አንደበት የመሰከረው ዘመድኩን በቀለ ደግሞ ሰሞኑን ሁሉ “አጀንዳዬን አልቀይርም”፤ “ኑ ለቅሶ እንድረስ” እያለ በወለጋ ወገኖቻችን ጭፍጨፋ ላይ ሲነግድ ነበር የከረመው። በዚህ የደም ንግድ ብዙዎችን አንዴ ጥቁር ሲያስለብስ፤ አንዴ ሲያስለቅስ ከከረመ በኋላ እንደለመደው “(የስድብ) አገልግሎቴን በዚህ ደግፉ” ብሎ ለአንድ ሳምንት እንደማይኖር መረጃ ሰጥጦ ተሰናብቷል። ቆፈናሙ የጀርመን ብርድ ሳይገባ ፈታ፣ ላላ፣ ዘና ልበል፤ ከቤተሰቦቼ ጋር ልዝናናበት ተውኝ ብሎ አጀንዳውን ቀይሯል። አስለቅሶ፣ “ለአገልግሎቱ” መደጎሚያ ብሩን ሰብስቦ፣ አልቀይርም ያለውን አጀንዳ ቀይሮ ለሳምንት ተሰናብቷል።

ዘመድኩን እንደምክንያት የሰጠው የጀርመን መንግሥት በ9 ዩሮ ተዝናኑ ብሎናል የሚል ነው። ምነው ያ ሁሉ አማራ ተጨፍጭፎ ገና ደሙ ሳይደርቅ አንተ እንዴት አጀንዳ ለመቀየር አንጀትህ አስቻለህ? ብሎ የሚጠይቅ የለም። እንዴት በቀን 90 ጊዜ ትህነግና እነ ጃል መሮ የሚልኩልህን ፎቶ “የአማራ ደም” እያልህ እየለጠፍህ በአስከሬን ሳንቲም ስትሰበስብ እንዳልቆየህ አሁን ለመዝናናት ልብህ እሺ አለ? ብሎ የሚሞግት የለም። እኛን በየቀኑ “አጀንዳዬን አልቀይርም” ስትለን ቆይተህ ለምን እና እንዴት አጀንዳህን ለመቀየር ደፈርህ? የጀርመን መንግሥት በግድ ተዝናኑ፤ ካልተዝናናችሁ ትቀጣላችሁ አላለም፤ ምነው አንተ መዝናናቱን ግዴታ አደረግኸው? በተለይ እንዳንተ ዓይነቱ “አጀንዳዬን አልቀይርም” ባይ ምነው ለጀርመን መንግሥት “አይ እኔ ለቅሶ ላይ ነኝ፤ ሐዘን ላይ ተቀምጫለሁ፤ አልዝናናም፤ ተውኝ ላልቅስበት” ማለት አቃተው? በማለት ከተከታዮቹ የሚሞግት የለም። ምክንያቱም የአእምሮ መላሸቅ ሰለባ ስለሆኑ እውነቱ ውሸት፤ ውሸቱ እውነት ሆኖባቸዋል። በአደንዛዥ ዕፅ እንደሚደነዝዝ ሰው በወሬ ድግምግሞሽ ማሰብ እስከሚሳናቸው ደንዝዘዋል።   

በአሁኑ ሰዓት ከድምጺ ወያኔ፣ 360፣ TMH፣ ርዕዮት፣ ኢትዮ ፎረም ወዘተ እኩል ትግራይ ከሚሰሙ መካከል አንዱ ዘመድኩን በቀለ ሆኗል። ትህነግ ደጋፊህ ሆኖ ለሕዝቡ እንድትሰማ ሲፈቅድልህ በመናገር ነጻነት ስላመነ ሳይሆን ከድምጺ ወያኔ እኩል ካድሬውና አጀንዳውን ፈጻሚ ምርጥ ወያኔ ስለሆንህለት ነው። ትህነግ ማለት አማራ ጠላታችን ነው፤ አማራን ማዋረድ፣ መግደል፣ መጨፍጨፍ፣ ማፈናቀል፣ መቅኖቢስ ማድረግ አለብን የሚለው ማለት ነው። የወልቃይትን ሕዝብ ከምድረገጽ ለማጥፋት ለ30 ዓመት የሞከረውና አሁን በቅርቡ ደግሞ አማራ ክልል መጥቶ ሒሳብ አወራርዳለሁ ባለው መሠረት የክልሉን መሠረተ ልማት አውድሞና ሊጥ ጠጥቶ የተባረረው ትህነግ ዘመድኩን በቀለ በሮማኖት አደባባይ መቀሌ ላይ እንዲሰማ ፈቅዷል። መረጃው እነሆ! (ምንጭ፤ Melke Ethio Habesha)

ትህነግ ሲያበሰብስ እንዲህ ነው። በአንድ በኩል ወዳጅ መስሎ ግፋ በለው፤ አብሬህ ነኝ ይላል። በሌላው ደግሞ የትህነግ ደጋፊ መሆንህን ለዓለም ያሳውቅብሃል። ዘመድኩን መቀሌ ላይ ሲደመጥ ቀድተው የላኩት ማንም ሳይሆኑ የትህነግ ካድሬዎች ናቸው። ዘመድኩን ተጠቁሯል፤ አጀንዳው የትህነግ አጀንዳ ነው። የፈለገ ቢያማትብ፣ ቅዱሳት መጻሕፍትን ቢያውቅና ቢመረምር ቢያገላብጥ ዘመድኩን በቀለ የሚያራምደው አጀንዳ ከትህነግ አጀንዳ ጋር የሚመሳሰል ነው።

ከመግቢያው ላይ የተጠቀሱት የኮንዶሚኒየም ሌቦች እና የዕርዳታ ማስተባበሪያ አመራር መያዝ ገቢ የሚያስገኙ የዜና ርዕሶች አይደሉም። ሥርዓት ለማፍረስ የሚጠቅሙ የዜና ርዕሶችም አይደሉም። የዩትዩብ ተመልካች የሚስቡ አይደሉም። መንጋውን ለመመገብ የሚጠቅሙ የወሬ ምግቦች አይደሉም። ተጨፈጨፈ፣ ተገደለ፣ ተሰደደ፣ … የሚሉት ናቸው ገቢ የሚያስገኙ የዜና ዘገባዎች። ይህንን የሚያውቁት ሸቃጮች ደግሞ መዘገብ ያለበትን ሳይሆን ኪሳቸውን የሚያደልብላቸውን እና መንጋውን እንደፈለጉ የሚነዱበትን ነው ቀን ተሌት የሚያወሩት። ታላቁ መጽሐፍ እንደሚለው “በድን ወዳለበት በዚያ አሞሮች ይሰበሰባሉ”።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Politics Tagged With: Abebe Belew, ermias legesse, Ethio 360, habtamu ayalew, Mereja TV, operation dismantle tplf, Stalin, Tewodros Tsegaye, Zemedie, zemedkun bekele

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfa says

    July 18, 2022 10:44 am at 10:44 am

    ዓለሙ ሁሉ ገምቷል የምለው ለዚህ ነው። በፈጠራ ወሬ ሰውን ማበራየት የተለመደ የንግድ ዓርማ ሆኖአል። ሲጀመር ያለምንም መረጃ ሽመልስ አብዲሳ እንዲህ አደረገ፤ ከንቲባዋ ይህን ሰራች፤ ዶ/ር አብይ ኦነግ ነው አይኑና ጆሮው እያየ እየሰማ ነው ሰውን የሚያስጨርሰው ኸረ ስንቱ ወዘተ የሚለፉ አክራሪ ብሄርተኞችና የወያኔ ተከፋዪች ቅንጣት ያህል መረጃ በሚያላዝኑት ጉዳይ ማቅረብ አይችሉም። አንድ አንድ ደግሞ ለይቶለት አብዶ የባለስልጣን ወላጆችን እስከ መሳደብና ተራ ዘለፋ ስድፍ እስከ መለጠፍ ደርሰዋል።
    በቅድሚያ የእኔ እይታ አቶ ሽመልስ አብዲሳም ሆነ ሌሎች ባለስልጣኖች ሆን ብለው ሰው በጅምላ ያስገድላሉ ብዬ አላምንም። ዶ/ር አብይም ሃገሩን የሚወድ በወስላታና በተመሰቃቀለ ህዝብ መካከል የቆመ ቅሚያና ዝርፊያን የሚጠላ ሰው ነው። ይህ ሲባል ባለስልጣን የሆኑ ሁሉ ለበጎ ተሰልፈዋል ማለት አይደለም። ብሄር ያሰከራቸው ቀን ተደምረው ማታ በመቀነስ ሃገር የሚያፈርሱ እንዳሉም መገመት ይቻላል። ይህ ደግሞ ፓለቲካ ነው። ስንዴን ከንክርዳድ ማበጠር የስለላ መረቡ ሥራ ነው። ይህን በፌስቡክ ጽፈሃል፤ ያን ተናግረሃል፤ ይህን አቁመህ ያን ንደሃል እያሉ ሰውን በየሰበቡ ማፈንና ገርፎና ያላቸውን ዘርፎ መልቀቅም የመንግስትን ባህሪ አያሳይም። ሊቆም ይገባዋል። መሆን ያለበት ለጻፉት፤ ለሚናገሩት ሁሉ መረጃ እንዲያቀርቡ መጠየቅ እንጂ “ወታደራዊ ሚስጢር ” አውጥተሃል በማለት እንደ ተመስገን ደሳለኝ ያሉ እውቅ ጋዜጠኞችን ማሰር ራስን ወንጀለኛ ማድረግ ነው። ገጣሚው ይግጠም። ጸሃፊው ይጻፍ፤ ለፍላፊው ይለፍልፍ። ህዝብ ይመዝነው። እውነት ያለውን ነገር እንማርበታለን፤ ሌላው ደግሞ መጣያ ሥፍራ ከተገኘ ቆሼ ወስዶ ማራገፍ ነው። ካልሆነ ስንቱ ታስሮ፤ ስንቱን አስፈራርቶ ይዘለቃል? ስንት የሚሰራ ጉዳይ እያለ በሃገራቸው አንድነት በምንም ሂሳብ የማይደራደሩትን ወገኖቻችን ስናሳድድ እንኖራለን?
    ማህበራዊ ሚዲያ ማለት መርካቶ ገቢያ ማለት ነው። ሌባው፤ ጤነኛውም የሚጋፋበት የእኔ አውራ ጣት ካንተ ይበልጣል የሚባባልበት የገቢያ መሃከል ነው። እዚያ ውስጥ ስለ ፓለቲካ የተለጠፈ ነገር አንብቦ ደሙ የሚፈላ ወይም በትካዜ ልቡ የሚሰበር ሰው ሁሉ ብኩን ነው። የኢንተርኔት አገልግሎት 99% በውሸትና ለሰው ልጆች ጥቅም በሌለው ነገር የተሞላ ነው። ማህበራዊ ሚዲያ ሲባል ራሱ ስሙ ቁጭ ብሎ ሰው ሰንበቴ እየጠጣ የሚጫወት ያስመስሉታል። አይደለም። የወሮበሎች ጉድጓድ ነው። እልፍ ተከታይ አለኝ ይላል አንድ ተነስቶ። እኔ የማንም ተከታይ መሆን አልፈልግም። ተከትለህ የት ነው የምትደርሰው የሰው ገቢያ ከማድመቅ በስተቀር። የአሜሪካ ሜጋ ቸርቾችና ማህበራዊ ሚዲያ ተመሳሳይነት አላቸው። ገቢያቸውን እንጂ ተከታዪቻቸውን አያውቁም። ከላይ በድህረ ገጽ ላይ ለናሙና የተለጠፉት ሁሉ አሰልቺዎችና አጋናኝ ወረኛ ሰዎች ናቸው። ከመሰረቱ (Default position) የወሰድ ግለሰቦችና የሚዲያ አናፋሾች በመሆናቸው ምንም አይነት መረጃ ቢቀርብላቸው ሃሳባቸውን የመለወጥ ተስፋ የላቸውም። የሚገርመው ግን ሁሉም ባይሆኑ ጥቂት የማይባሉት ለኢትዮጵያ ህዝብ አንድነትና ሰላም ቆመናል ይሉናል። ተግባራቸው ግን ሰው ከሰው ጋር የሚያጋጭ፤ የመንግስትን አመራር ያለ ምንም ተጨባጭ መረጃ የሚወነጅል ለሃገርና ለወገን ሲፋለሙ የቆሰሉ ሰዎችን የሚያጥላላ ወይም የሚያለያይ ብቻ በስማ በለው ሰምተው በስማ በለው ነገር የሚነዙ ቱልቱላዎች ናቸው። መንግስት ሥራውን እንዲሰራና በሰራው በጎ ነገር እንዲመሰገን ባልሰራው እንዲጠይቅ ለማድረግ የጅምላና የነሲብ ኩነናን ማቆም ያስፈልጋል። እንዴት ጠ/ሚሩ ሰው እያለቀ የስንዴ ማሳ ይጎበኛል? እንዴት ችግኝ ተከላ ይውላል? የሚሉን በውጭና በውስጥ ያሉ የሙታን ስብስቦች ውጊያው ከድህነት፤ ከአየር ንብረት ለውጥ እንዲሁም ከወያኔና ወያኔ እየከፈለም ሆነ እያስፈራራ ካሰለፋቸው የዘርና የውጭ ጉዳይ አስፈጻሚ ተላላኪዎች ጋር ነው። በአንድ እጅ ጠበንጃ በሌላው አካፋን ዶማ ይዘን ካልሰራን ችግራችን ይሰፋል እንጂ አይከስምም። እንዴት በፓርላማ የህሊና ጸሎት ሳይደረግ ቀረ ብለው ቡራ ከረዪ ላሉ ተደረገ አልተደረገ ለሟችና ለተፈናቃይ የሚያመጣው ምን ጥቅም አለ? ህሊና በጎደለው ህብረተሰብ መካከል የህሊና ጸሎት ለራስ ነው ወይስ ለሞቱት? ግን ጉዳዪ ቁርሾ መወጫና ነገር መፈለጊያ ስለሆነ ሰው ይንጫጫበታል።
    በማጠቃለያው ፓለቲካ ጥልፍልፍ ነው። በኢትዮጵያ ላይ የተጫነው የውጭና የሃገር ውስጥ ጫና የምናውቀው ቅንጣት ያህሉን ብቻ ነው። መንግስቱን በሴራ ያባረሩትና ወያኔን በአዲስ አበባ ሻቢያን በአስመራ ያስቀመጡት እነዚያ ሃይሎች ዛሬም ሊያተራምሱን እየሰሩ ነው። በቅርቡ ወደ ጀዳ ተጉዘው የሳውዲዊን ገዳይ ሰው በጭብጥ እጅ ሰላምታ የተገናኙት የአሜሪካው መሪ እንዴት እንዲህ ያደርጋሉ ተብሎ በብዙ እየተዘለፉ ነው። የእኔ እይታ ግን የሳውዲው ሰው ቆራጭ ለአሜሪካ ያለውን (Disdain) ያሳያል እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም። አሜሪካ በሳውዲ በፊት እንደነበራት ፓለቲካዊ ጫና የማድረግ ሃይል የላትም። እንዲህ ነው እንግዲህ የዓለም ፓለቲካ። የእኛው የጭቃና የጥላሽት መቀባባት ፓለቲካም ትርፍ አልባ ሰውን ከሰው የሚያላትም (Devoid of the truth) መኖሪያ ፍለጋ ለፍጆታ የሚቀርብ የእንክርዳድ ክምር ነው። ልብ ያለው ያስተውል። ጀሮ ያለው ይስማ። በቃኝ!

    Reply
  2. fasil says

    August 8, 2022 06:13 am at 6:13 am

    ewunetu siwetta taleqaqsalachu

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule