• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የተረሳው የኢሬቻ ግፍና ከህወሓት ጋር የተዘለቀው ፍቅር እሽሩሩ

October 4, 2020 11:08 am by Editor Leave a Comment

የዛሬ አራት ዓመት የኢሬቻን በዓል ለማክበር በወጣው ሕዝብ ላይ ያኔ ምኒልክ ቤተመንግሥት የነበረው አሁን መቀሌ ሆቴል የመሸገው ሕወሓት የተሰኘው የበረኻ ወንበዴዎች ቡድን ያደረሰው እጅግ ሰቅጣጭ ግፍ ፈጽሞ የሚዘነጋ አይደለም።

ዓመት ባለፈ ቁጥር ይህንን የግፍ ናዳ ስናስብ ተመሳሳይ ዕልቂት በአገራችን እንዲፈጸም የሚሹ የዚህ ዓመቱን ኢሬቻ ክብረበዓል በሰላም መጠናቀቁን በፍጹም የፈለጉት አልነበረም። ሆኖም ፍጹም ሰላም በሰፈነበት መልኩ በዓሉ ተጠናቅቋ።

ዓመታት አልፈው ያኔ የደረሰውን ግፍ ዘንግተው፤ ለኦሮሞ እንታገላለን የሚሉ ከህወሓት ጋር “ፍቅር እሹሩሩ” ማለታቸው ሕዝብን መናቅና መስደብ ብቻ ሳይሆን በቁሙ መግደልም ነው።

ከሁሉ በላይ ለኦሮሞ ሕዝብ እታገላለሁ የሚለው በቀለ ገርባ ህወሓት ያደረሰበት ግፍና ስቅየት (ቶርቸር) ረስቶ መቀሌ በመሄድ ከህወሓት ሹሞች ጋር ስብሰባ መቀመጡ ሳያንስ ስላሳለፈው ዘመን ሲጠየቅ “ህወሓት (እንኳን ቶርቸር ሊያደርገኝ አይደለም) ዝንቤን እንኳን እሽ አላለም” ሲል መደመጡ አሁን ያለበት ቦታ የሚንሰው ነው ያሰኛል።

ለማንኛውም ለትውስት፣ ለኅሊና ፍርድ፣ ሰከን ብሎ ለማሰብ ያመች ዘንድ የዛሬ አራት ዓመት “በሕዝብ አቆጣጠር አሁን ሁሉም ነገር አበቃ” በሚል ርዕስ ያወጣነውን አሁን ደግመን አትመነዋል።       

በሕዝብ አቆጣጠር አሁን ሁሉም ነገር አበቃ

ዛሬ ጨለሞ ዋለ። ዛሬ አገር ማቅ ለበሰች። ዛሬ የሆነውን ማመን ይከብዳል። ቄጤማና ቅጠል ይዘው የወጡ ሰላማዊ ዜጎች በጅምላ ተረሸኑ። “Down! Down! Woyane … Down! Down TPLF! …” በማለት ቁጣውን የገለጸ ሕዝብ እገዛሃለሁ በሚለው የትግራይ ህዝብ ተገንጣይ ቡድን (በህወሃት) ተጨፈጨፈ። ከአየርና ከምድር ጭስና ጥይት የተረጨበት ህዝብ፣ የሚገባበት ጠፍቶት የውሃ ራት ሆነ። ሞተ። ቆሰለ። በውሃ ተበላ።

irreecha53
“Down! Down! Woyane … Down! Down TPLF! …” የሚለውን ቀስቃሽ ንግግር ያደረገው ወጣት

የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላት የሚባለው የወንበዴው ቡድን መሪ መለስ ሞት በድንገት እንደ ቡሽ ክዳን አፈናጥሮ ሲወስደው ጥቁር ለበሶ ሳግ እየተናነቀው ዜና ያወጀው ተመስገን በየነ፣ ዛሬ ነጭ በነጭ ለብሶ አኻዝ ባይጠቅስም የሰው ህይወት ማለፉን የተናገረው “ሰፊውና የተከበረው የኦሮሞ ህዝብ” በማለት ነበር።

ተመስገን ከጌታቸው የተላከለትን ሰዎች “በመረጋገጥ” ሞታቸውን ሲተፋ ቢያመሽም ህወሃትና ወኪሎቻቸው የዘነጉት ነገር ቢኖር የኢሬቻ በዓል ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ዛሬ አይደለም፤ እስካሁን በተደረገው የበዓሉ አከባበርም ሁከት ሲነሳና ሰዎች በመረጋገት ሲሞቱ አልተሰማም፡፡

ብዙዎች እንዳሉትና፣ በማህበራዊ ገጾች እንደታየው ከኖረው ሃዘን ጋር ተዳምሮ የዛሬው ሃዘን በሕዝብ አቆጣጠር ሁሉም ነገር መጠናቀቁን ነው፡፡

የማህበራዊ ድረ ገጾች ምስል አስደግፈው እንዳሰራጩት ዜናና የውጭ መገናኛዎች እንዳሉት ቢሾፍቱ የኢሬቻን በአል ለማክበር የተሰባሰቡት ዜጎች ብዛት እስከ አራት ሚሊዮን ተገምቷል። ቢቢሲ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሲል ሌሎች ከዚያም ያስበልጡታል።

እንግዲህ እዚህ ህዝብ መሃል ነበር መርዝ የተተኮሰው። ጭስ የተተኮሰው። ህዝብ አየር አጥቶ እንዲታፈን የተፈረደው። ከዚያም በላይ ከባድ መሳሪያ ሲተኮስ የተቀረጹት ፊልሞች አረጋግጠዋል። ታንክ ሲጠቀሙም በምስል ተይዟል። በአየር ላይም ሄሊኮፕተር ተባባሪ ነበር።

ይህ ሁሉ የመሳሪያ አይነት የተሰለፈው ለወገን መሆኑ አገርን በድፍን አሳዝኗል። በዚህ ሁሉ ዝግጅት በተካሄደ የጅምላ ጭፍጨፋ ንጹሃን ዜጎች ሞቱ። ዜናው ከተሰማበት ደቂቃ ጀምሮ የሚወጡት መረጃዎች አስደንጋጭ ናቸው። ለጎልጉል መረጃ የሰጡ እንዳሉት “ሕዝብ ሲቃወም ዝም ቢሉ ምን ችግር ነበረው? ሲቃወም ውሎ ሲመሽ ወደቤቱ ይሄዳል!” እኚህ ሰው እንዳሉት በዓሉ በሚካሄድበት ስፍራ ህወሃትን የሚያሰጋው ነገር የለም። ቀድሞውኑ ህዝቡ ተከቦ ነበር። የተከበበና ከመንገድ ጀምሮ ተልብጦ ሲፈተሸ የዋል ህዝብ ምንም አደጋ ሊያስከትል እንደማይችል የታወቀ ነው። “ሲጀመር ፍርሃቻ የያዘው ህወሃት ህዝብ ሲሰበሰብ ስለሚታመም ከበሽታው በመነጨ ምላጭ ስቦ ህዝብን ረሸነ። ጨፈጨፈ። አቆሰለ። ይህ የማይሽር ጠባሳ በየትኛውም ጊዜ ሙሉ ዋጋ ያስከፍላል። ይቅርታ የለውም። አሁን የይቅርታን ገመድ በጠሷት። አለቀ። ካሁን በኋላ …”

እናቶች፣ አባቶች፣ ወጣቶች፣ ጎረምሶች … በያይነቱ በህወሃት መጨፍጭፋቸውን ህዝቡን አገንፍሎታል። በስፋት እንደሚባለው “አሁን ጊዜው ወያኔን በምትችለው ሁሉ ታገለው። ቦታ አትምረጥ፣ ጊዜ አትምረጥ … ወዘተ” የሚሉ ናቸው። የጅምላ ጭፍጨፋውን ተከተሎ አምቦ ህዝብ ቁጣውን አሰምቷል። በይፋ ባይነገርም እዚያም የህወሃት አንጋቾች ነፍስ አጥፍተዋል። ህዝቡም ንብረት አውድሟል። በሌላ በኩል ከቢሾፍቱ ወደደቡብ የሚወስደው መንገድ በበርካታ ቦታዎች ተዘግቷል፡፡

በጥልቀት መታደስ እያለ ሲፎክር የነበረው ህወሃት አመራሮችን ቀይሬአለሁ ብሎን ነበር፡፡ በመለስ ትዕዛዝ የአዲስ አበባ ንጹሃንን የጨፈጨፈው ወንጀለኛው ወርቅነህ ገበየሁን የኦሮሞ ህዝብ መሪ አድርጎ ከሾመ በኋላ የዛሬውን ዓይነት ጭፍጨፋ በማድረግ ወርቅነህ ለራሱና ለለማ መገርሣ “ሹመት ያዳብር” የሚያሰኝ ታማኝነቱን አሳይቷል፡፡

ህወሃት ጠርንፎ የያዛት አገራችን ጉዳይ አሳሳቢ ከሚባልበት ደረጃ አልፏል፡፡ በርካታ በሰላማዊ ትግል የሚያምኑ ሰላማዊ ሰዎች በዛሬው ዕለት ጠአቅጣጫ ለውጥ ሲያደርጉና ሲያሰሙ ማድመጥ የወንበዴው ቡድን ህወሃት ጉዳይ በሕዝብ አቆጣጠር ሁሉም ነገር ያበቃለት መሆኑን ያመላከተ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡

ጥቂት የሕዝብ አስተያየቶችን ከዚህ በታች አቅርበናል፤

#IrreechaMassacre

በርካቶች ኢሬቻ ሊያከብሩ ወደ ሆራ ሲሄዱ እንዲህ እያሉ ነበር …
“Nuti shororkessa miti, wayyaaneen shororkessadha”
“እኛ አሸባሪዎች አይደለንም፤ አሸባሪው ወያኔ ነው”
ዋሹ?

Ye Kebede Yetnayet And here is the evidence . A highly trained government commando covering his face as a terrorist. Also a heavily armored “Zilla” (a heavily armored technical vehicle recently assembled at Beshoftu Armament industry of METEC). The picture says it all- the killing was planned well in advance.

Mahlet Fantahun

የኢሬቻን በአል እያከበሩ የነበሩ ሰላማዊ ሰዎች ላይ የደረሰው ነገር እጅግ አሰቃቂ ነው። ለወትሮው ደብረዘይት/ቢሾፍቱ ከተማ ኢሬቻ በሚከበርበት ቀን፤ ወደ ሆራ በሚሄድ እና በሚመለስ ሰው ይጨናነቅ ነበር። ዛሬ ግን ከግማሽ ቀን በላይ አልቆየም። ወታደሮቹም ከየመንገዱ ያገኙትን እየደበደቡ ሲሰበስቡ ነበር። መንገዶቹ ጭር ብለዋል። ቢሾፍቱ ሆስፒታል በጣም በርካታ ህዝብ ተሰባስቧል። ግቢው ለቅሶ ቤት ነው የሚመስለው። እራሳቸውን ጥለው እያለቅሱ ወደ ሆስፒታሉ የሚሄዱ እናቶችን ማየት ይረብሻል። የሬሳ ሳጥን ይዘው የሞተባቸውን ቤተሰብ ሬሳ ለመውሰድ ሆስፒታሉ በር ላይ የሚጠብቁም አሉ።
★★★
እረፋድ ላይ ወደ ሆራ የሚሄዱና የሚመለሱ ወጣቶች እየጨፈሩ በድፍረት በሚያሰሙት ሰላማዊ ተቃውሞ ተደስቼ እና አድንቄያቸው ሳልጨርስ ነው ይህ አሳዛኝ ክስተት የተፈጠረው።

Addis Assefa Gonfa That is what I’M feeling…It did not have to be this way though…where is civilization?…where is common sense in all this? I don’t know why so many has to be sacrificed? So many has to be distracted? But now it looks the only way is out of this is fire with fire blood with blood…the barbaric way…the way they opted for…the only way they know….and I guess the end will be tragedy of an immense proportions… As a people Oromo in the past one year has walked the high walk with all the sacrifice to avert this … but it all fell on deaf ears… so let the *** begin

Kebede Degefu Nothing to say but I am outraged saddened no hope for political practices will work in that part of the world

Shovels must be changed to weapons, axes must be used the war they have started overhead must be reversed by all means

Bira’anuu Kabadaa Absolutely, everything has a limit! Our wish for peace and our resilience towards injustice in the name of peace fall on deaf ears and eyes! We can not go on like this everyday, our people being massacred and our heart broken.

Natnael Mekonnen

የነሱ አሸንዳ ያለምንም ኮሽታ ይከበራል እነሱን የሚደግልፍ ሰልፍም እንደዛው ሌላው ህዝብ ግን እንደ ቅጠል ይረግፋል

አንድ ዶክተር ከቢሾፍቱ እንደተናገሩት

«ለ41 አመታት ያህል በህክምና ሙያ ውስጥ አገልግያለሁ፤ በኢትዮ―ኤርትራ ጦርነት ላይም በሃኪምነት አገልግያለሁ። በአንድ ቀን ይሄን ያህል ግድያ ሳይ ግን ይህ የመጀመሪያዬ ነው።»

tplf-on-mourning-joke

Abel Wabella የምወድሽ  

We have a unique regime. They kill civilians & the call it stampede and will declare mourning days

Tsedale Lemma ‏

Every yr, millions of #Oromo gather to celebrate #Irreecha, non have died of ‘Stampede’ until today. Heartbreaking!! #Irreechamassacre

BefeQadu Z. Hailu ‏

People peacefully protested they don’t want cadres speak in #Irrecha and police shot teargas on them, blamed stampede.

BefeQadu Z. Hailu  

#Qilinto prison caught in fire and inmates run to survive. Warders shot them and gov in #Ethiopia said people died in stampede.

Dawit T. ‏

Too much to comprehend, too much to justify, too much to theorize, and too much to forgive. Ain’t too less to act upon it! #IrrechaMascara

Tsegaye Ararssa feeling determined.

Unfortunately, it has become increasingly more and more obvious that there is little likelihood for political end to this carnage. Regrettably, only military solutions are availing themselves. It has become abundantly clear that the matter now is going to be settled on the streets and jungles of Oromia, not on the corridors of the political class in Addis or on the diplomatic corridors of the regime’s foreign patrons. This must be the limit of politics, national and international.

irreecha17
የህወሃት ነፍጥ አንጋቾች ራሳቸውን በመሸፈን ለግድያ የተዘጋጁ ነበር – በታንክ ላይ መትረየስ ጭኖ ሕዝብ ሲያሸብር የነበረው ፊቱን የሸፈነበት ጨርቅ አስቀድሞ የተዘጋጀ ነበር

ሰላማዊው ሕዝብ



የህወሃትን የበላይነት ለማስጠበቅ ደም እንዲያፈሱ ሙሉ ሥልጣን የተሰጣቸው

irreecha18
irreecha19
irreecha20
irreecha22
irreecha23
irreecha24
irreecha25
irreecha3
irreecha55

በታንክና በሔሊኮፕተር የተከበበው ሕዝብ ተጨፈጨፈ

irreecha66
irreecha67
irreecha68
irreecha41
irreecha42
irreecha43
irreecha44
irreecha45
irreecha46
An injured protester waits for help after several people died during the Irrechaa, the thanks giving festival of the Oromo people in Bishoftu town of Oromia region, Ethiopia, October 2, 2016. REUTERS/Tiksa Negeri
An injured protester waits for help after several people died during the Irrechaa, the thanks giving festival of the Oromo people in Bishoftu town of Oromia region, Ethiopia, October 2, 2016. REUTERS/Tiksa Negeri
irreecha28
irreecha29
irreecha30
irreecha31
irreecha32
irreecha33
irreecha34
irreecha35
irreecha36
irreecha37
irreecha38
irreecha39
irreecha37-1
irreecha37-2
irreecha37-3
irreecha12
irreecha13
irreecha14
irreecha15
irreecha4
irreecha5
irreecha6
irreecha7
irreecha8
irreecha9
irreecha10
irreecha11
irreecha56
irreecha57
irreecha70
irreecha71
irreecha72
irreecha73
irreecha58
irreecha59
irreecha60
irreecha61
irreecha62
irreecha64
irreecha65
irreecha63

/>

የቤተሰብ እጅግ የመረረ ሐዘን

Dina Alemayehu ስለ እህቷ ይህንን አለች “ምን ልበል? ምን ላድርግ እህቴ!? ተቃጠልኩልሽ! ተንገበገብኩልሽ እህቴ!! ገና ነበር እኮ ጊዤሽ! እንዴት ልሁን?! ምን ልሁን ሰላምዬ?!! ኢህአዴግ ቀማኝ እህቴን!!!” በቀኝ የሚታዩት እናቷ ናቸው – ለርሳቸውም ዲና ይህንን አለች “እማዬ ይሄው እንደዛ ምትሳሽላት እህትሽ እንደወጣች ቀረች አቃጠለችን እኮ እግዚአብሔር ለእህቴም ለኢትዮጲያም ህዝብ ይፈርዳል”


ሲፈን ለገሰ ትዳር ከመሰረተች ገና ስድስት ወሯ ነው – ዛሬ በህወሃት ተቀጥፋለች ወንድሟ Ambo Gara Galgala ይህንን ብሏል። “ካገባች እንኳን ስድስት ወር ያልሞላት እህቴ ሲፈን ለገሰ ዛሬ ከጎኔ ተለየች። በቢሾፍቱ ሌሎች የቀመሱትን የሞት ፅዋ እሷም ተጋራች። ሃዘኔ መራር ነው ሲፎኮ ምንም የምናገርበትም አደበት የለኝም። ፈጣሪ ነፍስሽን በገነት ያኑረው!”

irreecha54-sifen
irreecha-sifoko
irreecha40

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: Left Column, News, Politics, Social Tagged With: irechaa, jawar massacre, olf, olf shanee, tplf

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
Copyright © 2026 · Goolgule