በሀገሬ ሰማይ ስር በሚደረገው የተቃውሞ ፖለቲካ እንቅስቃሴ ከኢዴፓ እስከ አንድነት ፓርቲ ድረስ በመሳተፍ ለአስራ ሶስት ዓመታት ያህል የምችለውን አስተዋጽኦ አድርጌያለሁ፡፡ ይህ ኩነትም የፓርቲዎችን ጓዳ ፈትሼ ግንዛቤ እንዳገኝ ስላመቻቸልኝ፣ በቀጣይ ህዝባችን የፖለቲካና ሰብአዊ መብቶቹ ተከብረው ነፃነቱን እንዳያገኝ እንቅፋት ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ የማስባቸውን ነጥቦች እንደሚከተለው ለማቅረብ እወዳለሁ፡፡ እንደ ገዥው ፓርቲ፣ ተቃዋሚ ድርጅቶችም ከኋላቀሩ የፖለቲካ ባህላ የተላቀቁ አለመሆናቸው ነው፡፡ እናም አዲስ የፖለቲካ ባህል ለማስጀመር ከመስራት ይልቅ ሳያውቁት ከዘመነ-መሳፍንት የተቀዳውን የፖለቲካ ባህል በተሻለ ተግባራዊ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ዛሬም ይታያሉ፡፡ የእስከ ዛሬውን የከሸፈ ሂደት የገመገመና የኢትዮጵያን ህዝብ ለአንዴና ለመጨረሻ ከተጫነበት የጭቆና ቀንበር ለማላቀቅ … [Read more...] about የሐምሌ ጨረቃ
Politics
የጋራ ንቅናቄው ከሰማያዊ ፓርቲ ጎን ይቆማል!
ያለፈው እሁድ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ጠርቶ በነበረው የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ላይ በህወሃት/ኢህአዴግ የተወሰደውን ጽንፈኛ፣ አክራሪና አጸያፊ የውንብድና ተግባር የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ይኮንናል፤ ያወግዛል፡፡ ፓርቲው ሰልፉን ለማካሄድ ከሁለት ወራት በፊት ፈቃድ ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም ቅዳሜ ነሐሴ 25፤2013 የፌዴራል ፖሊስና የደኅንነት አባላት የፓርቲውን ጽ/ቤት ጥሰው በመግባት የፈጸሙት ተራ የውብንድና ተግባር ብቻ ሳይሆን የህወሃት/ኢህዴግን ማንነት በግልጽ ያሳየ ለመሆኑ ከማንም በላይ ተግባሩ ራሱ ምስክር ነው፡፡ በዕለቱ እንደሆነው የህወሃት/ኢህአዴግ አሸባሪ ፖሊሶች የሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤትን ከመውረራቸው በፊት ኤሌክትሪክ መስመሩን ቆርጠዋል፡፡ በቀጣዩም ለእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ዝግጅት እያደረጉ የነበሩትን አመራሮችና ፈቃደኛ ሠራተኞችን ዘግናኝ በሆነ … [Read more...] about የጋራ ንቅናቄው ከሰማያዊ ፓርቲ ጎን ይቆማል!
ሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፉን ቀን ወደ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም አስተላለፈ!!
ሰላማዊ ትግላችን ይቀጥላል!!! ሰማያዊ ፓርቲ ለነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ጠርቶት የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ በመንግስት ታጣቂ ኋይሎች ሕገ-አራዊት እርምጃ ከተደናቀፈ በኋላ ፓርቲያችን ነሐሴ 30 ቀን 2005 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ጳጉሜ 2 ቀን 2005ዓ.ም ሠልፉ በድጋሚ እንደሚካሔድ አስታውቋል፡፡ ሠልፉ የተሳካና ሰላማዊ እንዲሆን በፓርቲ በኩል ልዩ ልዩ ተግባራት ከመከናወናቸው ጎን ለጎን አስፈላጊው የጸጥታ ጥበቃና የአስተዳደር ድጋፍ እንዲሰጠን በህጉ መሰረትም ሠልፉ እውቅና እንዲያገኝ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሰወቂያ ክፍል ነሐሴ 27 ቀን 2005ዓ.ም ደብዳቤ ለማስገባት በአካል ተገኝተን ጠይቀናል፡፡ ሆኖም ግን ይህ ክፍል ደብዳቢያችንን ለመቀበል ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ በፓርቲው በኩል በሁኔታው ተስፋ ባለመቁረጥ በኢትዮጵያ ፖስታ … [Read more...] about ሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፉን ቀን ወደ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም አስተላለፈ!!
ደቡብ ክልል ሪፖርተርን በህግ እጠይቃለሁ አለ
የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የደቡብ ክልል የመንግስት ጉዳዮችን ጠቅሶ እንደዘገበው "ሪፖርተር ጋዜጣ 3ምክትል ርእሰ መስተዳድሮች ከሃላፊነታቸው ተነሱ በማለት ያወጣው ዘገባ መሰረተ ቢስ" ብሎታል። ይሁን እንጂ ሪፖርተር ከሃላፊነታቸው ተነሱ ያላቸው ሶስት የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች በስልጣን ላይ ስለመኖራቸው ያለው ነገር የለም። ዜናውን አስተባበለ፣ ጉዳዩንም ወደ ህግ ሊወስድ ዛተ የተባለው የክልሉ የመንግስት ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተጠቀሰበት ዜና ከዚህ የሚከተለው ሲሆን፣ ዜናው ከሪፖርተር በኩል ስላለው የዜናው መረጃ እውነተኛነት አላካተተም። ሪፖርተር ለሰራው ዜና ምንጮቹ የተሳሳቱ ከሆነ ዜናውን ቀደም ሲል በሰራበት መጠንና ቦታ ይቅርታ ለመጠየቅና ራሱን በራሱ ማስተባበል ይጠበቅበታል። ዜናው እንደሚከተለው ይነበባል:- ሪፖርተር ጋዜጣ 3ምክትል ርእሰ መስተዳድሮች … [Read more...] about ደቡብ ክልል ሪፖርተርን በህግ እጠይቃለሁ አለ
የደቡበ ክልል ሦስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ከኃላፊነት ተነሱ
የደቡብ ክልልን ከሚመሩት አራቱ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች መካከል ሦስቱ ከኃላፊነት መነሳታቸውን ምንጮች ገለጹ፡፡ ለሦስቱ ከፍተኛ ባለሥልጣናት መነሳት ከነሐሴ 15 እስከ 19 ቀን 2005 ዓ.ም. ከተደረገው ግምገማ ጋር የተያያዘ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮች፣ ለእያንዳንዳቸው መነሳት የተለያዩ ምክንያቶች መኖራቸውን ያስረዳሉ፡፡ ከኃላፊነታቸው ከተነሱት መካከል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የሲቪል ሰርቪስ ቢሮ ኃላፊ ከሆኑ አንድ ዓመት ያልሞላቸው አቶ ታገሠ ጫፎ ሲሆኑ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የመንግሥት ዋና ተጠሪ አቶ አለማየሁ አሰፋና በተመሳሳይ ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳኒ ረዲ ናቸው፡፡ የአቶ አለማየሁ አሰፋና የአቶ ታገሠ ጫፎ መነሳት የተጠበቀና ውስጥ ለውስጥ ሲነገር የቆየ መሆኑን፣ ያልተጠበቀው ግን የአቶ ሳኒ ረዲ ነበር በማለት አስተያየት የሰጡት የደኢሕዴን አባልና ስማቸው … [Read more...] about የደቡበ ክልል ሦስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሮች ከኃላፊነት ተነሱ
በመንግስታዊ ውንብድና ትግላችን አይገታም!!!!!
ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ባካሄደው ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ለመንግሥት ያቀረባቸው ጥያቄዎች አስፈላጊው ምላሽ እንዲሰጣቸው በመጠየቅ ይህ ካልሆነ ግን ከሦስት ወር በኋላ ተቃዉሞውን ከፍ ባለ ደረጃ እንደሚያቀርብ በመጋለፅ ሰልፉን አጠናቋል፡፡ ለተነሱት ጥያቄዎች የተገኘ ምላሽ ባለመኖሩ ፓርቲው ለሕዝብ በገባዉ ቃል መሠረት ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ታላቅ የተቃዉም ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሔድ በመወሰን በሕግም ሆነ በሥራ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማጠናቀቅ እለቱን በመጠበቅ ላይ እያለ ምንም አይነት መለዮ ባልለበሱ ግለሰቦች የሚመራ የፖሊስ መለዮ ለባሽ ታጣቂዎች ከሕግ ውጭ ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም. ከምሽቱ 12 ሰዓት አካባቢ የፓርቲውን ቢሮ ጥሰው በመግባት ፓርቲው ይጠቀምባቸው የነበሩ የቅስቀሳ ቁሳቁሶችና ሌሎች የፓርቲውን ንብረቶች ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ … [Read more...] about በመንግስታዊ ውንብድና ትግላችን አይገታም!!!!!
ፖለቲካ ሳይንስ ነው ወይ? ፖለቲካ ምሁራዊነት ያስፈልገዋል ወይ?
መግቢያ በዚህ አርዕስት ላይ ለመጻፍ ከአሰብኩ ረዥም ጊዜ ሆነኝ። እንደሚታወቀው አንድ ጥናታዊ ጽሁፍ ለማቅረብ ቀላል አይደለም። የመንፈስ ርጋታን የሚጠይቅ ብቻ ሳይሆን፣ ለአንባቢ የሚቀርበው ጽሁፍ ከርስ በርስ ቅራኔዎች የተላቀቀና አሳማኝ እንዲሆን አድርጎ ለመጻፍና ለማስነበብ ረዥም ጊዜን ይፈጃል። ብዙ ዕውቀትንና ምርምርን ይጠይቃል። ተመራምሮና የተለያዩ አስተሳሰቦችን አወዳድሮና አመዛዝኖ ለአንባቢ አንድ የሚያረካና እንደመመሪያ ጥናት ለማቅረብ ረዥም ጊዜ ብቻ ሳይሆን ቢያንስ የሶስትና የአራት ሰዎችን የስራ ክፍፍል ይጠይቃል። አንድ ሰው ብቻ የሚጽፍ ከሆነ ደግሞ ቢያንስ የሶስት ወር ዝግጅት ማድረግ አለበት። በተጨማሪም በኢንስቲቱሽንና በገንዘብ የሚደገፍ መሆን አለበት። በተለይም ለአገር ዕድገትና ነፃነት ተብሎ የሚጻፍ ጽሁፍና የፖለቲካ ሀተታ በአቦ ሰጡኝ የሚቀርብ ሳይሆን ብዙ ጥንቃቄን … [Read more...] about ፖለቲካ ሳይንስ ነው ወይ? ፖለቲካ ምሁራዊነት ያስፈልገዋል ወይ?
የኢትዮጵያ መንግሥት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ጥቃት አላደረስኩም ሲል ካደ
በሳምንቱ መጨረሻ ላይ 100 የሚጠጉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት እንደታሰሩና አንዳንዶቹም ክፉኛ እንደተደበደቡ ፓርቲው ገለጸ:: እሁድ ሊካሄድ ለነበረው ሰላማዊ ሰልፍ የተዘጋጁ የድምጽ መሣሪያዎች እንደተወሰዱባቸውና ሰልፉም እንዳይካሄድ እንደተደረገ የፓርቲው ሊቀመንበር ይልቃል ጌታቸው አስታውቀዋል:: የመንግሥት መገናኛ ሚ/ር ሽመልስ ከማል ድርጊቱ አልተፈጸመም ሲሉ የካዱ ሲሆን መንገዱ አክራሪነትን ለመቃወም መንግስት ለጠራው ትዕይንተ ሕዝብ አስቀድሞ ተይዞ እንደነበር መንግሥት አስታውቆዋል:: ኢትዮጵያን የሚገዛው ኢህአዴግ የሕዝቡን ህይወት በተመለከተ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚያደርግ ይታወቃል:: ሰማያዊ ፓርቲ በሰኔ ወር የጠራው ህዝባዊ ተቃውሞ በ1997 ከተደረገውና የመቶዎች ህይወት ከቀጠፈው ሰላማዊ ትዕይንተ ሕዝብ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ነበር:: ያለፈው ተቃውሞው የመብት ተሟጋቾችና … [Read more...] about የኢትዮጵያ መንግሥት በሰማያዊ ፓርቲ ላይ ጥቃት አላደረስኩም ሲል ካደ
Jailed: top TPLF warlord Woldesilassie’s kingdom of death and deceit crumbles
He was the dead tyrant Meles Zenawi’s alter ego and docile horse for 21 years and the most feared man in the complex TPLF security cluster. He amassed millions through corrupt practices and managed to build his own kingdom in partnership with equally corrupt former first lady Azeb Mesfin and her daughter Semhal Meles, the two queens of his vast empire. The malevolent warlord was well protected by the Zenawi family for 21 years and well placed in the inner circle of the ruling elite where … [Read more...] about Jailed: top TPLF warlord Woldesilassie’s kingdom of death and deceit crumbles
ሰማያዊ ፓርቲ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ላይ ተቃውሞ አቀረበ
በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. የመጀመሪያውን የተቃውሞ ሠልፍ ያካሄደው ሰማያዊ ፓርቲ፣ በመጪው እሑድ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ተቃውሞ አቀረበ፡፡ ሁለተኛውንና በርካታ ሰዎች እንዳሚሳተፉበት ሲገልጽ የከረመውን ሰላማዊ ሠልፍ የሚያካሄደው ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደነበር ፓርቲው አስታውቆ፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በተደራቢነት በዕለቱ ሠልፍ እንደሚያደርግ ያስተላለፈው ጥሪ ትክክል አይደለም ብሏል፡፡ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ያስተላለፈውን፣ ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነትን እናውግዝ›› የሚል የሠልፍ ጥሪ የተቃወመው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ሲያስተዋውቅና ጥሪ ሲያደርግ መክረሙን ገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርግ ቀድሞ ማሳወቅ ለሚገባው … [Read more...] about ሰማያዊ ፓርቲ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ላይ ተቃውሞ አቀረበ










