• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የ2005 ዋና ዋና ፖለቲካዊ ክንዉኖች

September 10, 2013 07:10 am by Editor Leave a Comment

የመለስ ዜናዊ አስተሳሰብና ምግባር ሕዝብን በተለይም ፖለቲከኞችን በተራራቀ ተቃራኒ ጫፍ እንዳቆሙ መሞታቸዉ የኢትዮጵያን ፖለቲካ በበጎ ወይም በመጥፎ፥ ወይም በሁለቱም መሐል-ክፉኛ መንካቱ እንደማይቀር ያኔ ተብሎ ነበር። አሁንም አልቀረም።

የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚንስትር ተሸኙ።

ሁለት ሺሕ አራትም ተሰናበተ። እና አዲስ ዓመት። ሁለት ሺሕ አምስት። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃና ጳጳሳት እና፥ በአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ማግስት የባተዉ ሁለት ሺሕ አምስት ካዲስ መሪ፥ ካዲስ ርዕሠ ሊቃነ ጳጳሳት ሹመት ጋር አዲስ ተስፋ አጭሮም ነበር። ዓመቱ ዛሬ-አርጅቶ ሊሰናበት ሁለት ቀን ቀረዉ። የዓመቱን የኢትዮጵያ አበይት ፖለቲካዊ ክንዉኖች እየጠቃቀስን፥ ተስፋዉ መጠዉለግ-መፅደቁን፥ ላፍታ እንቃኛለን። አብራችሁኝ ቆዩ።

መለስ በተቀበሩ በሳምቱ ሁለት ሺሕ አምስት እንደ አዲስ ዓመት ሲብት ሁለት የስዊድን ጋዜጠኞችን ጨምሮ በሺሕ የሚቆጠሩ እስረኞች በምሕረት መፈታታቸዉን የኢትዮጵያ መንግሥት ማወጁ፥ የአዲሱ ዓመት አዳዲስ መሪዎች አሮጌዉን ከፋፋይ መርሕ ከአሮጌዉ ዓመት ጋር ለማሰናበት ፍንጭ ማሳየታቸዉ መስሎ ነበር።

ከእስረኞቹ የመፈታት ዜና በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግሥት ከኦጋዴን ብሔራዊ ነፃዉጪ ግንባር (ኦብነግ) ጋር ለመደራደር መወሰኑን አስታዉቆም ነበር።ኦብነግ የመለስ ዜናዊ መንግሥት ለረጅም ጊዜ ባሽባሪነት የወነጀለዉ፥ ከሁለት ሺሕ ሁለት ጀምሮ ደግሞ ከአልቃኢዳ፥ ከአልሸባብ፥ እና ከሁለት ሐገር በቀል ድርጅቶች ጋር በሕግ-በአሸባሪነት የፈረጀዉ ቡድን ነዉ።semayawi rally

በዚሕም ሰበብ በመለስ ሞት ማግሥት አዳዲሶቹ መሪዎች ከኦብነግ ጋር ለመደራደር መስማማታቸዉን ሲያስታዉቁ፥ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ አዲስ ተስፋ ማጫሩ አልቀረም። በአዲሱ ዓመት ዋዜማ ናይሮቢ ኬንያ ዉስጥ በኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስትር ሲራጅ ፈርጌሳና በኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጪ ግንባር የዉጪ ግንኙነት ሐላፊ በአብዱረሕማን መሕዲ መካካል የተደረገዉ ድርድር እንዲደረግ የወሰኑት አቶ መለስ ዜናዊ ከመሞታቸዉ በፊት መሆኑ ሲነገር ግን ተስፋዉ የአዲሱ ዓመት ፀጋ፥ የአዲሶቹ መሪዎችም ብልሕነት እንዳልሆነ ግልፅ ሆነ። እስረኞቹ የተለቀቁትም በመለስ ዉሳኔ እንደነበር ተነግሯል።

የሁለቱ ወገኖች ተደራዳሪዎች በድርድሩ ሥነ-ሥርዓታዊ ጉዳዮች ተስማምተዉ፥ ለመስክረም ማብቂያ ለሁለተኛ ዙር ድርድር ለመገናኘት ተቀጣጥረዉ ነበር። መንግሥት አማፂዉ ቡድን ሕገ-መንግሥቱን ካልተቀበለ አልደራደርም በማለቱ፥ አማፂዉ ቡድን ቅድመ ሁኔታዉን ባለመቀበሉ ቀጠሮዉ-በቀጠሮ ቀረ። ተስፋዉም ቢያንስ ለዚሕ ዓመት ተጨናጎለ።

ተስፋ የማይቆርጠዉ ወይም ተስፋ ላለመቁረጥ፥ ተስፋ የሚያደርገዉ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሌላ ተስፋ የሚያደርግበት ሰበብ ምክንያት አላጣም። የአዲሱ መሪዉ ቃል ዋናዉ ነበር። የአቶ መለስ ዜናዊ ሞት ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ሥልጣን በጊዚያዊነት የያዙት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚንስትርነትቱን ሥልጣን በይፋ ተረከቡ።

መስከረም አስር። አዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ኋላ እንዳሉት የዚያን ቀን ያደረጉትን ንግግር ፍሬ ሐሰብ ከማርቀቅ በስተቀር ንግግሩን የፃፉት ሌሎች ናቸዉ። ንግግሩን እንደ ኦጋዴኑ ድርድር ሟቹ ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የወሰኑት ወይም ፅፈዉ የተዉት ነዉ ማለት ግን አይቻልም።የንግግሩ ይዘት፥ ቃሉም ብዙ አዲስ አይደለም። ግን የአዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር ነዉ። የሐይለ ማርያም ደሳለኝ።

ሁሉም ተባለ። የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ጥሪ፥ የነፃ ጋዜጠኞች አቤቱታ፥ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስሞታ፥ የሙስሊሞች ጩኸትም ቀጠለ። ታሕሳስ መባቻ። የአል-ጀዚራዋ ጋዜጠኛ አዲሱን የጠቅላይ ሚንስትር ጠየቀች።

muslims1«ሙስሊሞችን በተመለከተ በቀጠለዉ የተቃዉሞ ሠልፍ ምክንያት (እና በሌላም ምክንያት) በሐገሪቱ ዉስጥ ብዙ ችግሮች አሉባችሁ። በሺ የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረዋል። ብዙዎቹ እንደሚሉት መንግሥት አህባሽ የተሰኘዉን የእስልምና (ሐራጥቃ) በሕዝቡ ላይ በሐይል ጭናችኋል፥ መንግሥት ሐይማኖቱን በሐይል ባዲስ መልክ ለመቅረፅ ጠንካራ እርምጃ ወስዷል ይላሉ። ጠንካራ እርምጃ ነዉ።»

ጠቅላይ ሚንስትሩ መለሱ።

«እንደሚመስለኝ ይሕ የአናሳዎች ድምፅ ነዉ። የአብዛኞቹ ድምፅ አይደለም። የአብዛኞቹ ሙስሊሞች ጥያቄ የራሳቸዉ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸዉ ነዉ። መንግሥት በነሱ የአስተዳደር ሥርዓት ዉስጥ የሚያገባዉ የለም። ለሐይማኖት ያልወገነ መንግሥት ነዉ ያለዉ።ሕገ-መንግሥቱም መንግሥት በሐይማኖታዊ ጉዳይ ጣልቃ እንደማይገባ ይደነግጋል።»

ጥር ማብቂያ። ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ «በሐይማኖታዊ ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ያሉት መንግሥት የሚቆጣጠረዉ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጉዳያቸዉ በፍርድ ቤት የሚታይ የሙስሊም መሪዎችን በአሸባሪነት የሚወነጅለዉን ፊልም አሰራጨ። ርዕስ፥ ጅሐዳዊ ሐረካት።

ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለ ማርያም ለአል-ጀዚራ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃለ ምልልስ በፖለቲካ ምክንያት የታሠረ አንድም ሰዉ እንደሌለ ተናግረዉ ነበር። ጥር ማብቂያ። ዓለም አቀፉ የሠብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ሑዩማን ራይትስ ዋች ባወጣዉ ዘገባዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ከጥር ሁለት ሺሕ አራት እስከ ታሕሳስ ሁለት ሺሕ አምስት በነበረዉ አንድ ዓመት ብቻ ሰላሳ የተቃዋሚ ፓርቲ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች በአወዛጋቢዉ የፀረ-ሽብር ሕግ ተወንጅለዉ እስራት ተበይኖባቸዋል።

የቀድሞዉ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ-ክርስቲያን ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ከሞቱበት እስከ ዓመቱ አጋማሽ ድረስ የዉጪ እና የሐገር ዉስጥ በሚል ለሁለት የተከፈሉት የሐይማኖት አባቶች ይታረቃሉ የሚል ተስፋ አሳድሮ ነበር። ድርድር፥ ዉይይትም ነበር። የካቲት-ሁሉም ቀረ። የሐገር ዉስጡ ሲኖዶስ የዉጪዉን ጥያቄ ዉድቅ አድርጎ ርዕሠ-ሊቃነ ጳጳሳት ሾመ።

ሚያዚያ፥ ምርጫና ጉብኝት ነዉ። መስከረም ላይ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቃል ገብተዉ ነበር።

ሚያዚያ ላይ ሠላሳ ሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድን ጨምሮ ከመንግሥትና ከገዢዉ ፓርቲ ይደርስብናል ያሉት ጫና እንዲቃለልላቸዉ ያቀረቡት ጥያቄ ዉድቅ ሆነብን በሚል ከአካባቢያዊና ከከተሞች አስተዳድር ምርጫ እራሳቸዉን አገለሉ። ገዢዉ ፓርቲ እና ተባባሪዎቹ ብቻቸዉን ተወዳድረዉ አሸነፉ።

ጠ/ሚ/ር ሐይለ ማርያም ደሳለኝ ከአዉሮጳ ሕብረትና ከፈረንሳይ ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር ብራስልስን፥ ሽትራስቡርግንና ፓሪስን የጎበኙትም ሚያዚያ አጋማሽ ነበር።

ግንቦት፥ የአፍሪቃ መሪዎች የአፍሪቃ ሕብረት የተመሠረተበትን ሐምሳኛ ዓመት አዲስ አበባ ዉስጥ በደማቅ ሥነ-ሥርዓት አከበሩ። መሪዎቹ በተሰናበቱ በሳምንቱ ሰማያዊ ፓርቲ የጠራዉ የተቃዉሞ ሠልፍ አዲስ አበባ ዉስጥ ተደረገ። ከ1997 ወዲህ ሕዝብ፥ መንግሥትን በመቃወም አደባባይ ሲወጣ የመጀመሪያዉ ነበር። ግንቦት ሃያ-አምስት።

በወሩ አንድነት ለፍትሕና ለዲሞክራሲ የጠራዉ ሠላማዊ የተቃዉሞ ሠልፍ ጎንደርና ደሴ ዉስጥ ተደረገ። የአደባባይ ተቃዉሞ ሠልፍ የማድረጉ ጥረት፥ ሙከራ፥ ዝግጅትም ቀጥሏል። የዚያኑ ያክል ተቃዋሚ ፖለቲከኞች እንደሚሉት በአባሎቻቸዉና በደጋፊዎቻቸዉ ላይ መንግሥት የሚፈፅመዉ እስራት እንግልትም አላባራም።udj rally

ግንቦትና ሰኔ፥-የኢትዮጵያንና የግብፅን የቃላት እንኪያ ሰላንታ እንዳሰሙን-ሐምሌ ተካቸዉ።

የአዉሮጳ ምክር ቤት የሰብአዊ መብት ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ ባርባራ ሎኽቢኸር የመሩት የመልዕክተኞች ቡድን ኢትዮጵያን ጎብኝቶ ነበር።

ሐምሌ – ቡድኑ ከመንግሥትና ከተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ጋር ከተነጋገረ በኋላ እስረኞችን ለመጎብኘት ጠይቆ ተፈቅዶለት ነበር። ቃሊቲ ሲደርስ «ማን ፈቀደልህ» ተባለ።

የዘንድሮዉ ሐምሌ ለሙስሊሞች የቅዱስ ረመዳን ወር ነበር። የድምጻችን ይሰማ የመስጊዱ ተቃዉሞ ጩኸታቸዉ ግን አላባራም። በተቃዉሞዉ ሰበብ ከፀጥታ አስከባሪዎች የሚደርስባቸዉ ወከባ እስራት ዘረፋና ግፍም ብሶ ቀጥሏል። ለኮፈሌ፥ ለኢዶ፥ ለዋቤ፥ ለቆሬ ከተሞች ደግሞ የዘንድሮዉ ረመዳን የአሳዝኝ ግድያ ወርም ነበር።

ሐምሌ ማብቂያ ፀጥታ አስከባሪዎች በተሰበሰቡ ሙስሊሞች ላይ በከፈቱት ተኩስ ሲያንስ አስር ሲበዛ ሃያ-ስድስት ሰላማዊ ሰዎች ገድለዋል። ኢድ-አልፊጥር የፌስታ፥ ደስታ፥ ታላቅ ዕለት ነዉ።የአዲስ አበባ ሙስሊሞች የዘንድሮዉን ረመዳን የፈጠሩት፥ ኢድን ያከበሩት የከብት፥ የበግ፥ የዶሮ ደም አፍስሰዉ ሳይሆን በፖሊስ ቆመጥ የራሳቸዉን ደም አዝርተዉ ነበር። ሁለት ጋዜጠኞችም ታስረዉ ነበር። ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት የጋዜጠኞቹን መታሰር አዉግዟል።

በዓለም ላይ በሸሪዓ ሕግ የሚገዙ ሁለት ሐገራት አሉ። ኢራንና ሳዑዲ አረቢያ። ጠቅላይ ሚንስትር ሐይለማርያም ደሳለኝ በኢድ አልፊጥር ማግሥት እንዳሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ኢትዮጵያን በሸሪዓ ሕግ የምትገዛ ሦስተኛ ሐገር ለማድረግ ይጥራሉ።

ዘንድሮ- ሦስት ሚንስትሮች የተሻሩ፥ ከሦስቱ አንዱ ከተከታዮቻቸዉ በሙስና የታሰሩበት፥ አዳዲስ ሚንስትሮች የተሾሙበት፥ ኢትዮጵያ ባለ-ሦስት ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ካቢኔ የሰየመችበትም ዓመት ነዉ። ዓመቱ በርካታ የህወሃት ቁልፍ ሰዎች እና የደኅንነት አመራሮች እንዲሁም አይነኬ ባለሃብቶች ከሥልጣናቸው እየተነቀሉ ሌሎችን ሲያጉሩበት በነበረው እስርቤት የተወረወሩበት ነው፡፡ የሙስናው መዘዝ ተመዝዞ መጨረሻው የት እንደሚደርስና ወደየት አቅጣጫ እንደሚነጉድ መጪው ዓመት ብዙ ያሳየናል፡፡ ዋናዎቹን የሙስና ሻርኮችንም ይደርስባቸው ይሆን ወይም አልፏቸው ይሄድ ይሁን አዲሱ ዓመት ያሳየናል፡፡(ምንጭ፡ የጀርመን ድምጽ ሬዲዮ፤ ዘገባው ለጋዜጣችን እንዲመች ሆኖ ለመታረሙ ኃላፊነቱን እንወስዳለን)

ለአገራችን ፍትሕ፣ ነጻነት፣ ሰላምና ዕርቅ እየተመኘን መልካም 2006 ለመላው ሕዝባችን!!

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule