• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሰማያዊ ፓርቲ ሕገ-መንግስት አረቀቀ

September 25, 2013 05:39 pm by Editor Leave a Comment

በቅርቡ የተመሰረተው የሰማያዊ ፓርቲ ‘‘የዜጎች የቃል ኪዳን ሰነድ ለዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ’’ በሚል መርህ ወደፊት የፖለቲካ ሥልጣን ሲይዝ የሚመራበትን አዲስ ህገመንግስት ማርቀቁን አስታወቀ። ረቂቅ ሰነዱ ላይ ምሁራንና ባለሙያዎች ውይይት ካደረጉ በኋላ ለሕዝብ እንደሚቀርብ ፓርቲው አስታውቋል።

የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት በአዲሱ ረቂቅ ሕገ-መንግስት ላይ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ውይይት እንደሚደረግ አስታውቀዋል። በውይይቱ ላይ ከዚህ በፊት የነበሩ ሦስት ህገ-መንግስቶች ድክመትና ጥንካሬ ምንድን ነው? አዲስ በሚረቀቀው ህገ-መንግስት ምሰሶዎች ምን ይሆናሉ፣ ስልጣንና ሕዝብን እንዴት ማገናኘት ይቻላል በሚሉ ወሳኝ ንድፈ ኀሳቦች ላይ የጠለቀ ውይይት እንደሚደረግ አስታውቀዋል።

‘‘የአሁኑ ሕገ-መንግስት የኢህአዴግ ፕሮግራም ቅጂ ነው’’ ያሉት ኢንጂነር ይልቃል እያረቀቁ ያሉት ሕገመንግሥት የሰነድ ዝግጅቱም ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁንና ምሁራን በሚያደርጉት ውይይት ከዳበረ በኋላ ለሕዝቡ ውይይት ቀርቦ ለባለሙያዎች ተመርቶ ዝርዝር ህጎች እንዲፃፉ ይደረጋል ብለዋል።

ፓርቲው ሰላማዊ ሰልፍ የሚያካሂደው ሕዝቡን ለማነቃቃትና ለማስተማር አባላትንም ለመመልመል ቢሆንም በተጓዳኝ ፓርቲውን ለማጠናከርና ምን አይነት ስርዓት እንገነባለን የሚለውንም ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ መሆኑንም ኢንጂነር ይልቃል ገልፀዋል።

ሰማያዊ ፓርቲ ሕገ-መንግስት ባለበት ሀገር ሌላ ሕገ-መንግስት ከማውጣት የሚያግደው ነገር እንደሌለ የጠቀሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ ፓርቲው እያካሄደ ያለው ትግል በሕገ-መንግስት የማይመራን አገዛዝ በዲሞክራሲያዊ ስርዓት የመተካት ስለሆነ አዲስ ህገ-መንግስት ማስፈለጉ የግድ ነው ብለዋል።

የፓርቲው ዋና አላማ በሀገሪቱ ሕጋዊ ስርዓትን መትከል በመሆኑ አሁኑ ባለው ሕግ-መንግስት በሚደረግ ምርጫ አብላጫ ወንበር ማግኘቱን ሲያረጋግጥ አዲሱን ሕገ-መንግስት ተግባራዊ ያደርጋል ብለዋል። በዚህ ሀገር ምርጫ ከተካሄደም ሰማያዊ ፓርቲ 99.6 በመቶ አብላጫ ወንበር ለማግኘት የሚያግደው ነገር እንደሌለም እርግጠኞች ነን ሲሉ አያይዘው ገልፀዋል።

ፓርቲው ከፖለቲካና ኢኮኖሚ አማራጭ ፕሮግራም በዘለለ አዲስ ህገ-መንግስት ማርቀቁ ቀዳሚ ተግባር መሆኑን የጠቀሱት ኢንጂነር ይልቃል፤ የፓርቲው አማራጭ ፕሮግራም የሚመነጨው ከረቀቀው ሕገ-መንግስት ነው ብለዋል። አዲሱ ህገ-መንግስት በሀገሪቱ ስለሚኖረው አጠቃላይ ስርዓትና መንግስታዊ አወቃቀር፣ የኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ የገበያ ስርዓት፣ ዓለም አቀፍ ግንኙነት፣ የመሬት ፖሊሲ፣ ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ ገዥ ኀሳቦች የሚመነጩት ከህገ-መንግስት እንደሆነ ገልፀዋል። የፓርቲው ፕሮግራም ከህገ-መንግስቱ የሚመነጩ ዝርዝርና ስትራቴጂካዊ አቅጣጫ በመሆኑ ቀዳሚውና ምሰሶው ሕገመንግስት ነው ብለዋል።

‘‘የኢትዮጵያ ችግር መጠነኛ ችግር ሳይሆን አጠቃላይ ሕጋዊ ስርዓት የመትከልና፤ የሁሉም የኢትዮጵያ ዜጎችን መብት፣ ባህል፣ ታሪክን ግምት ውስጥ ያስገባ ስርዓት የማቋቋም ጉዳይ ነው’’ ያሉት ኢንጂነሩ አሁን ካለው ህገ-መንግስት ሊካተቱ የሚችሉት የሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ ድንጋጌዎች እና ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ደረጃ የፈረመቻቸውን ድንጋጌዎች እንደሆኑም አስገንዝበዋል። ኢህአዴግ ለሀገር ደህንነትና ለህዝብ ጥቅም ሽፋን ከሕዝብ ነጥቆ የወሰዳቸው መብቶች በአዲሱ ህገ-መንግስት እንደሚካተቱ አመልክተዋል። ከኢህአዴግ መሠረታዊ ባህሪ ጋር ተመሳሳይ የሆኑ የሕዝብን አንድነት የሚነኩ፣ የተዛባውን የፌዴራሊዝም ጉዳዮች እንደገና የሚታዩ መሆኑንም ጠቁመዋል።

አዲሱ ህገ-መንግስት በማርቀቅ ሂደት ላይ ታላላቅ ምሁራን የተሳተፉበት መሆኑን ያስረዱት ኢንጂነሩ ውይይቱ በቅርቡ የትና መቼ እንደሚደረግ ፓርቲው ያሳውቃል ብለዋል።

በተያያዘ ባለፈው ዕሁድ ፓርቲው የጠራው ሰልፍ አለመካሄዱን በተመለከተ ኢንጂነር ይልቃል ተጠይቀው ሕጋዊው ስርዓት የውሸት እንደሆነ፣ ኢህአዴግ ትልቅ የህዝብ ፍርሃት እንዳለበትና ሕዝባዊ ተቀባይነቱ ባዶ እንደሆነ የተገነዘብንበት አጋጣሚ ነበር ሲሉ መልሰዋል።

ባለፈው እሁድ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም ፓርቲው የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት በኩል ጃንሜዳ ማካሄድ እንደሚችሉ በመግለፅ በአንፃሩ ሰማያዊ ፓርቲ ሰልፉን ለማካሄድ የጠየኩት መስቀል አደባባይ ነው በማለቱ ሰላማዊ ሰልፉ ከፓርቲው ጽ/ቤት በግምት አንድ መቶ ሜትር ከተካሄደ በኋላ ግንፍሌ ድልድይ ላይ በፖሊስ እንዲቋረጥ መደረጉ አይዘነጋም፡፡ (ሰንደቅ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule