በብዙ መልኩ ዴሞክራሲያዊ ገፅታን ያልተላበሰው ኢሕአዴግ ራሱን በገዥ መደብነት "አመቻችቶ" አስቀምጧል፡፡ ግንባሩ በቀደመው ዓመት አስረኛ ድርጅታዊ ጉባኤውን በዝግ በማካሄድ እንደተለመደው ባለ ዘጠኝ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት አጠናቋል፡፡ በዚሁ ጉባኤ፣ ከዚህ ቀደም ከተካሄዱ ጉባኤዎች በተለይም በ1994 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ከተካሄደው አራተኛው የድርጅቱ ጉባኤ ጀምሮ ይነሱ የነበሩ አጀንዳዎች ቅርፃቸውን ብቻ በመቀየር ይዘታቸውን እንደጠበቁ እስከ አስረኛው ድርጅታዊ ጉባኤ ድረስ ዘልቀዋል፡፡ በተለይም የመልካም አስተዳደር እጦትና የሙስና ጉዳይ ከድርጅቱ ጋር አብረው የተፈጠሩ እስኪመስሉ ድረስ ችግሮቹ ገንግነዋል፡፡ በ1994ዓ.ም የአዲስ አበባው ጉባኤ አብይ አጀንዳ በመሆን ጉባይተኛው የተወያየበት አጀንዳ "ጥገኛ ዝቅጠት አስተሳሰብ" የስርዓቱ አደጋ መሆኑን ነበር፡፡ የቃላት ሃብታሙ … [Read more...] about ነገረ – ኢሕአዴግ
Politics
ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ሳሞራ የኑስ ህወሃትን ለብሰው፣ ህወሃትን አጥልቀው (ጫማቸውና ሌላው አይታይም እንጂ) ህወሃትን ሆነው ታይተዋል፡፡ “ተጋብዘው ነው” ለማለት ለምትፈልጉ እንትኖች መልሱ ህወሃት ላይ ተጋብዘው ከተገኙ ወደፊት እንደ ሰማያዊ፣ መድረክ፣ ወዘተ ያሉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ የፓርቲዎቹ አርማ ያለበት ባርኔጣ አድርገው ይገኛሉ ማለት ነው - የተነፈሰ ሃሳብ ነው፡፡ ሳሞራ ህወሃትን ሲያይ ዋለ ተቃዋሚ ፓርቲ የት ነሽ እያለ ከነጠላው ፉከራ መልስ - “ሕገመንግሥቱ” ያለጥርጥር ተጥሷል፤ ይህ ከሆነ ደግሞ “ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ …” በሚል ክስ መመሥረት አለበት ማለት ነው፡፡ ይህ ሲሆን ተከሳሽ “አሸባሪ” ሊባል ነው፡፡ ከዚያ ተከሳሽ ወደ … የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር … [Read more...] about ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?
ልጅ የአባቱን ልደት ሲያከብር
በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡ ኢትዮጵያ የምትባለው አገር ጠ/ሚ/ር እንደሆኑ የሚነገርላቸው ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ የሻዕቢያን ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ የትኛውን ሻዕቢያ እንደሆነ በግልጽ ሳይጠቅሱ ሻዕቢያ እየወጋን ነው፤ ሕዝብን አስፈቅደን እርምጃ እንወስዳለን ማለታቸው አይዘነጋም፡፡ ለኤርትራ ተቆርቋሪነታቸው ወደር የሌለውና ይህም “የኤርትራ ሕዝብ ትግል ከየት ወደየት” የሚል መጽሐፍ እስኪጽፉ ያደረሳቸው ሞት የቀደማቸው መለስ በኢትዮጵያ የሻዕቢያ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ነበሩ፡፡ በዚሁ መጽሃፋቸው ላይ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው በማለት እምዬ ምኒልክን እንደ ቅኝ ገዢ የአውሮጳ ነገሥታት ኢትዮጵያንም እንደ ቅኝ ገዢ አውሮጳዊ አገር በማድረግ በማንም ቅኝ … [Read more...] about ልጅ የአባቱን ልደት ሲያከብር
ኦባማ “ልማታዊ” ጎብኚ?!
ለሁለት ቀናት በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደረጉት የአሜሪካው ፕሬዚዳንትና አጃቢዎቻቸው ለሁለት ቀን አዳር ለሆቴል ያወጡት ወጪ ከ27 ሚሊዮን ብር በላይ እንደነበር ተገለጸ፡፡ ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ የሚያደርጉት ጉብኝት በአንድ ሆቴል ብቻ እንደሚደረግ አስቀድሞ የተነገረ ቢሆንም የአስተዳደራቸው ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ አጃቢዎቻቸውና ሌሎች የደኅንነት ሠራተኞች በአራት ሆቴሎች ውስጥ አርፈው እንደነበር Weekly Standard የክፍያ ሰነዶችን በማስደገፍ ይፋ አድርጓል፡፡ አስቀድሞ የተለቀቀው መረጃ እንደሚያመለክተው የኦባማ ቡድን በሒልተን ሆቴል ቆይታ እንደሚያደርግና ወጪውም ብር 8,491,127.81 ወይም በግምት ዶላር $ 412,390.86 መሆኑን የሚያሳይ የኮንትራት ውል መፈረሙን ነበር፡፡ ከአሜሪካ መንግሥት የተጠያቂነት ቢሮ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው የፕሬዚዳንቱ ቡድን ለሁለት ቀናት … [Read more...] about ኦባማ “ልማታዊ” ጎብኚ?!
የድህረ-መለሱ ኢሕአዴግ አሰላለፍና የ“አዲሱ” ሥራ አስፈጻሚ የቢሆን ዕድል
የአራት ድርጅቶች ስብሰብ የሆነው ኢሕአዴግ፤ በሕወሓታዊ የድርጅት መንፈስ እየተመራ የስልጣን ቆይታ ዘመኑን ከአመታት ልኬት ወደ አስርታት ያሻገረ በመሆኑ፣ ከእንግዲህ የአገዛዝ ዘመኑን በክፍለ ዘመን ክፋይ አገላለጽ መጥራቱ ተራዛሚ የስልጣን ቆይታውን ይበልጥ የሚገልፀው ይሆናል፡፡ እናም ሩብ ክፍለ ዘመን ያህል በስልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ በሰሜን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ተዋረድ አገሪቱን “እየመራ” እዚህ ደርሷል፡፡ ግንባሩ ከፊት ለፊቱ አንደ “ትልቅ” ድርጅታዊ ጉባኤ ይጠብቀዋል፡፡ ነሐሴ 20/2007 ዓ.ም በመቀሌ ከተማ የድርጅቱ አስረኛ ጉባኤ መካሄድ ይጀምራል፡፡ የመቀሌው ጉባኤ ከመካሄዱ ከቀናት በፊት፣ አራቱም ድርጅቶች በየክልል ርዕስ ከተማቸዉ የየራሳቸውን ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ የድርጅታችዉን ሊቀ-መንበርና ም/ሊቀመንበር የሚመርጡ ይሆናል፡፡ ዛሬ ላይ እየታየ ካለው የግንባሩ ከፍተኛ … [Read more...] about የድህረ-መለሱ ኢሕአዴግ አሰላለፍና የ“አዲሱ” ሥራ አስፈጻሚ የቢሆን ዕድል
የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር የባንክ ሒሳብ ውስጥ የተገኘው 675 ሚሊዮን ዶላር የማን ነው?
የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነጂብ ራዛክ የግል የባንክ ሒሳብ ውስጥ 675 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሆኖ ተገኘ፡፡ ይህም ገንዘብ ከየት እንደተገኘ የአገሪቱ የፀረ ሙስና ኮሚሽን በምርመራ እንዲያጣራ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተፅዕኖ እያደረጉ ናቸው፡፡ ኮሚሽኑ ባለፈው ሰኞ እንደገለጸው፣ 675 ሚሊዮን ዶላር ያህል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ የግል ሒሳብ ተዛውሯል፡፡ ይህም ገንዘብ በዕርዳታ የገባ እንጂ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚመራው የአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድ የወጣ አለመሆኑን አመልክቷል፡፡ በአገሪቱ ውዝግብ ያስነሳውና የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግሥት ያንቀጠቀጠው ይኼ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ፣ በአገሪቱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን በዕርዳታ የመጣ ነው ቢባልም፣ ኮሚሽኑ ዕርዳታውን የሰጠውንም ሆነ በባንክ አካውንቱ ያስቀመጠውን ግለሰብ ወይም አካል አላሳወቀም፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ ሊያድበሰብስ … [Read more...] about የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር የባንክ ሒሳብ ውስጥ የተገኘው 675 ሚሊዮን ዶላር የማን ነው?
የአብዮቱ አይቀሬነትና ጥቁምታዎቹ!
በፖለቲካ ሳይንስ መዝገበ ቃላት ውስጥ “አብዮት” የሚለው ቃል “አዲስ ሥርዓትን በመሻት የነባሩን መንግስታዊ ወይም ማህበራዊ ሥርአት በግዳጅ ማስወገድ” በሚል የትርጉም ማዕቀፍ ላይ ሊያርፍ ይችላል፡፡ ‹የሰው ልጅ አብልጦ የሚሻው የተሻለ የፖለቲካ ሥርዓት በየአገራቱ አስካልተመሰረተ ድረስ አብዮት በየትኛውም የዓለም ክፍል አይቀሬ ክስተት› እንደሆነ የፖለቲካ ሳይንስ መምህራኑ አብዝተው ያስተምራሉ፡፡ ሰሚ የለም እንጂ፡፡ ኢህአዴግ የሚባል ገዥ መደብ ፣ ሩብ ክፍለ ዘመን ያህል አገሪቱን እንደ “መንግስት” በመራበት ተራዛሚ የአገዛዝ ዘመኑ ከፍ ሲል ከአምሮ በላይ የሆኑ፣ ስልጣን ላይ በወጣ ስብስብ ይፈፀማሉ ተብለው የማይታሰቡ ውስብስብ የፖለቲካ ሴራዎችን በመስራት ያደረሰው ሰብአዊ ውድመት፤ ዝቅ ሲል ደግሞ ከሰውነት በታች በወረደ የዝቅተኝነት ስሜት በዜጎች ላይ እያደረሰ ያለው የማህበረ ኢኮኖሚ … [Read more...] about የአብዮቱ አይቀሬነትና ጥቁምታዎቹ!
ኦባማ የአፍሪካን ገዢዎች እያዋዛ ደቆሳቸው!
ኦባማ በአፍሪካ ኅብረት ያደረገው ንግግር ብዙ ጥያቄዎችን መልሷል፤ የኦባማ ጉብኝት ያስከተለው ጫጫታ ሁሉ መልስ አገኘ፤ የሰው ልጆች በመሀከላቸው ምንም ዓይነት የአድልዎ ልዩነት ሳይደረግባቸው በሰውነታቸው ብቻ በተፈጥሮ ያገኙትን ክብራቸውንና ሞገሣቸውን አስከብረው መኖር እንዳለባቸው በአጽንኦት ተናገረ፤ ዛሬ የአሜሪካኑ ፕሬዚደንት ያደረገው ንግግር ከፕሬዚደንትና ጠቅላይ ሚኒስትር ጀምሮ እስከ ፖሊሶች፣ መርማሪዎችና አዛዦቻቸው፣ እስከጦር ኃይሉና አዛዦቻቸው፣ አስከዓቃብያነ ሕግና ዳኞች፣ እስከወህኒ ቤት ጠባቂዎችና አዛዦች በየሥልጣን ተዋረዱ ላይ ሆነው የኢትዮጵያውያንን የሰውነትና የዜግነት እኩልነት አፈራርሰው በጎሣ መሠረት ላይ ሊበታትኑት የሚሞክሩትን በኃይለኛ ቃላት ከመሬት በታች ከቶአቸዋል፤ ማሰብና ማስተዋል የጎደለው፣ ከአፍንጫ የራቀ አመለካከት የሌለበት፣ አገርን የሚያጠፋ፣ ከሰውነት ጎዳና … [Read more...] about ኦባማ የአፍሪካን ገዢዎች እያዋዛ ደቆሳቸው!
ለህወሃት/ኢህአዴግና መሰል የአፍሪካ አምባገነኖች የባራክ ኦባማ መልዕክት
በቅድሚያ ለህወሃት/ኢህአዴግ “የአንድን አገር (ኅልውና በማስጠበቅ) አንድ አድርጎ ማቆየት የሚችለው መሪው (ወይም በኢህአዴግኛ ፓርቲው ወይም ግምባሩ) እርሱ ብቻ እንደሆነ የሚናገር ከሆነ ያ መሪ (ፓርቲ ወይም ግምባር) አገሩን ከመገንባት ከሽፏል ማለት ነው … ማንም ሰው (ፓርቲ/ግምባር) ዕድሜልኩን መሪ/ፕሬዚዳንት መሆን የለበትም፤ አዲስ ሃሳብና ትኩስ ኃይል ወደ ሥልጣን ሲመጣ ያቺ አገር ከቀድሞው እየተሻለች ትሄዳለች፡፡” ቀጠሉ - “ሰዎች ለረጅም ጊዜ በሥልጣን ለምን መቆየት እንደሚፈልጉ እኔ አይገባኝም፤ በተለይ ብዙ ገንዘብ እያላቸው …” ልማታዊ አምባገነኖቹን የሚመለከት ነበር፡፡ ለሕገመንግሥት ቀያሪዎችና ሕግ አሻሻዮች “አንድ መሪ በሥልጣን ለመቆየት በጨዋታው መሃል ሕግ ለመቀየር ሲሞክር (በዚያች አገር) ያለመረጋጋትና የነውጥ አደጋ ያስከትላል፡፡” ራሳቸውን ከአፍሪካ “ዘላለማዊና … [Read more...] about ለህወሃት/ኢህአዴግና መሰል የአፍሪካ አምባገነኖች የባራክ ኦባማ መልዕክት
“ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ”
"ኦባማ ኢህአዴግን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የተመረጠ ነው ማለታቸው የኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ግንባታ ላይ ውሃ የሚቸልስ ነው" የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የኢትዮጵያ መንግስት ዛሬ ሀምሌ 20/2007 ዓ.ም ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ ቤተ መንግስት ውስጥ ለአሜሪካው ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ የሚያደረገው የእራት ግብዣ ላይ እንደማይገኙ ለነገረ ኢትየጵያ ገልጸዋል፡፡ የራት ግብዣው ላይ በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጥሪ የተደረገላቸው ኢ/ር ይልቃል "አሸባሪ አድርጎ የሚቆጥረን ኢህአዴግ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ሲመጡ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ ለማስመሰልና ዕውቅና ለማግኘት ያደረገው በመሆኑ አልገኝም" ብለዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል አክለውም "የኢትዮጵያ ህዝብ ጭቆና እና ስቃይ ውስጥ ባለበት በአሁኑ ወቅት ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ … [Read more...] about “ኢህአዴግ የጠራው የቅንጦት ግብዣ ላይ መገኘት የህዝቡን ሰቆቃ እንደመርሳት እቆጥረዋለሁ”










