• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር የባንክ ሒሳብ ውስጥ የተገኘው 675 ሚሊዮን ዶላር የማን ነው?

August 10, 2015 10:48 am by Editor Leave a Comment

የማሌዥያ ጠቅላይ ሚኒስትር ነጂብ ራዛክ የግል የባንክ ሒሳብ ውስጥ 675 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ሆኖ ተገኘ፡፡ ይህም ገንዘብ ከየት እንደተገኘ የአገሪቱ የፀረ ሙስና ኮሚሽን በምርመራ እንዲያጣራ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተፅዕኖ እያደረጉ ናቸው፡፡

ኮሚሽኑ ባለፈው ሰኞ እንደገለጸው፣ 675 ሚሊዮን ዶላር ያህል ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ የግል ሒሳብ ተዛውሯል፡፡ ይህም ገንዘብ በዕርዳታ የገባ እንጂ፣ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚመራው የአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድ የወጣ አለመሆኑን አመልክቷል፡፡

በአገሪቱ ውዝግብ ያስነሳውና የጠቅላይ ሚኒስትሩን መንግሥት ያንቀጠቀጠው ይኼ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ፣ በአገሪቱ ፀረ ሙስና ኮሚሽን በዕርዳታ የመጣ ነው ቢባልም፣ ኮሚሽኑ ዕርዳታውን የሰጠውንም ሆነ በባንክ አካውንቱ ያስቀመጠውን ግለሰብ ወይም አካል አላሳወቀም፡፡ በመሆኑም ኮሚሽኑ ሊያድበሰብስ የፈለገው ጉዳይ አለ ተብሎ እየተጠረጠረ ነው፡፡

የተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆኑ ሕዝቡ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት የገባው ገንዘብ ከማሌዥያ ኢንቨስትመንት ዴቨሎፕመንት ነው በማለት ቢወነጅሉም፣ ከፈንዱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ምንም ገንዘብ ተሰጥቶም ሆነ በአካውንታቸው ገብቶ እንደማያውቅ የፈንዱ ቢሮ አሳውቋል፡፡

በጠቅላይ ሚኒስትሩ እ.ኤ.አ. በ2009 የተመሠረተው የማሌዥያ ኢንቨስትመንት ፈንድ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ መሽመድመዱንና ወደ 11 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ብድር እንዳለበት ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ግልጽ አሠራር የለውም እየተባለም ይተቻል፡፡

እ.ኤ.አ. በሐምሌ 2015 መጀመርያ ላይ የዎል ስትሪት ጆርናል ሪፖርት፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ አካውንት ውስጥ 700 ዶላር ገቢ መሆኑን አትቶ ነበር፡፡

ከዚያ ጊዜ ወዲህ ሚኒስትሩ ለአገሪቱ ልማት የሚውለውን ፈንድ ለግል ጥቅም እንዳላዋሉ፣ በስማቸው የተቀበሉት ገንዘብ እንደሌለና ጆርናሉን በስም ማጥፋት ወንጀል እንደሚከሱ ሲናገሩ ከርመዋል፡፡

ውንጀላው ከተሰነዘረባቸው ጀምሮም በጉዳዩ ዙርያ የሚሞግቷቸውን ሁሉ ከሥልጣን ማስወገድ ይዘዋል፡፡ ባለፈው ሳምንትም የአገሪቱን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ሙሃይዲን ያሲን፣ እንዲሁም ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አብዱል ጋኒን ከሥልጣን አስወግደዋል፡፡

በጠያቂነታቸውና ተሟጋችነታቸው የሚታወቁትን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉን ጨምሮ አራት የካቢኒ አባላት ከሥልጣን ማስወገዳቸውን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሰጡት መግለጫም፣ የካቢኒ አባላት በመሉ በአገሪቱ መከፋፈልን ሊያመጣ የሚችልና ከመንግሥት አጀንዳ የተቃረነ ሐሳብ በግልጽ መወያየት እንደማይችሉ አሳውቀዋል፡፡

ጠቅላይ ዓቃቤ ሕጉ ጋኒ የማሌዥያ ኢንቨስትመንት ዴቨሎፕመንት ፈንድ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት ገብቶ እንደሆነ ከሚያጣራው ፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ ከማሌዥያ ማዕከላዊ ባንክ፣ እንዲሁም ከፖሊስ ጋር እየሠሩ ነበር፡፡ ከሥራ ከመታገዳቸው አስቀድሞም በጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት ውስጥ የገባው ገንዘብ ከአገሪቱ ልማት ፈንድ ጋር ግንኙነት እንደነበረው የሚያስረዳ ዶክመንት ደርሷቸው ነበር፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አራት ከፍተኛ ባለሥልጣናትን ከሥራ ሲያስወግዱ የሁለት መገናኛ ብዙኃንን የሥራ ፈቃድም አግደዋል፡፡

የአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድ ላይ የተሠራ ሽፍጥ አለ በመባሉ ምክንያት፣ ተከትሎ በማሌዥያ ዋና ከተማ ኳላላምፑር ውጥረት ነግሷል፡፡ የታቃውሞ ሠልፍም ተካሂዷል፡፡ ተቃውሞ አድራጊዎችም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሥራ ይልቀቁ ብለው መጠየቃቸውን ዘ ጋርድያን ዘግቧል፡፡

ከተቃውሞ ሰልፍ ጋር በተያያዘ 29 ሰዎች የታሰሩ ሲሆን፣ ክስ የተመሠረባቸውም በአገሪቱ እስከ 20 ዓመት እስራት በሚያስፈርደው ያልተፈቀደ ተቃውሞ ላይ በመሳተፍ ተብሎ ነው፡፡

በአገሪቱ የኢንቨስትመንት ፈንድና በጠቅላይ ሚኒስትሩ አካውንት ላይ ምርመራ እየተደረገ ቢሆንም፣ የኮሚሽኑ ውጤት ሚስተር ራዛክን ከጥፋተኝነት የሚያድን ሊሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬን ፈጥሯል፡፡

ከምርመራው ጋር ተያይዞ የዴሞክራቲክ አክሽን ፓርቲ አባልና የፓርላማው መሪ ሚስተር ሊም ኪት ሲያንግ፣ የዚህን ድርጊት ውጤት ማሌዥያውያንና የዓለም ሕዝቦች በትኩረት እየተከታተሉት ነው ብለዋል፡፡

‹‹ጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ የማሌዥያ መሪ ሆነው ለመቆየት ከፈለጉ ከእንዲህ ዓይነቱ ሙስና የፀዱ ለመሆናቸው ማሌዥያውያንን ማሳመን ይጠበቅባቸዋል፤›› ሲሉም ተደምጠዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለግል ጉዳያቸው ምንም ዓይነት ገንዘብ እንዳልወሰዱ ገልጸው፣ ውንጀላው ከሥልጣናቸው እንዲወርዱ ሆን ተብሎ የተጠነሰሰ ሴራ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ባለቤታቸው ሮዝማህ ማንሱር በጣም አባካኝና የተደላደለ የቅንጦት ሕይወት የሚወዱ በመሆናቸው፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዚህ ጋር ተያይዞ ስማቸው እየተብጠለጠለ ነው፡፡

ሒዩማን ራይት ስዎች የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. በኳላላምፑር የሚካሄደውን ስብሰባ ለመሳተፍ መምጣታቸውን አስመልክቶ፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ራዛክ ጋር በጉዳዩና በሰብዓዊ መብት ጉዳይ ላይ እንዲነጋገሩ ጥሪ አቅርቧል፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Filed Under: News, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule