ለ900ሺ አስቸኳይ እርዳታ የሚያስፈልገው ህዝብ የእርዳታ እህል የጫኑ መኪኖች ሰሙኑን መቀሌ ከተማ ደርሰዋል።
አንድ ሚሊዮን ለሚጠጋ ተረጂ እስከ 350 መኪኖች እህል ጭነው በቀጥታ ከጅቡቲ ትግራይ ገብተዋል።
መንግስት እንዳለው የጫኑት ኢትዮጵያ ውስጥ የተመረተ ሳይሆን ከውጭ በእርዳታ የገባ መሆኑ ጭነው የመጡት ሹፌሮች አውግተውኛል።
“ድርቁ በቁጥጥር ስር ኣውለነዋል” የሚል የትግራይ መንግስት መግለጫ ተደጋግሞ እየተሰማ ባለበት ቅፅበት “ለእርዳታ የመጣው እህል እየተሸጠ ነው” የሚል ወሬ በስፋት እየተሰማ ነው።
እህሉ መቀሌ ከተማ ወደሚገኙ የዱቄት ፋብሪካዎች እየተሸጠ መሆኑና ጥያቄ ላነሱ ሹፌሮች ደግሞ “ድርቁን በቀላሉ ስለተቆጣጠርነው ትርፉ ተሽጦ ለአባይ እንዲሆን ተወስኗል” ተብሎዋል።
ከእኔ ጋር ሁኖ ጨዋታው ሲያዳምጥ የነበረው ወጣት “… የትኛው አባይ ነው? አባይ ግድብ፣ አባይ ወልዱ፣ ወይስ አባይ ፀሃዬ …” ብሎ ጠይቋል።
የትግራይ ገዢዎች ድርቁም እህሉም በቁጥጥራቸው ስር ያዋሉ ይመስላሉ …!!! ድርቅ ካጠቃው፣ ህይወቱ በአደጋ ውስጥ ከገባ፣ ህይወቱን ለማቆየት የጎረሳት ማቆያ ምግብ ከጉሮሮው የሚቀሙ ሌቦች እንጠብቀው።
ኤፍ ኤም ፋና ትግርኛ ፕሮግራም ምስጋና ይድረሳቸውና ትንሽ ብትሆንም የድርቁ ሰለባ ወገኖች ድምፅ አሰምተውናል።
“ወጣቱ ስደት ከመሄድ ትንሽ ተረጋግቶ ነበር። ኣሁን በድርቁ ምክንያት ፈርቶ ባህር እየገባ ነው … ተማሪዎች በዚህ ሁኔታ መማር ኣንችልም ብለው ቤት እየዋሉ ነው … ከ8 ሺ በላይ የቀበሌያችን ከብቶች በምግብና ውሃ እጦት ክፉኛ ተደርቀውብናል … መንግስት ቶሎ ሊደርስልን ይገባል … ” ብለው ሲናገሩ ሰምተናል።
ነፃነትና ኣብ ኢድና እያ…!
IT IS SO……
“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡
Martha Teklu says
The present situation in Ethiopia is caused by the mastermind of Woyanes. For any cause, it has its effect. If one uses its power to exploit the country, deposit billion of dollars in the U.S. , European and Asian banks, the exploited country does not have the capital to invest in any production. Our Ethiopian lands are sold or leased to foreign investors, Our young girls are sold to Middle East households in a modern time slavery system. The name may not be slavery, but the system is the same. Our young men, having no means of survival, are driven in search of wages under very harsh, risky and illegal journeys to the unknown. At the same time, we see Woyane investors and tourists sipping coffee and counting their investment growing in the US or other foreign countries. The law of the country is not to serve the population but solely to serve the interest and wellbeing of the Woyanes. The citizens of Ethiopia are subjected to scramble for anything edible, be homeless and accept their lot. If one is a strong supporter of Woyanes, he might receive some “lifach” or scrap of favors. In my own country and birth place, I will be persecuted because I will and not support the “hoddam” woyanes. The U.S. is satisfied with the actions of Woyanes. What business brings billions of dollars to this country; what country will send its young army to fight for the US and still continue to be a “yes” men. There is no law that says the US has to abide to the needs of oppressed people. One has to be an enemy of the US to be criticized for human rights violations and it does not apply to your “server”.
Tesfa says
Martha
Be assured, you are not alone in this fight. There are millions who share your opinion.
thank you,