• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እናንተ እውነትን የምትደባብቁ ነግ በኔ በሉ!!

December 3, 2015 10:44 am by Editor Leave a Comment

ኢቢሲ “በቀኑ ዜና እወጃየ በጎንደር ማረሚያ ቤት ትላንት በደረሰው የእሳት ቃጠሎ የሞተ ሰው የለም ብየ የዘገብኩት ኮማንደር ሰይድ ሃሰን የሚባሉ የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ “ዋሽተው” መረጃ ስለሰጡኝ ነው … ሃቁ ግን 17 እስረኞች ከእሳቱ ለማምለጥ ሲሞክሩ እርስ በእርስ ተረጋግጠው ህይወታቸው አልፏል ይህንንም የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሸን ኮሚሽነር አስተዳደር ሃላፊ በላይ ዘለቀ የሚባሉ (ስሙንማ ይዘውታል) ገልፀውልኛል” ሲል ማምሻውን አስተባብሏል … (አላግጧል) መቸስ የሞተ ሰው የለም ብለው 17 ከሞተ … 17 ሰው ብለው ካመኑ የሟቹ ትክክለኛ ቁጥርም ሌላ ሊሆን ይችላል!! የሆነ ሁኖ ከዚህ የተዘበራረቀ አሳፋሪ ዜና … ሁለት ነገር ተረዳሁ …

1ኛ፡ ብሔራዊ ቴሌቪዥናችን ያልተረጋገጠ መረጃ የሚያቀርብ ግድ የለሽ ተቋም መሆኑን አውቀናል፤
2ኛ፡ ማረሚያ ቤቶቻችን በስራቸው ላሉት ዜጎች ህይዎት እንኳን ግድ በሌላቸው ውሸታም አልያም በስራቸው ባለ ማረሚያ ቤት ስለሚከናወነው ነገር ምንም እውቀት በሌላቸው ሰዎች እንደሚመሩ አጋጣሚው ነግሮናል፤

gondar17 ሰውኮ እጅግ ብዙ ነው … የሃዘን ቀን ሁሉ በመላው ኢትዮጵያ መታወጅ ያለበት ጉዳይ ነው … 17 ኢትዮጵያዊያን የሚያድናቸው አጥተው በማረሚያ ቤት ማለቃቸው ብሔራዊ ውርደት አቅመ ቢስነት ነው!! በዚህ ላይ የጋዜጠኞቹ ወሽካታነትና ከህዝቡ ሃዘን በላይ ተቋሞቹ ለማይረባ ፖለቲካቸው ማሰብ ያሳፍራል!!

ጋዜጠኞች በተለይ በዓል እና ድግስ በያለበት ለመገኘት ማንም የማይቀድመው የክልሉ ቴሌቪዥን በወቅቱ ከማንም በፊት በቦታው መገኘት እና ትክክለኛ መረጃ ማድረስ ነበረበት … ቢሯቸው ተዘፍዝፈው በስልክ ሰው አልሞተም … ተሳስተን ነው ሙቷል እያሉ የሚዘላብዱት ምናይነት አሳፋሪ ሙያዊ ስነምግባር ቢኖራቸው ነው?

ደግሞ ኢቢሲ “ስህተቱ የአቶ እከሌ ነው፤ እርማቱ የማንትስ ነው” እያለ የሚቀልደው የመንደር እድር ወይም የቤተ ዘመድ ጉዳይ መሰለው እንዴ?? ይሄ አንገብጋቢ የሆነ አገራዊ ጉዳይ ነው … መንግስት እኔ እጠብቃቸዋለሁ ብሎ በራሱ ሃላፊነት ስር ያስቀመጣቸውን የህዝብ ልጆች መነሻው ምንም ይሁን ምን የሞታቸው ምክንያት እሳቱም ይሁን “እርግጫ” ወይም ሌላ … ብቻ ሃላፊነቱን ባለመወጣቱ 17 ወገኖቻችን ህይወታቸው አልፏል!!

ለሟች ወገኖች መፅናናትን እየተመኘሁ መንግስትም ሆነ በመንግስት ትዕዛዝ የምትንቀሳቀሱ የሚዲያ ተቋማት ይህን ጉዳይ በዘገባችሁበት ግዴለሽና አሳፋሪ አዘጋገብ ለእናተም ቤተሰብና ላቆሰላችሁት ኢትዮጲያዊ ሁሉ ፈጣሪ የሚያፅናና ቀን ያምጣ ከማለት ሌላ የምለው የለኝም!!

(Alex Abreham አሌክስ አብርሃም)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule