• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እናንተ እውነትን የምትደባብቁ ነግ በኔ በሉ!!

December 3, 2015 10:44 am by Editor Leave a Comment

ኢቢሲ “በቀኑ ዜና እወጃየ በጎንደር ማረሚያ ቤት ትላንት በደረሰው የእሳት ቃጠሎ የሞተ ሰው የለም ብየ የዘገብኩት ኮማንደር ሰይድ ሃሰን የሚባሉ የማረሚያ ቤቱ ሃላፊ “ዋሽተው” መረጃ ስለሰጡኝ ነው … ሃቁ ግን 17 እስረኞች ከእሳቱ ለማምለጥ ሲሞክሩ እርስ በእርስ ተረጋግጠው ህይወታቸው አልፏል ይህንንም የአማራ ክልል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሸን ኮሚሽነር አስተዳደር ሃላፊ በላይ ዘለቀ የሚባሉ (ስሙንማ ይዘውታል) ገልፀውልኛል” ሲል ማምሻውን አስተባብሏል … (አላግጧል) መቸስ የሞተ ሰው የለም ብለው 17 ከሞተ … 17 ሰው ብለው ካመኑ የሟቹ ትክክለኛ ቁጥርም ሌላ ሊሆን ይችላል!! የሆነ ሁኖ ከዚህ የተዘበራረቀ አሳፋሪ ዜና … ሁለት ነገር ተረዳሁ …

1ኛ፡ ብሔራዊ ቴሌቪዥናችን ያልተረጋገጠ መረጃ የሚያቀርብ ግድ የለሽ ተቋም መሆኑን አውቀናል፤
2ኛ፡ ማረሚያ ቤቶቻችን በስራቸው ላሉት ዜጎች ህይዎት እንኳን ግድ በሌላቸው ውሸታም አልያም በስራቸው ባለ ማረሚያ ቤት ስለሚከናወነው ነገር ምንም እውቀት በሌላቸው ሰዎች እንደሚመሩ አጋጣሚው ነግሮናል፤

gondar17 ሰውኮ እጅግ ብዙ ነው … የሃዘን ቀን ሁሉ በመላው ኢትዮጵያ መታወጅ ያለበት ጉዳይ ነው … 17 ኢትዮጵያዊያን የሚያድናቸው አጥተው በማረሚያ ቤት ማለቃቸው ብሔራዊ ውርደት አቅመ ቢስነት ነው!! በዚህ ላይ የጋዜጠኞቹ ወሽካታነትና ከህዝቡ ሃዘን በላይ ተቋሞቹ ለማይረባ ፖለቲካቸው ማሰብ ያሳፍራል!!

ጋዜጠኞች በተለይ በዓል እና ድግስ በያለበት ለመገኘት ማንም የማይቀድመው የክልሉ ቴሌቪዥን በወቅቱ ከማንም በፊት በቦታው መገኘት እና ትክክለኛ መረጃ ማድረስ ነበረበት … ቢሯቸው ተዘፍዝፈው በስልክ ሰው አልሞተም … ተሳስተን ነው ሙቷል እያሉ የሚዘላብዱት ምናይነት አሳፋሪ ሙያዊ ስነምግባር ቢኖራቸው ነው?

ደግሞ ኢቢሲ “ስህተቱ የአቶ እከሌ ነው፤ እርማቱ የማንትስ ነው” እያለ የሚቀልደው የመንደር እድር ወይም የቤተ ዘመድ ጉዳይ መሰለው እንዴ?? ይሄ አንገብጋቢ የሆነ አገራዊ ጉዳይ ነው … መንግስት እኔ እጠብቃቸዋለሁ ብሎ በራሱ ሃላፊነት ስር ያስቀመጣቸውን የህዝብ ልጆች መነሻው ምንም ይሁን ምን የሞታቸው ምክንያት እሳቱም ይሁን “እርግጫ” ወይም ሌላ … ብቻ ሃላፊነቱን ባለመወጣቱ 17 ወገኖቻችን ህይወታቸው አልፏል!!

ለሟች ወገኖች መፅናናትን እየተመኘሁ መንግስትም ሆነ በመንግስት ትዕዛዝ የምትንቀሳቀሱ የሚዲያ ተቋማት ይህን ጉዳይ በዘገባችሁበት ግዴለሽና አሳፋሪ አዘጋገብ ለእናተም ቤተሰብና ላቆሰላችሁት ኢትዮጲያዊ ሁሉ ፈጣሪ የሚያፅናና ቀን ያምጣ ከማለት ሌላ የምለው የለኝም!!

(Alex Abreham አሌክስ አብርሃም)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule