• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኢኮኖሚው [እንዳወራነው] አላደገም!

October 20, 2015 08:12 pm by Editor Leave a Comment

በነጻ አውጪ ስም ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር – ህወሃት ሰሞኑን ዕቅድ ብሎ ባወጣው ዘገባ ላይ ለዓመታት ሲወራለት የነበረው የድርብ አኃዝ ዕድገት እንደተደሰኮረለት እንዳልሆነ እንዲያውም ኢኮኖሚው ውድቀት ላይ መሆኑን የሥራ አጥነት ሁኔታ አሳሳቢ ከመሆኑ የተነሳ በከተማዎች ብቻ ሳይሆን በገጠርም ችግር እየሆነ መምጣቱን ለራሱ ባመነበት የኢኮኖሚ ፕላን ላይ አትቷል፡፡ ነገረ ኢትዮጵያ/Negere Ethiopia በፌስቡክ ገጹ ላይ ያወጣው ዘገባ ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡-

መንግስት ኢኮኖሚው ውድቀት ላይ መሆኑን አመነ

• የኢኮኖሚ መዋቅሩ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራትም ያነሰ ነው

• የወጪ ንግድ ገቢ እና የገቢ ንግድ ክፍተት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል

• ለውጭ ገበያ የቀረበው አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ ሰሊጥና የጥራጥሬ ሰብሎች መጠን በእቅዱ ከተያዘው በእጅጉ ያነሰ ነው

• ለውጭ ይቀርባል ተብሎ ከታቀደው ቡና የቀረበው ሩቡ ብቻ ነው

• መስራት የሚቻለውን ያህል የልማት ሥራ ሳይሰራ ቀርቷል

• ሥራ አጥነት በከተማ ብቻ ሳይሆን በገጠር አካባቢዎችም ሰፊ ችግር ሆኗል

ላለፉት 10 አመታት ኢትዮጵያ 11.2 በመቶ በማደግ በዓለም ፈጣን እድገት እያሳዩ ከሚገኙ ጥቂት ሀገራት መካከል አንዷ እንደሆነችና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ሀገራት ጋር ልትመደብ እንደሆነ ሲናገር የነበረው ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የኢኮኖሚ ውድቀት እንዳጋጠመው አመነ፡፡ የብሔራዊ የፕላን ኮሚሽን በመስከረም ወር 2008 ዓ.ም የሁለተኛውን አምስት አመት የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ (ከ2008-2012 ዓ.ም) ላይ ለመወያየት ያዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ እንደሚያሳየው በተለይም መንግስት ለኢኮኖሚው አንቀሳቃሽ ሞተር ነው የሚለው የግብርና ዘርፍ፣ የውጭ ንግድና የማኑፋክቼሪንግ ኢንዱስትሪው ውድቀት አጋጥሞታል፡፡plan

“በአጠቃላይ በተጠናቀቀው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ዘመን የተመዘገበው የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ከሚጠበቀው አንፃር ዝቅተኛ ነው፡፡ የኢኮኖሚው መዋቅር ለውጥ ከማረጋገጥ አንፃር የተመዘገበው አፈፃፀም ዝቅተኛ ነው” ያለው ሰነዱ የኢኮኖሚ መዋቅሩ ከሳህራ በታች ከሚገኙ ሀገራትም ያነሰ እና በጣም ዝቅተኛ መሆኑን አስምሮበታል፡፡ በኢኮኖሚው ችግር ምክንያትም ስራ አጥነት ከከተሞች አልፎ በገጠረ አካባቢዎችም ሰፊ ችግር እንደሆነም ተመልክቷል፡፡

ከሸቀጦች የወጪ ንግድ ይገኛል ተብሎ የተገመተው ገቢ በ2006 ዓ.ም ከነበረውም ያልተለየ፣ ከዚህ ገቢ የተገኘው የገቢ ንግድ (import) ወጪን የመሸፈን አቅሙም በ2007 ዓ.ም ከአለፈው ጊዜ ያነሰ ነው ያለው ሰነዱ፤ በወጪ ንግድ ገቢ (export) ወጪ እና በገቢ ንግድ ((import) ወጪ ያለው ክፍተትና ጉድለት እየሰፋ መጥቶ በ2007 ዓ.ም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል፡፡ የታየው ደካማ የውጭ ንግድ አፈፃፀም አስተማማኝ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት ኢኮኖሚውን ለማሳደግ፣ ከውጭ ብድርና እርዳታ ጥገኝነት ለመላቀቅ ለሚደረገው ጥረት ማነቆ እንደሆነ በሰነዱ ላይ ሰፍሯል፡፡

የውጭ ንግድ መዳከም የውጭ ምንዛሬ ለሚፈልጉትና አቀድኳቸው ላላቸው የመሰረተ ልማት፣ የኢንዱስትሪና የማህበራዊ ልማት እንዳይሳኩ እየፈጠረው ያለው እንቅፋት አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ብሏል፡፡ ለውጭ ገቢ ንግድ መዳከም በዋነኛነት የማምረት አቅም አለማደግ፣ የማኑፋክቸሪንግና የግብርና ሸቀጦች በመጠን፣ በአይነትም፣ በጥራት ማምረት አለመቻሉ እንደሆነ በሰነዱ ላይ ተገልፆአል፡፡

eprdfs economic policyበትራንስፎርሜሽን ዕቅዱ መጨረሻ ለውጭ ገበያ ይቀርባል ተብሎ የነበረው ቡና ሩብ ያህሉን እንኳን ማቅረብ አልተቻለም ያለው ሰነዱ በመጀመሪያው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መጨረሻ ለውጭ ገበያ ይቀርባሉ ተብሎ የነበሩት የአበባ፣ የጨርቃጨርቅና የቆዳ ምርቶችም በቡና ገበያ ላይ ከታየውም በላይ ክፍተት እንደነበረበት በዝርዝር አስቀምጧል፡፡

ሰነዱም “በግብርና ዘርፍ የኤክስፖርት ሰብሎች የሆኑት አበባ፣ አትክልትና ፍራፍሬ፣ ቡና፣ ሰሊጥና የጥራጥሬ ሰብሎች ሲሆኑ ለውጭ ገበያ የቀረበው መጠን ይደረጋል ተብሎ ከታቀደው በእጅጉ ያነሰና በማኑፋክቼሪንግ ነባር ኢንዳስትሪዎችና በከፍተኛ አቅማቸውና በጥራት እንዲያመርቱ፣ በተጨማሪም አዳዲስ ኢንቨስትመንትን በስፋትና በጥራት መልምሎ ወደ ሥራ ማስገባት በታቀደው ልክ ሊፈፀም ባለመቻሉ ለወጪ ንግድ የማምረት አቅማችን ዝቅተኛ መሆኑን ዋና ምክንያቶች ነበሩ” ብሏል፡፡

መንግስት በታክስ አሰባሰብም ትልቅ ክፍተት እንዳለበት ያመነው ሰነዱ “ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት አማካይ አፈፃፀም ለመድረስ በታክስ አስተዳደርና አሰባሰብ ተጨማሪ ጥረት ማደረግ እንዳለብን ያመለክታል፡፡ መሰብሰብ የሚችለው የታክስ ገቢ አለመሰብሰቡ መስራት የሚቻለውን ያህል የልማት ሥራ በዛው ልክ ሳይሰራ ቀርቷል ማለት እንደሆ ከልብ ሊጤን ይገባዋል” ብሏል፡፡


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule