• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልጅ የአባቱን ልደት ሲያከብር

September 1, 2015 09:27 am by Editor 1 Comment

በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡

ኢትዮጵያ የምትባለው አገር ጠ/ሚ/ር እንደሆኑ የሚነገርላቸው ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ የሻዕቢያን ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ የትኛውን ሻዕቢያ እንደሆነ በግልጽ ሳይጠቅሱ ሻዕቢያ እየወጋን ነው፤ ሕዝብን አስፈቅደን እርምጃ እንወስዳለን ማለታቸው አይዘነጋም፡፡

ለኤርትራ ተቆርቋሪነታቸው ወደር የሌለውና ይህም “የኤርትራ ሕዝብ ትግል ከየት ወደየት” የሚል መጽሐፍ እስኪጽፉ ያደረሳቸው ሞት የቀደማቸው መለስ በኢትዮጵያ የሻዕቢያ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ነበሩ፡፡ በዚሁ መጽሃፋቸው ላይ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው በማለት እምዬ ምኒልክን እንደ ቅኝ ገዢ የአውሮጳ ነገሥታት ኢትዮጵያንም እንደ ቅኝ ገዢ አውሮጳዊ አገር በማድረግ በማንም ቅኝ ተገዝታ የማታውቀውን ኢትዮጵያ የቅኝ ገዢነትን “ክብር አጎናጽፈዋታል”፡፡

ባለራዕዩ በዚሁ የሻዕቢያ ተላላኪነታቸው ኢሣያስን እንደ ግለሰብ “አጉራ ዘለል”፣ “ዕብድ” ፣ … እያሉ ከመዝለፍ በስተቀር ሻዕቢያን እንደ ድርጅት በከረረ ቃል ለመናገር ይከብዳቸው እንደነበር አብሮ የሚጠቀስ ቢሆንም በመለስ ፋውንዴሽን ግን የተዘነጋ “ሌጋሲያቸው” ይመስላል፡፡

የዛሬ 54ዓመት ትግል የሚባለውን የጀመረው ጀብሃ ነው፤ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ሻዕቢያ ተከሰተ፤ እርሱም ህወሃትን ወለደ፤ ህወሃትም ኢህዴንን (የአሁኑን ብአዴን) የአማርኛ ክፍል አድርጎ ከአባትና አያቶቹ በተማረው መሠረት ፈጠረ፡፡ ህወሃት ወላድ በመሆኑ የኦሮሚኛና ሌሎች “ጠቃሚ” የሆኑ የቋንቋ ክፍሎች ወለደ፣ እንደ ጭቃ እያቦካ ጠፈጠፈ፡፡

አሁን የኤርትራ የነጻነት ትግል የሚባለውን በባለቤትነት የሚወስደው ኤርትራን ነጻ አውጥቶ የሚገዛትና አንዳንዴም ለኢትዮጵያ ነጻነት ጥሩ አሳቢ እንደሆነ የሚደሰኮርለት ሻዕቢያ ነው፡፡

ሻዕቢያ የኢትዮጵያ የቅርብ ጠላት ነው በማለት አጥብቃችሁ በመቃወማችሁ የተገመገማችሁ፣ የታሰራችሁ፣ መከራ የተቀበላችሁ፣ … ያላችሁም የለቀቃችሁም የህወሃት አባላት፤ የአይደር ህጻናት ደም ከኅሊናችሁ ሊጠፋ ያልቻለ የትግራይ ተወላጆች፤ እንዲህ ያለውን ቤት ድረስ የመጣ የሻዕቢያ ድፍረት “የኤርትራ ሕዝብ የነጻነት ትግል የጀመረበት” በማለት አለባብሳችሁ ነው የምታልፉት ወይስ …?

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    September 2, 2015 05:49 am at 5:49 am

    “በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡”
    “ብሔር ብሔረሰቦች ሆኑ የኢትዮጵያ ልጆች ማለት ኤርትራውያን የየትኛው ክልል ልጆች ናቸው? ሻዕቢያ፣ ህወአት፣ ኦነግና ኦብነግ ሲጠሩ አራት ሲናገሩ አንድ፣ ሲኖሩ ጎን ለጎን፣ ሲፋቀሩ በውስጥ፣ ሲጣሉ በውጭ፣ አንድ አካል አንድ አምሳል ማለት ይህ አደለምን!?
    ** ይህ አዲስ አባባ ከተማ ለነዋሪው(ለተፎካካሪ ፓርቲ) በመንገድ ሥራ፣ በውጭ መሪዎች ስብሰባ፣ በሰልፉ ዕውቅና ማግኘት ፖሊስ ተሰላፊውን በቆመጥ በመደብደብ ወጣት ሴትና እርጉዝ አጥንት በመስብርና በመፈንከት ሲከለልና ሲከለከል..እንዴት ነው ለኤርትራውያን ሳያሳውቁም፣ ሳያስፈቅዱም፣ በማናቸውም ግዜና ወቅት፣ጥበቃ እየተደረገላቸው አጃቸውን ከፍ! ደረታቸውን ነፍተው! አንገታቸውን ቀና አድርገው! የሚጮሁት!? ግን ያለፈው ሰልፍ ኢሳያስ አፈወርቂ ከሥልጣን ይውርድ! ዲሞክራሲ! ፍትህ! ነበር ጥያቄያቸው አሁን ደሞ ሁሉን እረስተው በህወአት ተጋድሎ ድል አድርገን ከቅኝ ገዢዋ ኢትዮጵያ ነፃ የሆንበት ቀን ብለው ኢትዮጵያ ምድር ላይ ይጨፍራሉ!?
    ** እነኝህ የነፃ መሬት ባላቤቶች ፈንዳቂዎች የአሁን አልቃሾች ኢትዮጵያ ውስጥ በነፃነት እየኖሩ፣ እየሰሩና እየሰረሰሩ፣ በነፃ እየተማሩ የወደፊት ሀወአት ትግራይን ለዳግማዊ ሻዕቢያ የመሸጥ አዝማሚያ ያለው ይመስላል…ከሞላው ኤርትራዊ ኢሳያስ አፈወርቂ ብቻ የኢትዮጵያ ጠላትና ገንጣይ ሆነ!? ዛሬ የሚያለቅሱት ሁሉ የትኛውን ትግል ነው የሚዘክሩት ያው መገንጠልን አደለምን!?እንግዲህ የህወአት መናጆዎች የኦህዴድ ደሕዴን ብአዴን ይህንን ቀይ ቀለም ባንዲራ ነክሮ ከውስጥ እያባሉና እያጫረሱ ለሀገር መፍረስ አብረው እየጨፈሩ በትውልድ ባይቀልዱ የተሻለ ነው።

    “እኛም መብታችን በሀገራችን!” በግፍ በአድልዎ በበቀል ያጣነው አሰብ ወደባችን፣ሉዓላዊ ክብራችን እነሱም ወንድሞቻችን… ኢህአዴግ ልዩ ቸርና ለጋስ ሆኖ እንደ ጠ/ሚኒስትሩ አማካሪ ጌታቸው ረዳ አባባል” ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር ናት ተቃዋሚው ጎራ ምቀኛ ነው ለምን ለሱዳን መሬት ተሰጠ፣ ለጅቡቲና ኬንያ መብራትና ውሃ ተሰጠ፣ ለሌሎች ሀገሮች ለምን ዕርዳታና እገዛ ተደረገ ይላሉ ምቀኞች! ይህ የኢህአዴግ ዓላማና ፍላጎት አደለም ለጎረቤቶቻችን እንሰጣላን!” ብለዋል ስለዚህ ኢህአዴግ ሌላውን እያበላና እያስበላን እኛን እርስ በእርስ እያባላን መቀጠል የለበትም! እንቢኝ በል! ሸዋን ተበላህ በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am
  • በላይነህ ክንዴ ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ኢትዮ 360ዎች ጠቆሙ July 31, 2023 01:54 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule