• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልጅ የአባቱን ልደት ሲያከብር

September 1, 2015 09:27 am by Editor 1 Comment

በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡

ኢትዮጵያ የምትባለው አገር ጠ/ሚ/ር እንደሆኑ የሚነገርላቸው ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ የሻዕቢያን ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ የትኛውን ሻዕቢያ እንደሆነ በግልጽ ሳይጠቅሱ ሻዕቢያ እየወጋን ነው፤ ሕዝብን አስፈቅደን እርምጃ እንወስዳለን ማለታቸው አይዘነጋም፡፡

ለኤርትራ ተቆርቋሪነታቸው ወደር የሌለውና ይህም “የኤርትራ ሕዝብ ትግል ከየት ወደየት” የሚል መጽሐፍ እስኪጽፉ ያደረሳቸው ሞት የቀደማቸው መለስ በኢትዮጵያ የሻዕቢያ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ነበሩ፡፡ በዚሁ መጽሃፋቸው ላይ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው በማለት እምዬ ምኒልክን እንደ ቅኝ ገዢ የአውሮጳ ነገሥታት ኢትዮጵያንም እንደ ቅኝ ገዢ አውሮጳዊ አገር በማድረግ በማንም ቅኝ ተገዝታ የማታውቀውን ኢትዮጵያ የቅኝ ገዢነትን “ክብር አጎናጽፈዋታል”፡፡

ባለራዕዩ በዚሁ የሻዕቢያ ተላላኪነታቸው ኢሣያስን እንደ ግለሰብ “አጉራ ዘለል”፣ “ዕብድ” ፣ … እያሉ ከመዝለፍ በስተቀር ሻዕቢያን እንደ ድርጅት በከረረ ቃል ለመናገር ይከብዳቸው እንደነበር አብሮ የሚጠቀስ ቢሆንም በመለስ ፋውንዴሽን ግን የተዘነጋ “ሌጋሲያቸው” ይመስላል፡፡

የዛሬ 54ዓመት ትግል የሚባለውን የጀመረው ጀብሃ ነው፤ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ሻዕቢያ ተከሰተ፤ እርሱም ህወሃትን ወለደ፤ ህወሃትም ኢህዴንን (የአሁኑን ብአዴን) የአማርኛ ክፍል አድርጎ ከአባትና አያቶቹ በተማረው መሠረት ፈጠረ፡፡ ህወሃት ወላድ በመሆኑ የኦሮሚኛና ሌሎች “ጠቃሚ” የሆኑ የቋንቋ ክፍሎች ወለደ፣ እንደ ጭቃ እያቦካ ጠፈጠፈ፡፡

አሁን የኤርትራ የነጻነት ትግል የሚባለውን በባለቤትነት የሚወስደው ኤርትራን ነጻ አውጥቶ የሚገዛትና አንዳንዴም ለኢትዮጵያ ነጻነት ጥሩ አሳቢ እንደሆነ የሚደሰኮርለት ሻዕቢያ ነው፡፡

ሻዕቢያ የኢትዮጵያ የቅርብ ጠላት ነው በማለት አጥብቃችሁ በመቃወማችሁ የተገመገማችሁ፣ የታሰራችሁ፣ መከራ የተቀበላችሁ፣ … ያላችሁም የለቀቃችሁም የህወሃት አባላት፤ የአይደር ህጻናት ደም ከኅሊናችሁ ሊጠፋ ያልቻለ የትግራይ ተወላጆች፤ እንዲህ ያለውን ቤት ድረስ የመጣ የሻዕቢያ ድፍረት “የኤርትራ ሕዝብ የነጻነት ትግል የጀመረበት” በማለት አለባብሳችሁ ነው የምታልፉት ወይስ …?

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    September 2, 2015 05:49 am at 5:49 am

    “በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡”
    “ብሔር ብሔረሰቦች ሆኑ የኢትዮጵያ ልጆች ማለት ኤርትራውያን የየትኛው ክልል ልጆች ናቸው? ሻዕቢያ፣ ህወአት፣ ኦነግና ኦብነግ ሲጠሩ አራት ሲናገሩ አንድ፣ ሲኖሩ ጎን ለጎን፣ ሲፋቀሩ በውስጥ፣ ሲጣሉ በውጭ፣ አንድ አካል አንድ አምሳል ማለት ይህ አደለምን!?
    ** ይህ አዲስ አባባ ከተማ ለነዋሪው(ለተፎካካሪ ፓርቲ) በመንገድ ሥራ፣ በውጭ መሪዎች ስብሰባ፣ በሰልፉ ዕውቅና ማግኘት ፖሊስ ተሰላፊውን በቆመጥ በመደብደብ ወጣት ሴትና እርጉዝ አጥንት በመስብርና በመፈንከት ሲከለልና ሲከለከል..እንዴት ነው ለኤርትራውያን ሳያሳውቁም፣ ሳያስፈቅዱም፣ በማናቸውም ግዜና ወቅት፣ጥበቃ እየተደረገላቸው አጃቸውን ከፍ! ደረታቸውን ነፍተው! አንገታቸውን ቀና አድርገው! የሚጮሁት!? ግን ያለፈው ሰልፍ ኢሳያስ አፈወርቂ ከሥልጣን ይውርድ! ዲሞክራሲ! ፍትህ! ነበር ጥያቄያቸው አሁን ደሞ ሁሉን እረስተው በህወአት ተጋድሎ ድል አድርገን ከቅኝ ገዢዋ ኢትዮጵያ ነፃ የሆንበት ቀን ብለው ኢትዮጵያ ምድር ላይ ይጨፍራሉ!?
    ** እነኝህ የነፃ መሬት ባላቤቶች ፈንዳቂዎች የአሁን አልቃሾች ኢትዮጵያ ውስጥ በነፃነት እየኖሩ፣ እየሰሩና እየሰረሰሩ፣ በነፃ እየተማሩ የወደፊት ሀወአት ትግራይን ለዳግማዊ ሻዕቢያ የመሸጥ አዝማሚያ ያለው ይመስላል…ከሞላው ኤርትራዊ ኢሳያስ አፈወርቂ ብቻ የኢትዮጵያ ጠላትና ገንጣይ ሆነ!? ዛሬ የሚያለቅሱት ሁሉ የትኛውን ትግል ነው የሚዘክሩት ያው መገንጠልን አደለምን!?እንግዲህ የህወአት መናጆዎች የኦህዴድ ደሕዴን ብአዴን ይህንን ቀይ ቀለም ባንዲራ ነክሮ ከውስጥ እያባሉና እያጫረሱ ለሀገር መፍረስ አብረው እየጨፈሩ በትውልድ ባይቀልዱ የተሻለ ነው።

    “እኛም መብታችን በሀገራችን!” በግፍ በአድልዎ በበቀል ያጣነው አሰብ ወደባችን፣ሉዓላዊ ክብራችን እነሱም ወንድሞቻችን… ኢህአዴግ ልዩ ቸርና ለጋስ ሆኖ እንደ ጠ/ሚኒስትሩ አማካሪ ጌታቸው ረዳ አባባል” ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር ናት ተቃዋሚው ጎራ ምቀኛ ነው ለምን ለሱዳን መሬት ተሰጠ፣ ለጅቡቲና ኬንያ መብራትና ውሃ ተሰጠ፣ ለሌሎች ሀገሮች ለምን ዕርዳታና እገዛ ተደረገ ይላሉ ምቀኞች! ይህ የኢህአዴግ ዓላማና ፍላጎት አደለም ለጎረቤቶቻችን እንሰጣላን!” ብለዋል ስለዚህ ኢህአዴግ ሌላውን እያበላና እያስበላን እኛን እርስ በእርስ እያባላን መቀጠል የለበትም! እንቢኝ በል! ሸዋን ተበላህ በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule