• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ልጅ የአባቱን ልደት ሲያከብር

September 1, 2015 09:27 am by Editor 1 Comment

በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡

ኢትዮጵያ የምትባለው አገር ጠ/ሚ/ር እንደሆኑ የሚነገርላቸው ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ የሻዕቢያን ጉዳይ አስመልክተው ሲናገሩ የትኛውን ሻዕቢያ እንደሆነ በግልጽ ሳይጠቅሱ ሻዕቢያ እየወጋን ነው፤ ሕዝብን አስፈቅደን እርምጃ እንወስዳለን ማለታቸው አይዘነጋም፡፡

ለኤርትራ ተቆርቋሪነታቸው ወደር የሌለውና ይህም “የኤርትራ ሕዝብ ትግል ከየት ወደየት” የሚል መጽሐፍ እስኪጽፉ ያደረሳቸው ሞት የቀደማቸው መለስ በኢትዮጵያ የሻዕቢያ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ ነበሩ፡፡ በዚሁ መጽሃፋቸው ላይ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ጥያቄ ነው በማለት እምዬ ምኒልክን እንደ ቅኝ ገዢ የአውሮጳ ነገሥታት ኢትዮጵያንም እንደ ቅኝ ገዢ አውሮጳዊ አገር በማድረግ በማንም ቅኝ ተገዝታ የማታውቀውን ኢትዮጵያ የቅኝ ገዢነትን “ክብር አጎናጽፈዋታል”፡፡

ባለራዕዩ በዚሁ የሻዕቢያ ተላላኪነታቸው ኢሣያስን እንደ ግለሰብ “አጉራ ዘለል”፣ “ዕብድ” ፣ … እያሉ ከመዝለፍ በስተቀር ሻዕቢያን እንደ ድርጅት በከረረ ቃል ለመናገር ይከብዳቸው እንደነበር አብሮ የሚጠቀስ ቢሆንም በመለስ ፋውንዴሽን ግን የተዘነጋ “ሌጋሲያቸው” ይመስላል፡፡

የዛሬ 54ዓመት ትግል የሚባለውን የጀመረው ጀብሃ ነው፤ ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ሻዕቢያ ተከሰተ፤ እርሱም ህወሃትን ወለደ፤ ህወሃትም ኢህዴንን (የአሁኑን ብአዴን) የአማርኛ ክፍል አድርጎ ከአባትና አያቶቹ በተማረው መሠረት ፈጠረ፡፡ ህወሃት ወላድ በመሆኑ የኦሮሚኛና ሌሎች “ጠቃሚ” የሆኑ የቋንቋ ክፍሎች ወለደ፣ እንደ ጭቃ እያቦካ ጠፈጠፈ፡፡

አሁን የኤርትራ የነጻነት ትግል የሚባለውን በባለቤትነት የሚወስደው ኤርትራን ነጻ አውጥቶ የሚገዛትና አንዳንዴም ለኢትዮጵያ ነጻነት ጥሩ አሳቢ እንደሆነ የሚደሰኮርለት ሻዕቢያ ነው፡፡

ሻዕቢያ የኢትዮጵያ የቅርብ ጠላት ነው በማለት አጥብቃችሁ በመቃወማችሁ የተገመገማችሁ፣ የታሰራችሁ፣ መከራ የተቀበላችሁ፣ … ያላችሁም የለቀቃችሁም የህወሃት አባላት፤ የአይደር ህጻናት ደም ከኅሊናችሁ ሊጠፋ ያልቻለ የትግራይ ተወላጆች፤ እንዲህ ያለውን ቤት ድረስ የመጣ የሻዕቢያ ድፍረት “የኤርትራ ሕዝብ የነጻነት ትግል የጀመረበት” በማለት አለባብሳችሁ ነው የምታልፉት ወይስ …?

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    September 2, 2015 05:49 am at 5:49 am

    “በአዲስ አበባ የሚገኙ ኤርትራ ተወላጆች ሻዕቢያ “ትጥቅ ትግል” የጀመረበትን 54ኛ ዓመት ማክበራቸውን የህወሃት ዜና አገልግሎት ፋና ዘግቧል፡፡”
    “ብሔር ብሔረሰቦች ሆኑ የኢትዮጵያ ልጆች ማለት ኤርትራውያን የየትኛው ክልል ልጆች ናቸው? ሻዕቢያ፣ ህወአት፣ ኦነግና ኦብነግ ሲጠሩ አራት ሲናገሩ አንድ፣ ሲኖሩ ጎን ለጎን፣ ሲፋቀሩ በውስጥ፣ ሲጣሉ በውጭ፣ አንድ አካል አንድ አምሳል ማለት ይህ አደለምን!?
    ** ይህ አዲስ አባባ ከተማ ለነዋሪው(ለተፎካካሪ ፓርቲ) በመንገድ ሥራ፣ በውጭ መሪዎች ስብሰባ፣ በሰልፉ ዕውቅና ማግኘት ፖሊስ ተሰላፊውን በቆመጥ በመደብደብ ወጣት ሴትና እርጉዝ አጥንት በመስብርና በመፈንከት ሲከለልና ሲከለከል..እንዴት ነው ለኤርትራውያን ሳያሳውቁም፣ ሳያስፈቅዱም፣ በማናቸውም ግዜና ወቅት፣ጥበቃ እየተደረገላቸው አጃቸውን ከፍ! ደረታቸውን ነፍተው! አንገታቸውን ቀና አድርገው! የሚጮሁት!? ግን ያለፈው ሰልፍ ኢሳያስ አፈወርቂ ከሥልጣን ይውርድ! ዲሞክራሲ! ፍትህ! ነበር ጥያቄያቸው አሁን ደሞ ሁሉን እረስተው በህወአት ተጋድሎ ድል አድርገን ከቅኝ ገዢዋ ኢትዮጵያ ነፃ የሆንበት ቀን ብለው ኢትዮጵያ ምድር ላይ ይጨፍራሉ!?
    ** እነኝህ የነፃ መሬት ባላቤቶች ፈንዳቂዎች የአሁን አልቃሾች ኢትዮጵያ ውስጥ በነፃነት እየኖሩ፣ እየሰሩና እየሰረሰሩ፣ በነፃ እየተማሩ የወደፊት ሀወአት ትግራይን ለዳግማዊ ሻዕቢያ የመሸጥ አዝማሚያ ያለው ይመስላል…ከሞላው ኤርትራዊ ኢሳያስ አፈወርቂ ብቻ የኢትዮጵያ ጠላትና ገንጣይ ሆነ!? ዛሬ የሚያለቅሱት ሁሉ የትኛውን ትግል ነው የሚዘክሩት ያው መገንጠልን አደለምን!?እንግዲህ የህወአት መናጆዎች የኦህዴድ ደሕዴን ብአዴን ይህንን ቀይ ቀለም ባንዲራ ነክሮ ከውስጥ እያባሉና እያጫረሱ ለሀገር መፍረስ አብረው እየጨፈሩ በትውልድ ባይቀልዱ የተሻለ ነው።

    “እኛም መብታችን በሀገራችን!” በግፍ በአድልዎ በበቀል ያጣነው አሰብ ወደባችን፣ሉዓላዊ ክብራችን እነሱም ወንድሞቻችን… ኢህአዴግ ልዩ ቸርና ለጋስ ሆኖ እንደ ጠ/ሚኒስትሩ አማካሪ ጌታቸው ረዳ አባባል” ኢትዮጵያ ታላቅ ሀገር ናት ተቃዋሚው ጎራ ምቀኛ ነው ለምን ለሱዳን መሬት ተሰጠ፣ ለጅቡቲና ኬንያ መብራትና ውሃ ተሰጠ፣ ለሌሎች ሀገሮች ለምን ዕርዳታና እገዛ ተደረገ ይላሉ ምቀኞች! ይህ የኢህአዴግ ዓላማና ፍላጎት አደለም ለጎረቤቶቻችን እንሰጣላን!” ብለዋል ስለዚህ ኢህአዴግ ሌላውን እያበላና እያስበላን እኛን እርስ በእርስ እያባላን መቀጠል የለበትም! እንቢኝ በል! ሸዋን ተበላህ በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule