አቶ ዠ፣ ከ Fast Lane ዩኒቨርስቲ በተልዕኮ በአራት ወራት እድሜ የዶክትሬት ድግሪ የተጫነባቸው የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። በ“ተልዕኮ” ማለት ለ Fast Lane ዩኒቨርሲቲ ደብዳቤ መጻፍና ገንዘብ መላክ ነው ተብሎ ይታማል። ይህን ሃሜት እኔ ጭምጭታ ነው የሰማሁት። ጭምጭምታው ግን ከሁነኛ (አስተማማኝ) ሰው ነው። አቶዠ፣ቀድሞ በደርግ ጊዜ መፈክር ጸሃፊ፣ በኋላም በኢሃዲግ ጊዜ ልማታዊ ጸሃፌ ተውኔት፣ቀድሞ የኢሃዲግ ፍቅር ቤት ሥራ አስቀማጭ፣ ይቅርታ ሥራ አስኪያጅ፣ በዩናይትድ ኔሽንስ የኢትዮጵያ ተወካይ፣ ለዩናይትድ ኔሽንስ ዋና ጸሃፊነት በራስ አነሳሽነት ተወዳዳሪ፣ ወዘተርፈ...ወዘተርፈ....ወዘተርፈ....እንዳልኩት የክብር ዶክትሬት እንደሚጫንባቸው ጭምጭምታ ተሰማ። ጭምጭምታው ደግሞ ከሁነኛ ምንጮች ነው። ሆኖም ችግር … [Read more...] about የአቶ ዠ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ጉዳይ
Politics
“ወልቃይትና ጠግዴ በኢትዮጵያ ታሪክ በትግራይ ስር ሆነው አያውቁም” ታሪክ
የወልቃይት ጉዳይ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሶ ደም እያፋሰሰ ባለበት በሁኑ ወቅት ቴድሮስ አድሃኖም ወልቃይትን የትግራይ ግዛት አድርገው በመቁጠር "የአማራ ብሔር ተወላጆች ወልቃይት መጥተው መኖር ከፈለጉ የትግራይ ሕዝብ በደስታ ይቀበላቸዋል" በማልተ የትግራይ ሕዝብ ወክለው ስለ ወልቃይት የትግራይ ክልልነት በድፍረት በፌስቡክ ላይ ይህንን ብለዋል - ሙሉው ቃል ከዚህ በታች ይገኛል:- በጎንደር የተከሰተውን የማንነት ጥያቄ ሰበብ በማድረግ አንዳንድ ግለሰቦች ብጥብጥ ለማስነሣት ቢሞክሩም መንግሥታችን በሰከነ ዘዴ በአጭር ጊዜ ውስጥ በቁጥጥር ሥር አውሎታል:: የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ከአማራ ተወላጆች ጋር በመወያየትና በማሳመን የወልቃይትን መሬት የትግራይም ሆኑ የአማራ ተወላጆች በጋራ እንዲኖሩበት በማግባባት ላይ ይገኛል፡፡ ወልቃይት የአማራ ነው በማለት የሚነዛው ፕሮፓጋንዳም የሐሰት መሆኑና … [Read more...] about “ወልቃይትና ጠግዴ በኢትዮጵያ ታሪክ በትግራይ ስር ሆነው አያውቁም” ታሪክ
በጎንደር የተነሳው አመጽ እየሰፋ ነው!
በጎንደር የሰዎች ህይወት ከማለፉ በተጨማሪ ሕዝብ የማያምንባቸውንና ከትግራይ ተገንጣይ ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው ባላቸው ንብረቶች ላይ ርምጃ መውሰዱ ታውቁዋል። ማክሰኞ ሊነጋጋ አካባቢ ተነሳ የተባለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመቀላቀል ወደ ጎንደር ያመሩ ወገኖችም መበራከታቸው እየተሰማ ነው። ለዓመጹ ውጤታማነት የዘር ትግል ሳይሆን ኅብረብሔራዊ እንቅስቃሴ እንደሚበጅ ተገለጸ። አመጹ የተቀሰቀሰው የማንነት ጥያቄ ባነሱና "እኛ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም" በሚል የተነሳውን ጥያቄ ከውጤት ለማድረስ ከተመረጡት የኮሚቴ አባላት መካከል አራት የሚሆኑትን ከትግራይ የመጡ ነፍጥ አንጋቾች ከያዟቸው በኋላ እንደሆነ ለኢሳት በድምጽ ማብራሪያ የሰጡ አረጋገጠዋል። ከዚያም ኮሎኔል ዘውዱ ደመቀን ለመያዝ ሙከራ ተደረገ። ይህን ጊዜ ኮሎኔሉ "በሬን አልከፍትም ጥዬ እወድቃለሁ" በማለት ሊያስሯቸው ከመጡት ሃይሎች … [Read more...] about በጎንደር የተነሳው አመጽ እየሰፋ ነው!
“የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች እስካልተቀየሩ ድረስ ሕይወታችን የከፋ አደጋ ላይ ነው”
ዛሬ አቶ በቀለ ገርባ በውስጥ ከነቴራ፣ በቁምጣና በባዶ እግራቸው ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡ ጉዳዩን የተከታተለው ኤሊያስ ገብሩ ጎዳና ይህንን የአቶ በቀለን ንግግር በፌስቡክ ገጹ ላይ አትሞአል፡፡ ይህ ምስክርነት በፍርድ ቤት ካሰሙ በኋላ በአማርኛ በኦሮሚኛ እና በ እንግሊዝኛ በየማህበራዊ ገጾችና ድረገጾች ተሰራጭቶዋል፡፡ "በባለፈው ቀጠሯችን ለብሰን ፍርድ ቤት ልንቀርብ የነበረውን ጥቁር ልብስ አውልቁ ተባልን፡፡ አናወልቅም አለን፡፡ የፈለግነውን የመልበስ ሕገ-መንግስታዊ መብታችን ነው፡፡ ጥቁር ልብስ የለበስነውም፤ ከ50ሺህ በላይ የአንድ ብሄር ተወላጆች እስር ቤት መገኘታቸውንና በዚህ ዓመትም በጥቂት ወራት ውስጥ ከ200-300 የሚደርሱ የኦሮሚያ ክልል ተወላጆች መገደላቸውን በማዘን ለመግለጽ ነው፡፡ ድርጊታችንም ይሆን የነበረው የፍርድ ቤትን አሰራርን ምንም በማይነካ መልኩ በሰላም … [Read more...] about “የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች እስካልተቀየሩ ድረስ ሕይወታችን የከፋ አደጋ ላይ ነው”
አድዋ! 120 ዓመት!
“… የተተከለው ድንኳን ሲታይ ከብዛቱ የተነሳ አፍሪካ ኤሮጳን ለመጠራረግ የተነሳች ይመስላል፡፡ የጦርነቱ ዕለት ኢትዮጵያውያኑ ደማቅ ቀለም ያለው ካባ ለብሰው፤ ጠመንጃና ጦር ይዘው፤ ጎራዴ ታጥቀው፤ የነብር ያንበሳ ቆዳ ለብሰው፤ አዝማሪዎቹ እየዘፈኑ፤ ቄሶች፤ ልጆች፤ ሴቶች ሳይቀሩ ፀሐይዋ ፈንጠቅ ስትል በተራራው ላይ በታዩ ጊዜ የኢጣሊያን ክፍል አሸበሩት” የበርክለይ ምስክርነት፤ አጤ ምኒልክ በጳውሎስ ኞኞ፤ ገጽ 195 … [Read more...] about አድዋ! 120 ዓመት!
የህወሃት ግፍ እና የሕዝብ ፍጹም ምሬት
በኦሮሚያ የተማሪዎች ተቃውሞ የተጀመረው በኖቬምበር 12 ቀን 2015 ዓ.ም ጊንጪ በመባል በምትታወቀው ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ አዲስ አበባ በስተ ደቡብ ምዕራብ 80 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አነስተኛ ከተማ ሲሆን መንስዔውም የመንግስት ባለስልጣን አካላት በአካባቢው የሚገኘውን ደን ለኢንቨስትመንት ልማት በሚል ለመመንጠር በመሞከራቸው ነው፡፡ ተቃውሞው ወዲያው ወደ ሌሎች የኦሮሚያ ክልል አካባቢዎች የተስፋፋ ሲሆን የተቃውሞው ጥያቄም በመስፋት የአዲስ አበባ የተቀናጀ የልማት ማስተር ፕላን በመባል የሚታወቀውን የአዲስ አበባ ማዘጋጃቤት ድንበር የማስፋፋት እቅድ ተቃውሞ ያካተተ ሆኗል፡፡ ተቃውሞው እስከ ዲሰምበር ወር ሲቀጥል ገበሬዎች እና ሌሎችም ተቃውሞውን ተቀላቅለዋል፡፡ በርካታ ተቃውሞ አድራጊዎች እንዳስታወቁት መንግስት ተቃውሞውን በጉልበት ለማስቆም የፈጸመው ተግባር እና በዚህም … [Read more...] about የህወሃት ግፍ እና የሕዝብ ፍጹም ምሬት
ተቃውሞ አድራጊዎች ላይ የሚደረገው አፈና አልቀነሰም
ከኖቬምበር ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በስፋት እየተካሄደ ያለውን ሰላማዊ ተቃውሞ የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይል በጉልበት እያፈነው እንደሚገኝ ሂውማን ራይትስ ወች ዛሬ አስታወቀ፡፡ ከ2016 ዓ.ም. መነሻ ጀምሮ በእየለቱ ሰዎች እንደሚገደሉ እና በዘፈቀደ እንደሚታሰሩ ሂውማን ራይትስ ወች አስታውቋል፡፡ የወታደራዊ ሰራዊትን ያካተተው የጸጥታ ሃይል ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ የሚገኙ በርካታ ሰዎችን ቀጥታ በመተኮስ ገድሏል፡፡ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረው ያለምንም ክስ እንደታገቱ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሳምንታት የተቃውሞው ድግግሞሽ የቀነሰ መስሎ ቢታይም አፈናው ግን ቀጥሏል፡፡ “ኦሮሚያን በበርካታ የጸጥታ ሃይሎች የማጥለቅለቅ እርምጃ የሚያመለክተው በተማሪዎች፣ ገበሬዎች እና ሌሎች ተቃዋሚዎች የሚደረገውን ሰላማዊ ተቃውሞ ባለስልጣን አካላቱ በከፍተኛ ሁኔታ አለመፈለጋቸውን … [Read more...] about ተቃውሞ አድራጊዎች ላይ የሚደረገው አፈና አልቀነሰም
ጋኔኑ ማነው?
“ጋኔን ልክ ማስገባት የሚችለው … መንግሥት ነው” ጌታቸው ረዳ ታኅሳስ 6፤2008 ዓም “የታጠቁ ወንበዴዎች በየመንገዱ በየመንደሩ እየዞሩ ህዝብን የሚያሸብሩበት ሁኔታ ነው የተፈጠረው፤ ወደለየለት ሽፍትነት ተገብቶ ነው ያለው፡፡ እነዚህ ሰዎች የተላለፈላቸው መመሪያ ይሄ ነበር ወይስ አልነበረም ሌላ ጉዳይ ነው፡፡ በሀገራችን ላይ ሁከት የጠራ ወገን፣ ጋኔል የጠራ ወገን ጋኔሉን ስለመቆጣጠሩ እርግጠኛ መሆን አይችልም፡፡ አሁን የጠሯቸው ሰዎች የጠሩትን ጋኔል ስለመቆጣጠራቸው እርግጠኛ አይደሉም፡፡ ይህንን ጋኔን ልክ ማስገባት የሚችለው የተደራጀ ህዝብና መንግስት ብቻ ነው፡፡” አፈቀላጤ ጌታቸው የካቲት 11፤2008ዓ.ም ይህንን አሉ: “እኔ ሁከት የጠሩ ወገኖች ነው (ጋኔን) ያልኩት። ሁከቱን ስለማይመልሱት ሕዝብና መንግሥት ይህንን ሁከት መመለስ ይገባቸዋል፤ በአጋጣሚ የእንግሊዝኛን አባባል ወደ … [Read more...] about ጋኔኑ ማነው?
አቅም የተፈጠረላቸው ፈላሾች – ህወሃቶች
ከ1997 ምርጫ በኋላ ወደ አዲስ አበባ ከፈለሱት የክልል ነዋሪዎች መካከል ከ87 በመቶ በላይ የትግራይ ተወላጆች እንደሆኑ አንድ የስታትስቲክስ ባለስልጣን ባለሙያ ጠቆሙ። ቁጥሩ የሚያሳየው ባግባቡ ከሃብትና ንብረት፣ ወይም ከመተዳደሪያ ጋር የተመዘገቡትን ብቻ እንደሚያካትት ባለሙያው አመልክተዋል። ከዘጠና በመቶ በላይ ከሌሎች ክልሎች ወደ አዲስ አበባ የሚፈልሱት የእለት ጉርስ ፍለጋ ነው። በኢንቨስትመንት ስም በሚፈናቀሉ ዜጎች ኮቴ፣ በኮንደሚኒየም ቤቶች ዝውውር፣ መከላከያ፣ ደህንነትና ሁሉንም ዓይነት የፖሊስ ተቋማት ጨምሮ በመንግሥት መስሪያ ቤቶች ቅጥርና በመሳሰሉት ሰፊ ቁጥር ያላቸው የትግራይ ተወላጆች ወደ አዲስ አበባ ተምመዋል፤ እየተመሙም ናቸው። እንደባለሙያው የሌሎች ክልል ተወላጆች በስፋት ወደ አዲስ አበባ ቢፈልሱም፣ የትግራይ ተወላጆችን ልዩ የሚያደርገው “አቅም እየተፈጠረላቸው … [Read more...] about አቅም የተፈጠረላቸው ፈላሾች – ህወሃቶች
“አፋኝ ህጎችና ፖሊሲዎች ለማሻሻል የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ የለም”
እ.ኤ.አ. በ2015 ዓ.ም በኢትዮጵያ መንግስት በተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አባላት፣ ጋዜጠኞች፣ እና ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ አድራጊዎች ላይ እያደረገ ያለውን ጫና ቀጥሏል፤ አብዛኞቹ እንግልት፣ ዘፈቀዳዊ እስር እና በፖለቲካ የተቀናበረ ክስ ገጥመዋቿል፡፡ ገዢው ፓርቲ የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢህአዴግ) ግንቦት ወር በተካሄደው ምርጫ 547 የፓርላማ መቀመጫዎችን አሸንፏል፤ ይሄውም የሆነበት አንዱ ምክንያት ጠንካራ ተጻራሪ ሃሳብ የላቸው ወይንም ተቃዋሚዎች በመታፈናቸው ነው፡፡ በሰኔ ወር የዩናይትድ ስቴትስ (አሜሪካ) ፕሬዚደንት ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያን ከመጎብኘታቸው አስቀድሞ የተወሰኑ ታዋቂ እስረኞች ከመፈታታቸው ባሻገር በኢትዮጵያን መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና መገናኛ ብዙሃኑን አስረው የያዙትን እጅግ አፋኝ ህጎች እና ፖሊሲዎች ለማሻሻል የተደረገ መሰረታዊ … [Read more...] about “አፋኝ ህጎችና ፖሊሲዎች ለማሻሻል የተደረገ መሠረታዊ ለውጥ የለም”