• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ቴዲ አፍሮ

July 14, 2017 04:12 pm by Editor 2 Comments

  • ቴዲ “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” ዘ ጋርዲያን
  • “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ቴዲ

የፍቅር፣ የዕርቅና አንድነትን መልዕክት በማንገብ ዘፈን ዘፍኖ ገንዘብ ከመሰብሰብና ታዋቂ ከመሆን በላይ የሚለፋው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አዲሱ አልበሙ ከወጣ በኋላ ከእንግሊዙ ጋዜጣ ዘ ጋርዲያን ጋር ባደረገው ቃለምልልስ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ቁልጭ አድርጎ ተናግሯል፡፡ “በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ያለው ቴዲ “የአፍሪካ ሞዴል ነበርን” በማለትም የቀደመውን የኢትዮጵያን ታላቅነትና ክብር አስታውሷል፡፡

በቅርብ የተለቀቀውን “ኢትዮጵያ” አልበም በተመለከተና ስለ አገሩ እንዲሁም ስለ ራሱ የህይወት ፍልስፍና የዜና ዘገባ ያወጣው ዘ ጋርዲያን ቃለ ምልልሱን ያደረገው በቴዲ የመኖሪያ ቤት በመገኘት ነበር፡፡ ስለ ቴዲ የቀድሞ ሥራዎች፣ ሰው ገጭተህ ገድለሃል በሚል ክስ ተመሥርቶበት በእስር ስላሳለፈው ህይወቱ፣ አዲሱ አልበሙ በሽያጭ ቀዳሚነትን የያዘ ስለመሆኑ ወዘተ በርካታ ጉዳዮችን በዘገባው አካትቷል፡፡

“ወጣቱ ትውልድ ያለፈውን ታሪኩን በተመለከተ አጣብቂኝ ውስጥ ነው ያለው፤ (የአገራችንን) መልካም ታሪክ የማስተማር ኃላፊነት እንዳለብኝ ይሰማኛል፤ (ወጣቱ) ስላለፈው ታሪክ ስኬት ኩራት ሊሰማው ይገባል” በማለት የተናገረው ቴዎድሮስ ካሳሁን አዲሱ አልበሙ ይህንኑ የኢትዮጵያን የቀድሞ ገናናነት እንደገና በማስታወስ ለአንድነት ጥሪ የሚያደርግ ሥራ መሆኑን ተናግሯል፡፡

በእነዚህና ሌሎች የቴዲ ሥራዎች ላይ ጋዜጣው ትንታኔ ከሰጠ በኋላ ኢትዮጵያን ለመከፋፈል የኖረ ምኞት እንዳላቸው አውሮጳውያን አቅጣጫውን በመቀየር ቴዲ አፍሮን ከአጼ ቴዎድሮስ፣ ምኒልክና ኃይለሥላሴ ጋር በአንድ የዘር ቋት ውስጥ መድቦ ሲያበቃ ሁሉንም አማራ በማለት ከመሰየም አልፎ ቴዲንም የአማራ ብሔረተኝነትን ናፋቂ አድርጎ አቅርቦታል፡፡ ለዚህ አስተሳሰቡ ደጋፊ ማስረጃ ለማድረግም በቴዲ ክፍሎች ውስጥ የምኒልክ ጎራዴ፣ የኃይለሥላሴ ዘመን ሠንደቅ ዓላማና የሳቸው ፎቶ መኖሩን አብሮ አስፍሯል፡፡ ለዚህ መሰሉ ፍረጃ ቴዲ የሰጠው መልስ “ወጣቱ ትውልድ አባቶቹ ለዚህች አገር ምን እንዳደረጉ ማወቅ አለበት፤ ምኒልክ ለዚህች አገር፣ ለአንድነት እና ለጸረ ቅኝአገዛዝ መዋጋታቸው ግልጽ ነው” በማለት ኢትዮጵያዊ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ዓላማ ይዞ የተነሳ የሚመስለው ጋዜጣ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ 88 ቋንቋዎች የሚነገሩ ቢሆንም ቴዲ ግን “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” በማለት ቴዲን በዘር ሣጥን ውስጥ ከቶታል፡፡ በመቀጠልም “ከታዋቂዋ የአማራ ድምጻዊት ሒሩት በቀለ” ጉልበቶች ላይ ቁጭ ብሎ እሷ ስትዘፍን ያዳምጥ እንደ ነበር ማስታወሱን ዘግቧል፡፡ ይህ የጋዜጣው ዘገባ አገላለጽ የቀደሙትንም ሆነ አዲሶቹን የኢትዮጵያ ድምጻዊንን በህወሓት/ኢህአዴግ የዘር መስፈሪያ ውስጥ አስገብቶ ለማጥበብ የሞከረ ሆኖ ማግኘታቸውን ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ገልጸዋል፡፡

ጋዜጣው በማጠቃለያው የቴዲ ሙዚቃ ቅንብሮች ከኢትዮጵያና ከዳያስፖራው ባለፈ መልኩ በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የማይሰሙ መሆናቸውን ከገለጸ በኋላ ምክንያቱንም ሲያስረዳ ቋንቋውም ሆነ የሙዚቃው ስልት ኢትዮጵያዊ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡ ከዚህ አልፎም ቴዲን ከሙላቱ አስታጥቄና መሐሙድ አህመድ ጋር በማነጻጸር የቴዲ ሥራዎች እንደ ሁለቱ አርቲስቶች ለምዕራባውያን አድማጮች ቅቡል አለመሆናቸውን ላነሳው ሃሳብ እንደ ተጨማሪ ማድመቂያ አቅርቧል፡፡ ለዚህ ግን የቴዲ ምላሽ “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ብሏል፡፡

እንደ ሃሳብ፤ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ቴዎድሮስ ካሳሁን ኢትዮጵያዊ ድምጻዊ እንደሆነ ያምናል፡፡ በዚህ የ “ዘ ጋርዲያን” ዘገባ ላይ ቴዲን የአማራ አርቲስት ተድርጎ የቀረበው ሃተታ አግባብነት አለው ብለን አናምንም፡፡ የቴዲ አፍሮ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለዚህ የተዛባ አቀራረብ ማስተካከያ ይሆን ዘንድ በተለይ ለ “ዘ ጋርዲያን” ምላሽ ቢሰጥ ሃሳብ እናቀርባለን፡፡ (Photograph: Mulugeta Ayene AP)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    July 15, 2017 04:17 pm at 4:17 pm

    ውድ ጎልጉል፣ ቶም ለተሰኘ ለ”ዘ ጋርድያን” ጸሐፊ ሁለት ጊዜ ማብራርያ ጽፌ ሁለቱንም ጊዜ ሠርዞታል። የመጀመሪያ ቅሬታዬ በሙዚቃው ዓለም ጥላሁንን አለማንሳት አይቻልም የሚል ነው። ሁለተኛው የአገራችንን ታሪክ አለማወቁ መሐሙድ አማራ ሙዚቀኛ አይደለም፤ በአማርኛ ግን ይዘፍናል። በትግርኛ ቢዘፍን አድማጭ 100 ሺህ ሰው አይሞላም [ከትግራይ 4 ሚሊዮን ሕዝብ ሁሉም ሬዲዮ አለው ሁሉም ያደምጣል ካላልን በስተቀር]። በወላይትኛም፣ ወዘተ። አማርኛ ብዙ ሰው የሚሰማው ስለሆነ፣ ከገበያም አንጻር። በበአንጻሩ ዴጃቩ እና አባዲ ለተባሉት ሠፊ መድረክ ሰጥቶአቸዋል። ለ ዘ ጋርድያን ዋና አርታኢ ቅሬታ ማቅረብ ይኖርብናል።

    Reply
    • Editor says

      July 15, 2017 04:57 pm at 4:57 pm

      መልካም ብለዋል አለም። ሌሎችም የርስዎን አርአያነት ቢከተሉ የሚበጅ ይመስለናል። ከሁሉ በላይ ግን የቴዲ አፍሮ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ጋዜጣውን ቢያነጋግር የተሻለ መፍትሔ ያመጣል ብለን እናምናለን።

      ጊዜዎን ወስደው ስለላኩልን አስተያየት እናመሰግናለን።

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule