• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?

June 7, 2017 06:38 am by Editor 1 Comment

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል።

የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው።

ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር ቤት አብረው ታስረው እንደነበርና ጓደኛሞችም እንደነበሩ የአቶ አሰፋን ኢሜይል እንደሚፈልጉ ጭምር ገልጸው ከአውስትራሊያ አሜሪካ በሚመጡ ጊዜ ሊያገኟቸው እንደሚፈልጉ ይጽፋሉ። የቦርከና ድረገጽ አዘጋጅም ይሄንንኑ መልዕክት ለአቶ አሰፋ ይልካሉ። አቶ አሰፋም ማኬንዚን እንደሚያውቁትና ሊያገናኙትም እንደሚፈልጉ ገልጸው መልስ ይሰጣሉ። ከዛ በኋላ ግሪጎሪ ማኬንዚ እና አቶ አሰፋ በተጀመረው መስመር ተጉዘው ይገናኛሉ። በዳላስ ከተማ በሚገኝም አንድ የጣሊያን ሬስቶራንት አብረው ራት ይበላሉ። ለሦስት ሰዓት ያህል ሲጨዋወቱ ካመሹም በኋላ ለሌላ ጊዜ ቀጠሮ ይዘው ይለያያሉ።

አቶ አሰፋ ከራት በፊት የተነሱት በሚመስለው ፎቶ ላይ ጥሩ ሁኔታና ጤንነት ይታይባቸው ነበር ያሉት ቬሮኒካ፤ በማግስቱ ጠዋት ግን ሆስፒታል እንደገቡ፣ የምግብ መመረዝ ሕመም እንዳጋጠማቸው እና ይሄንኑ ለግሪጎሪ ማኬንዚም እንደጻፉ፤ ከዛ በኋላ ግን አቶ አሰፋ ከሆስፒታል ሕይወታቸው አልፎ እንደወጡ፤ አብሮ ራት የበላው እንግዳ ግን ምንም እንዳልሆነ በመግለጽ የአቶ አሰፋ ሕልፈተ ሕይወት ድረስ ያለውን ጉዳይ በዚህ ይቋጫሉ።

ከዚህ አያይዘው ለአቶ አሰፋ ሞት ምክንያት ይሆናሉ የሚሏቸውን ነገሮች ያነሳሉ። የአገር ውስጥና የውጪ አገር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ሽኩቻ እንደነበራቸው፣ የድርጅቶቹንም እኩይ ባህሪና ሴራ አጋልጠው እንደጻፉ፣ ወደፊትም እንደሚጽፉ፤ ቅራኔያቸው ከነሱ ብቻ ሳይሆን ከእጀ ረዥሙ ከሲ.አይ.ኤ.ም (CIA) ጋር እንደነበርና እሱንም ከማጋለጥ ወደ ኋላ እንዳላሉ። በዚህም ምክንያት የፖለቲካ ድርጅቶቹ ወደፊትም ሕዝብ የማያውቀው ጉዳያችንን ያወጣብናል ብለው እንደሚፈሯቸው CIAም ትንሽም ሆነ ትልቅ ጠላት ንቆ እንደማይተው ገልጸው፤ የገዳይና የተገዳይ ድራማ የሚመስል ነገር በአቶ አሰፋ ሞት እንደሚታይ ጥርጣሬያቸውን አስፍረዋል።

ጸሐፊዋ ተቆርቆሪነታቸውን ገልጸው ይህንንን መጻፋቸው ባያስወቅሳቸውም፤ ከዛ በኋላ ግን እሳቸውም ሆኑ ቤተሰብና ወዳጅ፣ አንባቢም ሆነ ሰሚ፣ ወቃሽም ሆነ ተወቃሽ አንዳቸውም ጉዳዩን ሳያነሱት ወራቶች መቆጠር ጀመሩ። ቬሮኒካ ሄንን ለመጻፍ ብቻ ሲሉ የጻፉ ስላልሆነ ከዛ በኋላ የተሰማ ወይም የተደረሰበት ነገር ካለ ቢጽፉልን መልካም ነበር። ጥርጣሬን ብቻ ጥለው ሲጠፉ ግን፤ ጥርጣሬአቸው ሌላ ጥርጣሬና ጥያቄዎች ሊያስከትል በቃ።

ለመሆኑ ቬሮኒካ ከራት በፊት ይመስላል ያሉትን የአቶ አሰፋን ፎቶ የት አዩ? አቶ አሰፋ ለግሪጎሪ ማኬንዚም የጻፉት ደብዳቤ መኖሩን በምን አወቁ? ጽሑፉንስ ያየው ማነው? እንግዳውስ ጤና መሆኑ የታወቀው እንዴት ነው? ሌላው በጥርጣሬ ውስጥ የወደቁት የፖለቲካ ድርጅቶችን ቤሮኒካ ያነሱትን ለመጠየቅ አልሻም። አፍም ብዕርም ያላቸው በመሆኑ እሱን ለነሱ ትቼ የምጠይቀውን ተጨማሪ ጥያቄ ላንሳ።

የአቶ አሰፋ ቤተሰብ ስለአሟሟታቸው የሚያውቀም ምንድነው? ሐኪምስ በምን ምክንያት እንደሞቱ ያረጋገጠበት መረጃ ምን ይላል? በርግጠኝነት የተነገርው የምግብ መመረዝስ ከምን ተነሳ? ራት ከበሉት ምግብ ከሆነ የበሉበትን የኢጣሊያን ሬስቶራንትን ስለዚሁ ጉዳይ የጠየቀ የለም ወይ? አብሮ ራት የበላው እንግዳስ ስለጉዳዩ ምን ተናገረ? እነዚህና እነዚህን የመሳሰሉን ጥያቄዎች ዓይን አፍጠው የተቀመጡ በመሆናቸው ቬሮኒካም ሆኑ ሌሎች ጉዳዩ ያገባናል የምትሉ ካላችሁ መልስ ስጡ። ተገድለውም ከሆነ “ተገደሉ”፤ የግዜሩን ሞት ሞተውም ከሆነ “ሞቱ” በሉን። አንባቢን ከጥርጣሬ ውስጥ ስለከተታችሁት የአቶ አሰፋ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ ማለቱ አይቀርም።

ቸር ይግጠመን!

ወለላዬ ከስዊድን ለጎልጉል ልከውት የታተመ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Al says

    June 17, 2017 07:28 pm at 7:28 pm

    Veronica is TPLF planted cyber task force creating confusion, spreading hate and weaken the vibrant diaspora. Open your eyes people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule