• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?

June 7, 2017 06:38 am by Editor 1 Comment

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል።

የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው።

ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር ቤት አብረው ታስረው እንደነበርና ጓደኛሞችም እንደነበሩ የአቶ አሰፋን ኢሜይል እንደሚፈልጉ ጭምር ገልጸው ከአውስትራሊያ አሜሪካ በሚመጡ ጊዜ ሊያገኟቸው እንደሚፈልጉ ይጽፋሉ። የቦርከና ድረገጽ አዘጋጅም ይሄንንኑ መልዕክት ለአቶ አሰፋ ይልካሉ። አቶ አሰፋም ማኬንዚን እንደሚያውቁትና ሊያገናኙትም እንደሚፈልጉ ገልጸው መልስ ይሰጣሉ። ከዛ በኋላ ግሪጎሪ ማኬንዚ እና አቶ አሰፋ በተጀመረው መስመር ተጉዘው ይገናኛሉ። በዳላስ ከተማ በሚገኝም አንድ የጣሊያን ሬስቶራንት አብረው ራት ይበላሉ። ለሦስት ሰዓት ያህል ሲጨዋወቱ ካመሹም በኋላ ለሌላ ጊዜ ቀጠሮ ይዘው ይለያያሉ።

አቶ አሰፋ ከራት በፊት የተነሱት በሚመስለው ፎቶ ላይ ጥሩ ሁኔታና ጤንነት ይታይባቸው ነበር ያሉት ቬሮኒካ፤ በማግስቱ ጠዋት ግን ሆስፒታል እንደገቡ፣ የምግብ መመረዝ ሕመም እንዳጋጠማቸው እና ይሄንኑ ለግሪጎሪ ማኬንዚም እንደጻፉ፤ ከዛ በኋላ ግን አቶ አሰፋ ከሆስፒታል ሕይወታቸው አልፎ እንደወጡ፤ አብሮ ራት የበላው እንግዳ ግን ምንም እንዳልሆነ በመግለጽ የአቶ አሰፋ ሕልፈተ ሕይወት ድረስ ያለውን ጉዳይ በዚህ ይቋጫሉ።

ከዚህ አያይዘው ለአቶ አሰፋ ሞት ምክንያት ይሆናሉ የሚሏቸውን ነገሮች ያነሳሉ። የአገር ውስጥና የውጪ አገር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ሽኩቻ እንደነበራቸው፣ የድርጅቶቹንም እኩይ ባህሪና ሴራ አጋልጠው እንደጻፉ፣ ወደፊትም እንደሚጽፉ፤ ቅራኔያቸው ከነሱ ብቻ ሳይሆን ከእጀ ረዥሙ ከሲ.አይ.ኤ.ም (CIA) ጋር እንደነበርና እሱንም ከማጋለጥ ወደ ኋላ እንዳላሉ። በዚህም ምክንያት የፖለቲካ ድርጅቶቹ ወደፊትም ሕዝብ የማያውቀው ጉዳያችንን ያወጣብናል ብለው እንደሚፈሯቸው CIAም ትንሽም ሆነ ትልቅ ጠላት ንቆ እንደማይተው ገልጸው፤ የገዳይና የተገዳይ ድራማ የሚመስል ነገር በአቶ አሰፋ ሞት እንደሚታይ ጥርጣሬያቸውን አስፍረዋል።

ጸሐፊዋ ተቆርቆሪነታቸውን ገልጸው ይህንንን መጻፋቸው ባያስወቅሳቸውም፤ ከዛ በኋላ ግን እሳቸውም ሆኑ ቤተሰብና ወዳጅ፣ አንባቢም ሆነ ሰሚ፣ ወቃሽም ሆነ ተወቃሽ አንዳቸውም ጉዳዩን ሳያነሱት ወራቶች መቆጠር ጀመሩ። ቬሮኒካ ሄንን ለመጻፍ ብቻ ሲሉ የጻፉ ስላልሆነ ከዛ በኋላ የተሰማ ወይም የተደረሰበት ነገር ካለ ቢጽፉልን መልካም ነበር። ጥርጣሬን ብቻ ጥለው ሲጠፉ ግን፤ ጥርጣሬአቸው ሌላ ጥርጣሬና ጥያቄዎች ሊያስከትል በቃ።

ለመሆኑ ቬሮኒካ ከራት በፊት ይመስላል ያሉትን የአቶ አሰፋን ፎቶ የት አዩ? አቶ አሰፋ ለግሪጎሪ ማኬንዚም የጻፉት ደብዳቤ መኖሩን በምን አወቁ? ጽሑፉንስ ያየው ማነው? እንግዳውስ ጤና መሆኑ የታወቀው እንዴት ነው? ሌላው በጥርጣሬ ውስጥ የወደቁት የፖለቲካ ድርጅቶችን ቤሮኒካ ያነሱትን ለመጠየቅ አልሻም። አፍም ብዕርም ያላቸው በመሆኑ እሱን ለነሱ ትቼ የምጠይቀውን ተጨማሪ ጥያቄ ላንሳ።

የአቶ አሰፋ ቤተሰብ ስለአሟሟታቸው የሚያውቀም ምንድነው? ሐኪምስ በምን ምክንያት እንደሞቱ ያረጋገጠበት መረጃ ምን ይላል? በርግጠኝነት የተነገርው የምግብ መመረዝስ ከምን ተነሳ? ራት ከበሉት ምግብ ከሆነ የበሉበትን የኢጣሊያን ሬስቶራንትን ስለዚሁ ጉዳይ የጠየቀ የለም ወይ? አብሮ ራት የበላው እንግዳስ ስለጉዳዩ ምን ተናገረ? እነዚህና እነዚህን የመሳሰሉን ጥያቄዎች ዓይን አፍጠው የተቀመጡ በመሆናቸው ቬሮኒካም ሆኑ ሌሎች ጉዳዩ ያገባናል የምትሉ ካላችሁ መልስ ስጡ። ተገድለውም ከሆነ “ተገደሉ”፤ የግዜሩን ሞት ሞተውም ከሆነ “ሞቱ” በሉን። አንባቢን ከጥርጣሬ ውስጥ ስለከተታችሁት የአቶ አሰፋ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ ማለቱ አይቀርም።

ቸር ይግጠመን!

ወለላዬ ከስዊድን ለጎልጉል ልከውት የታተመ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Al says

    June 17, 2017 07:28 pm at 7:28 pm

    Veronica is TPLF planted cyber task force creating confusion, spreading hate and weaken the vibrant diaspora. Open your eyes people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule