• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?

June 7, 2017 06:38 am by Editor 1 Comment

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል።

የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው።

ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር ቤት አብረው ታስረው እንደነበርና ጓደኛሞችም እንደነበሩ የአቶ አሰፋን ኢሜይል እንደሚፈልጉ ጭምር ገልጸው ከአውስትራሊያ አሜሪካ በሚመጡ ጊዜ ሊያገኟቸው እንደሚፈልጉ ይጽፋሉ። የቦርከና ድረገጽ አዘጋጅም ይሄንንኑ መልዕክት ለአቶ አሰፋ ይልካሉ። አቶ አሰፋም ማኬንዚን እንደሚያውቁትና ሊያገናኙትም እንደሚፈልጉ ገልጸው መልስ ይሰጣሉ። ከዛ በኋላ ግሪጎሪ ማኬንዚ እና አቶ አሰፋ በተጀመረው መስመር ተጉዘው ይገናኛሉ። በዳላስ ከተማ በሚገኝም አንድ የጣሊያን ሬስቶራንት አብረው ራት ይበላሉ። ለሦስት ሰዓት ያህል ሲጨዋወቱ ካመሹም በኋላ ለሌላ ጊዜ ቀጠሮ ይዘው ይለያያሉ።

አቶ አሰፋ ከራት በፊት የተነሱት በሚመስለው ፎቶ ላይ ጥሩ ሁኔታና ጤንነት ይታይባቸው ነበር ያሉት ቬሮኒካ፤ በማግስቱ ጠዋት ግን ሆስፒታል እንደገቡ፣ የምግብ መመረዝ ሕመም እንዳጋጠማቸው እና ይሄንኑ ለግሪጎሪ ማኬንዚም እንደጻፉ፤ ከዛ በኋላ ግን አቶ አሰፋ ከሆስፒታል ሕይወታቸው አልፎ እንደወጡ፤ አብሮ ራት የበላው እንግዳ ግን ምንም እንዳልሆነ በመግለጽ የአቶ አሰፋ ሕልፈተ ሕይወት ድረስ ያለውን ጉዳይ በዚህ ይቋጫሉ።

ከዚህ አያይዘው ለአቶ አሰፋ ሞት ምክንያት ይሆናሉ የሚሏቸውን ነገሮች ያነሳሉ። የአገር ውስጥና የውጪ አገር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ሽኩቻ እንደነበራቸው፣ የድርጅቶቹንም እኩይ ባህሪና ሴራ አጋልጠው እንደጻፉ፣ ወደፊትም እንደሚጽፉ፤ ቅራኔያቸው ከነሱ ብቻ ሳይሆን ከእጀ ረዥሙ ከሲ.አይ.ኤ.ም (CIA) ጋር እንደነበርና እሱንም ከማጋለጥ ወደ ኋላ እንዳላሉ። በዚህም ምክንያት የፖለቲካ ድርጅቶቹ ወደፊትም ሕዝብ የማያውቀው ጉዳያችንን ያወጣብናል ብለው እንደሚፈሯቸው CIAም ትንሽም ሆነ ትልቅ ጠላት ንቆ እንደማይተው ገልጸው፤ የገዳይና የተገዳይ ድራማ የሚመስል ነገር በአቶ አሰፋ ሞት እንደሚታይ ጥርጣሬያቸውን አስፍረዋል።

ጸሐፊዋ ተቆርቆሪነታቸውን ገልጸው ይህንንን መጻፋቸው ባያስወቅሳቸውም፤ ከዛ በኋላ ግን እሳቸውም ሆኑ ቤተሰብና ወዳጅ፣ አንባቢም ሆነ ሰሚ፣ ወቃሽም ሆነ ተወቃሽ አንዳቸውም ጉዳዩን ሳያነሱት ወራቶች መቆጠር ጀመሩ። ቬሮኒካ ሄንን ለመጻፍ ብቻ ሲሉ የጻፉ ስላልሆነ ከዛ በኋላ የተሰማ ወይም የተደረሰበት ነገር ካለ ቢጽፉልን መልካም ነበር። ጥርጣሬን ብቻ ጥለው ሲጠፉ ግን፤ ጥርጣሬአቸው ሌላ ጥርጣሬና ጥያቄዎች ሊያስከትል በቃ።

ለመሆኑ ቬሮኒካ ከራት በፊት ይመስላል ያሉትን የአቶ አሰፋን ፎቶ የት አዩ? አቶ አሰፋ ለግሪጎሪ ማኬንዚም የጻፉት ደብዳቤ መኖሩን በምን አወቁ? ጽሑፉንስ ያየው ማነው? እንግዳውስ ጤና መሆኑ የታወቀው እንዴት ነው? ሌላው በጥርጣሬ ውስጥ የወደቁት የፖለቲካ ድርጅቶችን ቤሮኒካ ያነሱትን ለመጠየቅ አልሻም። አፍም ብዕርም ያላቸው በመሆኑ እሱን ለነሱ ትቼ የምጠይቀውን ተጨማሪ ጥያቄ ላንሳ።

የአቶ አሰፋ ቤተሰብ ስለአሟሟታቸው የሚያውቀም ምንድነው? ሐኪምስ በምን ምክንያት እንደሞቱ ያረጋገጠበት መረጃ ምን ይላል? በርግጠኝነት የተነገርው የምግብ መመረዝስ ከምን ተነሳ? ራት ከበሉት ምግብ ከሆነ የበሉበትን የኢጣሊያን ሬስቶራንትን ስለዚሁ ጉዳይ የጠየቀ የለም ወይ? አብሮ ራት የበላው እንግዳስ ስለጉዳዩ ምን ተናገረ? እነዚህና እነዚህን የመሳሰሉን ጥያቄዎች ዓይን አፍጠው የተቀመጡ በመሆናቸው ቬሮኒካም ሆኑ ሌሎች ጉዳዩ ያገባናል የምትሉ ካላችሁ መልስ ስጡ። ተገድለውም ከሆነ “ተገደሉ”፤ የግዜሩን ሞት ሞተውም ከሆነ “ሞቱ” በሉን። አንባቢን ከጥርጣሬ ውስጥ ስለከተታችሁት የአቶ አሰፋ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ ማለቱ አይቀርም።

ቸር ይግጠመን!

ወለላዬ ከስዊድን ለጎልጉል ልከውት የታተመ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Al says

    June 17, 2017 07:28 pm at 7:28 pm

    Veronica is TPLF planted cyber task force creating confusion, spreading hate and weaken the vibrant diaspora. Open your eyes people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule