• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሲሾም ያልበላ… ድሮ ቀረ” — [የግንቦት 20 ወግ]

May 28, 2017 07:35 pm by Editor Leave a Comment

አንጀት አርስና አንገት አስደፊ አስተያየት አንጀታቸው ካረረ ሽማግሌ። በመስሪያ ቤታችን የግንቦት 20 በዓልን እያከበርን ነው። ክቡር ሰብሳቢው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ብዙ የበዙና የተባዙ የለውጥ ማሳያዎችን ሲናገሩ ቆይተው በመጨረሻ እንዲህ አሉ፡-

“…ባጭሩ ከግንቦት 20 ድል በኋላ ተቆጥሮ የማያልቅ ብዙ ለውጥ አምጥተናል። በተለይም ኪራይ ሰብሳቢነትን በመታገል ረገድ ሙስና በማኅበረሰቡ ዘንድ ነውር ሆኖ እንዲታይ አድርገናል። ሁላችሁም እንደምታውቁት ድሮ ድሮ… “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል”… እየተባለ በድፍረት ይነገር ነበር። ይህ ማለት ሲሾሙ መብላት ሲሻሩ ላላመቆጨት ወሳኝ መሆኑን ኅብረተሰቡ አምኖበት ነበር። አሁን ግን ይህ አባባል እየቀረና እየተረሳ ነው። ይህም የትግል ውጤት ነው።”

ሰብሳቢው ይህንን በክብር እየተናገሩ እያለ ጋሽ ደፋሩ እጃቸው ላጥ! አድርገው አወጡ። (ጋሽ ደፋሩ የመስሪያ ቤታችን ሽማግሌው ሠራተኛ ናቸው። እንዲያውም በቅርቡ ጡረታ ሊወጡ ነው እየተባለ ይወራል።)

“እዚህ ጋ አስተያየት አለኝ… እዚህ ጋ…” አሉ ጋሽ ደፋሩ የሰብሳቢውን ንግግር በድፍረት አቋርጠው። ሰብሳቢ ንግግሩ በመቋረጡ እየተበሳጨ…

“ለአስተያየት ዕድል እስከሚሰጣችሁ ብትጠብቁ ጥሩ ነው ጓዶች… ለማንኛውም ሽማግሌን ማክበር ስላለብን… ሀሳብዎትን ይናገሩ” ብሎ ፈቀደላቸው።

ጋሽ ደፋሩ “እህህ…እሁሁ..” ብለው ጉሮሯቸውን በመሞረድ ይህንን አሉ። “ስለፈቀድህልኝ በሥልጣን ላይ ሥልጣን ይፈቀድልህ። ስላከበርኸኝም ከጥበቃ እስከ ሚኒስትር ማዕረግ ያለው ሠራተኛ ሁሉ ያክብርህ። ሽማግሌን ማክበር ጥሩ ነው። ቢያንስ ከመረገም ያድናል። … ወደዋናው ጉዳየ ስገባ… እኔ ምለው ልጄ.. የምትናገረውን አታውቅም ልበል?”

“ማ ? እኔ ነኝ የምናገረውን የማላውቅ?” አለ ሰብሳቢው ቆጣ ብሎ።

“አወና ! አንተ ራስህ።” ጋሽ ደፋሩ ንግግራቸውን በድፍረት ቀጠሉ።

“ምን ለማለት ፈልገው ነው?” ሰብሳቢው የበለጠ ተቆጣ።

“ለማለት የፈለግሁትን እስከምል መቼ አስጨረስኸኝ። መናገር እንጅ ማዳመጥ ብሎ ነገር እኮ አልፈጠረብህም።… ባጭሩ ለማለት የፈለግሁት… ይህ “ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል” የሚለው አባባል የቀረው በእኛ ትግል ነው ስትል ትንሽም ሀፍረት ያልተሰማህ የምትናገረውን ስለማታውቅ ነው።”

“እስኪ እርስዎ ያወቁት ያስረዱኝ!” አለ ሰብሳቢው አሁንም ንግግራቸውን አቋርጦ። በእጅጉ እንደደነገጠ ፊቱ ያሳብቅበታል።

“አስረዱኝ ማለት ጥሩ። ያልተረዱትን ከተረዱት መጠየቅ የጨዋ ደንብ ነው። አየህ ልጄ…. ይህ አባባል ድሮ ድሮ ተደጋግሞ ይነገር የነበረው ብዙዎቹ ተሹመው ሳይበሉ ከሥልጣን ይወርዱ ስለነበር ነው። አሁን ግን…. ሲጀመር ተሹሞ እንደፈለገው የሚበላ ባለሥልጣን አይሻርም። ቢሻርም እንደተሾመ ይብዛም ይነስም በየአቅሙ በልቶ ስለሚሻርና ማንም በመሻሩ ሲቆጭ ስለማይታይ… አባባሉ እየቀረ ነው። እናም…የአባባሉን መቅረት መናገርህ ሐቅ ሆኖ ሳለ የመቅረቱ ምክንያት “ትግላችን ለውጥ ስላመጣ ነው” ማለትህ ግን ቅጥፈት ነው።”

ተሰብሳቢው በሳ ቅ በታጀበ ጭብጨባ….ጯ..ጯ…ጯ…ቿ..ቿ..ቿ…!!! ሰብሳቢው በሐፍረት ዝምምምም። (መላኩ አላምረው@DireTube)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions, Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule