“የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል ሲለኝ - ደነገጥኩ” የሚል አስተያየት የሰጠው ኳስ አፍቃሪ ከጎልጉል የአዲስ አበባ ወኪል ጋር የተገናኘው አዲስ አበባ ስታዲየም ነበር። ጉዳዩ ለሚዲያ ግብዓት እንደሚውል ባይረዳም ገጠመኙን ለመናገር የተገደደው ስለ ምርጫ አንስተው ሲወያዩ ነው። ድንገት ተገናኝተው ቆሎ በመገባበዝ የጀመሩት ጨዋታ ዘጋቢውን ወደ 1997 ምርጫ ትዝታ ወረወረው። ተግባብተው አወጉና ተለያዩ። የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል!! ለምን? መርዝ ዘርቶ በጥይት ለማጨድ? የስታዲየሙ ሰው የመኪና ማስጌጫ ለመግዛትና ለማስገጠም ሰባራ ባቡር እንደሄደ ይናገራል። እዛም እንደ ደረሰ የሚፈልገውን ገዝቶ እያስገጠመ ሳለ አንድ ጎረምሳ ቢጤ ይጠጋቸውና ወሬ ይጀምራል። ጎረምሳው የትግራይ ተወላጅ ነው። አንዳንድ ማስጌጫዎች የሚፈልግ ከሆነ እሱ ዘንድ በርካሽ እንደሚያገኝ እየነገረው ቃላት መለዋወጥ ጀመሩ። … [Read more...] about “የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል” ሲለኝ – ደነገጥኩ
Archives for March 2015
የቅማንት ክልል መመሥረትን በሶስት መንገዶች . . .
ጎንደር የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ ሳለሁ፤ ከጓደኞቼ መካከል ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ። አንድ ላይ የዘጠነኛ፣ የአስረኛና የአስራ አንደኛ ክፍል ተማሪዎች ነበርን። ግንብነህ አየለና አምባቸው አየለ ይባላሉ። በተለይ እሁድ እሁድ ማታ፤ ከዚያች በዚያ ወቅት ከነበረችው አንዲቷ ሲኒማ ቤት፤ ሲኒማ ጎንደር፤ የሚታዩትን ሲኒማዎች ለማየት፤ ከግማሽ ሰዓት በፊት ከአምባቸው አየለ ጋር ቆመን፤ (ሁለት ሜዟችንን -> አንድ ሽልንግ -> ሃምሳ ሳንቲም፤ በኪሳችን ቋጥረን) የሲኒማውን ማስታወቂያ ስዕሎችና ፎቶግራፎች እያየን፤ ከፎቁ ላይ የሚንቆረቆረውን የሬይ ቻርልስ “ኖ ሞር ኖ ሞር ጃክ” እየሰማን ስንጠብቅ ትዝ ይለኛል። ቀን ላይ፤ ሸጋዎቹ የዞብልና ባላጋራቸው የአፍሪቃ ቡድን እያለፉ ሌሎች ሲተኩ፤ እኒሁኑ ተተኪ ቡድኖች ሲጫወቱ ለማየት፤ ፋሲለደስ የእግር ኳስ ሜዳ ስለምንሄድ፤ የቀኑን ሲኒማ … [Read more...] about የቅማንት ክልል መመሥረትን በሶስት መንገዶች . . .
የርዕሰ አድናራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ
በእንግሊዝ ሃገር የሚገኘው ኢትዮጵያዊ ስደተኛ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታይ ገንዘብና ጉልበቱን አስተባብሮ በእግዚአብሔር ተራዳዒነት የገዛውን ህንፃ ቤተ ክርስቲያን ለወያኔ ሹማምንት አሳልፈው በመስጠት ሥልጣንና ንዋይን የሚያጋብሱ የመሰላቸው የለንደኑ ዳያብሎስ አባ ግርማ ከበደና ተከታዮቻቸው፤ የቤተ ክርስቲያኑን አባላት መብት የሚነፍግ ተግባር ፈጽመው አባላቱ በቤተ ክርስቲያኗ ንብረት እኩል የመገልገል መብታቸው እንዲከበርላቸው ጉዳያቸውን ወደ ፍርድ ቤት ወስደው በ13/02/2013 በዋለው የእንግሊዝ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ችሎት ተፈረደላቸው። ይህንን አስመልክቶ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ያስተላለፈውን ውሳኔና ያወጣውን ትዕዛዝ (interim relief order ) አባ ግርማና ተከታዮቻቸው ተግባራዊ አናደርግም በማለታቸው የፍርድ ቤትን ትዕዛዝ ባለማክበረ (በContempt of Court) ተከሰው … [Read more...] about የርዕሰ አድናራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ወቅታዊ ሁኔታ
መለሰ ዜናዊ ናፈቁኝ – የለቅሶ አየር ሰዓት አማረኝ
ሰላም ወገኖቼ!! ተጠፋፋን። ግን አንለያይም። ድሮ የዘፈን ምርጫ ክፍለ ጊዜ ነበር። እሁድ እሁድ ወታደሮች ከደጀን፣ እናትና አባት፣ ቤተሰብ ከቤት ሆነው ይኮሞክሙት ነበር። አሁን ግን ለምን ተከለከለ? ባድመ፣ ሽራሮ፣ ዛላምበሳ፣ ገመሃሎ፣ ላከ ኤርትራም አሉ፤ ዘላበድኩ መሰለኝ … ብቻ የዘፈን ምርጫ ክፍለ ጊዜው ትዝ ብሎኝ ነው። ቀጭኑ ዘ-ቄራ ነኝ!! “የለቅሶ ማስተላለፊያ የአየር ሰዓት/ክፍለ ጊዜ ቢጀመር ጥሩ ነው። ምርጫውን ያደምቀዋል” የሚል አስተያየት ሟርተኞች ያቀርባሉ። ግን ምን አለበት የከፋቸው ቢያለቅሱ። በየጓዳው እያለቀሱ ነው። አደባባይ ወጥተው ቢያለቅሱ ምን ነውር አለው? ለመለስ ደረት እየተመታ ሲለቀስ የአየር ሰዓት ተፈቅዶ የለ? ለሞተ ሰው ከተፈቀደ በህይወት ላለው፣ ግብር ለማያጓድለው ለምን ይከለካል? ወይስ ነዋሪው በሟች ተበልጧል? ነገርን ነገር ያነሳዋል እንዲባል … [Read more...] about መለሰ ዜናዊ ናፈቁኝ – የለቅሶ አየር ሰዓት አማረኝ
ሰማያዊ ቀን!
የሰማያዊ ፓርቲ እሁድ መጋቢት 20 ቀን በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂዷል፡፡ በትዕይንቱ የወጣው ሕዝብ ነጻነት እንደሚፈልግ፤ ስቃይ፣ አፈናና ስደት እንደበቃው ባሰማው መፈክር አሰምቷል፡፡ ነገረ ኢትዮጵያ ከፎቶዎች ጋር በማጀብ ከሰልፉ ዝግጅት ጀምሮ በየሰዓቱ በፌስቡክ በለቀቀው መረጃ መሠረት አዲስ አበባን ጨምሮ በጅማ፣ በአዲስ አበባ፣ በሶዶ፣ በአርባ ምንጭ፣ በጭሮ፣ በደብረ ታቦር፣ በወልቂጤና ሌሎችም ከተሞች ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ እንደተለመደው የኢህአዴግ ፖሊስ ሰልፉን በማጨናገፍ፣ ተሰላፊው ሰልፉን ጀምሮ ለማብቃት የወሰነበት ቦታ እንዳይደርስ በመከላከል ድርጅታዊና ወገናዊ ሥራውን አከናውኗል፡፡ በየከተማው በተካሄደው ትዕይንተ ሕዝብ ሰልፈኞቹ የሚከተሉትን መፈክሮች አሰምተው እንደ ነበር ከዜናው ዘገባ ለመረዳት ተችሏል፡ ነፃነት እንፈልጋለን፣ ነፃነት፣ … [Read more...] about ሰማያዊ ቀን!
ቆራጥ ጀግና ማነው?
አንድነት ይፈጠር - ሀገር ነጻ ትውጣ ንብረትም ይቅርብኝ - ምንም ነገር ልጣ ዳሩ መሀል ሳይሆን - ድንበሩ ተደፍሮ ርቱዕ አንደበት - እንዳይቀር ተቀብሮ ጋዜጠኝነትም - እንዲኖር ተከብሮ ቸነፈር ረሀብ - ሙቀቱን ሳይፈራ ውሎ የከረመ - ከታጋዮች ጋራ ጽናቱ ጠንካራ - ወገኑን የሚወድ ጌትነት የጠላ - ጭቆናን ለመናድ ነጻነት ናፋቂ - በደል የመረረው ውነተኛ ታጋይ - ቆራጥ ጀግና ማነው? … [Read more...] about ቆራጥ ጀግና ማነው?
“የስለላ ሰራተኞች መሯቸዋል፤ በጽናት የሚሰራ የለም”
በኢትዮጵያ የብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት መዋቅር ውስጥ ተመድበው የሚያገለግሉ የሰለላ ሰራተኞች በጽናት መስራት በማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸው ተሰማ። ለዓመታት የስለላ ሠራተኛና የአዲስ አበባ ቀጠና ኦፊሰር የነበረች የህወሃት አባል መክዳቷ ታወቀ። የጎልጉል ታማኝ የዜና ምንጮች አንዳሉት ድርጅቷ ህወሃትንና ታላቁን የአፈና ተቋም የስለላ ኦፊሰር የነበረችው የመክዳት ውጥኗ እውን የሆነላት ከስድስት ዓመት በኋላ ነው። በተደጋጋሚ ጊዚያት የዲፕሎማት ቪዛ እንዲሰጣት ፓስፖርቷን ለኢሚግሬሽን ብትልክም ያልተሳካላት ይህቺ የስለላ ኦፊሰር፣ በመጨረሻ የተሳካላት ስፔን አገር ለስለላ ስልጠና በማግኘቷ ነው። አዲስ አበባ የሚገኙ ባልደረቦቿ “እርሷ ዕድለኛ ናት” በማለት ለጎልጉል ዘጋቢ እንዳሳበቁት፣ ኦፊሰሯ ስፔን አገር ከባልደረቦቿ ተለይታ ያመራችው ወደ አሜሪካ ነው። እዚያም እንደ ደረሰች … [Read more...] about “የስለላ ሰራተኞች መሯቸዋል፤ በጽናት የሚሰራ የለም”
ኦህዴድ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ላይ ጀገነ
ኦነግ ሲከተል የነበረው መንገድ ስህተት እንደነበር በይፋ በመናገር የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) የተሰኘውን አዲስ ድርጅትና ወኪሎች ይዘው ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት አቶ ሌንጮ ለታ ተቀባይ በማጣታቸው ወደመጡበት የተመለሱት ኦህዴድ ባቀረበው ተቃውሞ መሆኑ ታወቀ። የኢህአዴግ አፈ ቀላጤ የስላቅ መልስ ሰጡ። ኦዴግ (ኦዲኤፍ) በ2012 ምርጫ ሊጋበዝ እንደሚችል ቃል ተገብቶለታል። የኦሮሞን ሕዝብ ትግል ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በመነጠል ከኢትዮጵያ (“አቢሲኒያ አገዛዝ”) መገንጠልን አማራጭ አድርጎ ለግማሽ ምዕተ አመት ሲወድቅ ሲነሳ የኖረውን ኦነግ ሲመሩ የነበሩት አቶ ሌንጮ ለታ፣ ወደ አዲስ አበባ ሲያቀኑ ተቃውሞ ደርሶባቸው ነበር። የቀድሞው የትግል ጉዞ ስህተት እንደነበር በይፋ አስታውቀው ለድርድር ኢህአዴግ ደጅ የዘለቁት አቶ ሌንጮ ከጉዟቸው በፊት የተነሳባቸውን ተቃውሞ … [Read more...] about ኦህዴድ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ላይ ጀገነ
Yemen in our prayers
Poor Yemen is fast becoming the new playground of every wanabe strong Arab regime in the Middle East. Yemen is a safe location where they could test their acquired toys and pretend to act like a real army fighting real battles. Yemen never have it good. It was not blessed with oil, the only commodity that sustains the Arab monarchs’. Yemen came out from the womb staggering and never seem to have acquired this thing called stability, freedom and democracy. It is said long time ago the Axumite … [Read more...] about Yemen in our prayers
የህፃናት አምባ ልጆች ትዝታና ቁጭት
ወቅቱ 1973 ዓ.ም ነበር፡፡ አገሪቱ ከተለያዩ የውስጥና የውጪ ኃይሎች ጋር ጦርነት ውስጥ የገባችበት ጊዜ ነው፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወታደሮች ልጆቻቸውን ያለ አሳዳጊ ጥለው በየጦር ሜዳው ወድቀዋል፡፡ አሳዳጊና ተንከባካቢ ያጡት ህፃናት በየጎዳናው መውደቃቸው ያሳሰበው የደርግ መንግስት፤ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በነበሩት መንግስቱ ኃይለማርያም ልዩ ትዕዛዝ የአብዮታዊት ኢትዮጵያ ህፃናት አምባ ተቋቁሞ አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ በቀድሞ አጠራር በሸዋ ክፍለ ሃገር ሀይቆችና ቡታጅራ አውራጃ፣ በአላባ ቁሊቶ ወረዳ፣ አላጌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ወላጆቻቸውን በጦርነትና በሌሎችም ሰው ሰራሽና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ያጡ ህፃናትን ተቀብሎ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውን በማሟላት፣ በትምህርትና በሥነ ምግባር ኮትኩቶ የማሳደግን ዓላማ አንግቦ የተቋቋመው አምባው፤ “ሰብለ አብዮት”፣ “መስከረም ሁለት ኦጋዴን”፣ … [Read more...] about የህፃናት አምባ ልጆች ትዝታና ቁጭት