• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል” ሲለኝ – ደነገጥኩ

March 31, 2015 08:07 am by Editor Leave a Comment

“የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል ሲለኝ – ደነገጥኩ” የሚል አስተያየት የሰጠው ኳስ አፍቃሪ ከጎልጉል የአዲስ አበባ ወኪል ጋር የተገናኘው አዲስ አበባ ስታዲየም ነበር። ጉዳዩ ለሚዲያ ግብዓት እንደሚውል ባይረዳም ገጠመኙን ለመናገር የተገደደው ስለ ምርጫ አንስተው ሲወያዩ ነው። ድንገት ተገናኝተው ቆሎ በመገባበዝ የጀመሩት ጨዋታ ዘጋቢውን ወደ 1997 ምርጫ ትዝታ ወረወረው። ተግባብተው አወጉና ተለያዩ። የትግራይ ተወላጆች ታጥቀናል!! ለምን? መርዝ ዘርቶ በጥይት ለማጨድ?

የስታዲየሙ ሰው የመኪና ማስጌጫ ለመግዛትና ለማስገጠም ሰባራ ባቡር እንደሄደ ይናገራል። እዛም እንደ ደረሰ የሚፈልገውን ገዝቶ እያስገጠመ ሳለ አንድ ጎረምሳ ቢጤ ይጠጋቸውና ወሬ ይጀምራል። ጎረምሳው የትግራይ ተወላጅ ነው። አንዳንድ ማስጌጫዎች የሚፈልግ ከሆነ እሱ ዘንድ በርካሽ እንደሚያገኝ እየነገረው ቃላት መለዋወጥ ጀመሩ። በዛው የተጀመረው ጨዋታ ስር እየሰደደ ሄደና ስለምርጫ ማውጋት ጀመሩ።

“ተቃዋሚዎች የትግራይ ህዝብን የመበቀል አጀንዳ እንጂ ሌላ ምንም ዓላማ የላቸውም። ያስጠሉኛል። ልማት አይወዱም። ከዚህ በላይ ምን እንዲደረግ ይፈልጋሉ? የትግራይ ህዝብ ነጻ አወጣቸው …” ወዘተ እንደ ሰውየው ገለጻ ጎረምሳው ብዙ ተናግሯል። በመሃሉ “አንተ ትፈራለህ እንዴ? እኔ ለምሳሌ ካንተ ጋር በፍቅር እያወራሁ ነው” ሲል ሰውየው በመካከል ጥያቄ አነሳበት። ጎረምሳው እየሳቀ ማብራሪያ ሲሰጥ ድንገት የ1997ቱን ምርጫ አነሳና ቤተሰቦቹና ታላላቅ የአገሩ ተወላጆች የነገሩትን አወሳ።

“ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ ያልታጠቅነው ሁሉ ታጥቀናል” አለ። እሱ መሳሪያ እንዳለው ሰውየው ጠየቀው? “አዎ!! ምን ችግር አለው ጠይቀህ መውሰድ ትችላለህ” ሲል እንዴትና ከነማን መሳሪያ እንደሚወስድ ተናገረ። “መሳሪያው ምን ያደርግልሃል? ምን ልታደርግበት” ሰውየው እየሳቀ “አሁን እኔን ትገለኛለህ” ሲል ጠየቀው።

ጎረምሳው ብዙ ብዙ ተናገረ። ከተለያዩ በኋላ ሰውየው ድንጋጤ ውስጥ ስለወደቀ የሰማውን ለማሰላሰል አንድ ጥግ ይዞ ተቀመጠ። “ምን እየሆነ ነው?” ሲል አሰበ። የትግራይ ተወላጆችን ለይቶ ማስታጠቅ፣ ጠላት እንዳላቸው በስውር በማስተማር ማደራጀት፣ ከመደበኛ ስራቸው ውጪም ቢሆን ባልደረቦቻቸውን እንዲሰልሉና ተጠራጣሪ ሆነው እንዲኖሩ ማድረግ፣ በቀልን እያሰቡ ውለው በቀልን እያሰቡ እንዲተኙ ማድረግ፣ ከትልቅ እስከ ትንሽ ያሉት ሁሉ ቂምና በቀል እየጋቱ ሌሎች ህዝቦች ሁሉ የትግራይ ህዝብ ጠላትና ቀን ጠባቂ እንደሆኑ በመሳመን የጥይት ስንቅ ማስያዝ … ለምን? ለምን? እስከመቼ? እንዲህና እንዲያ እያሰበ ተምታቶበት እንደከረመ ለጎልጉል ዘጋቢው አወጋው።

በ1997 ቅድመ ምርጫ የመጨረሻ ሰላማዊ ሰልፍ ወቅት የቅንጅት ሱናሚ አዲስ አበባን የዋጣት ዕለት፣ ሱናሚው አዲስ አበባን አጥለቅልቆ ኢህአዴግን በተለይም ህወሃትን ጣር ውስጥ በከተተበት ወቅት ምንም ነገር ማድረግ ይቻል ነበር። ቤተ መንግስት ገብቶ ሁሉንም የጨዋታ ህጎች መደፍጠጥ ይቻል ነበር። የጎጥም ይሁን የጎሳ ችግር የበቀል አራራ ቢኖር ኖሮ ከዚያን ጊዜ በላይ አመቺ ወቅት አልነበረም። ባድሜ ስትወረር የተመመው የኢትዮጵያ ህዝብ፣ ደጀን የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ ጉዳዩ የትግራይና የተወላጆቿ ነው ብሎ አልተቀመጠም። ፈንጂ ላይ እየሮጠ፣ ፈንጂ ላይ “እናት አገር ወይም ሞት” በማለት እየደነሰ ያለቀው ይህ ትውልድ በእውነት ቂመኛ ነው? የዘጋቢው ጥያቄ ነው!!

በርግጥ የኢትዮጵያ ህዝብ ኢህአዴግ ላይ ቢያቄምስ ይፈረድበታል? ይኮነናል? ሃጢአት ተደርጎ ይወሰድበታል? በሰላም ከሚኖርበት ቀዬ የሚፈናቀል ህዝብ ቢያቄም ኩነኔ ነው? “ከክልላችን ውጣ” ተብሎ ደብዳቤ የተጻፈለት የ1ኛ ክፍል ተማሪ ቂም አርግዞ ቂምን ቢገላገላት ይወቀሳል? በዘሩ ምክንያት በደል የሚፈጸምነት ህዝብ ግፍ በዝቶበት “ቢያስታውከው” በተነፈሱ ቁጥር “አሸባሪ” እየተባሉ እስር ቤት የሚጣሉ ወገኖች በቂም ቢመረቅዙ እንዴት “ተው” ይባላሉ? የአገሪቱን ሃብት ውስን ሰዎችና ድርጅታቸው ሲቀራመቱት በገሃድ እየታየ ሰዎች እልህ ቢጋቡ፣ ጸሎት/ዱዓ ለማድረግና ቤተ እምነትን በነጻነት ማቆም ሲከለከል ዝም ማለት ይቻላል? ጥቂቶች ህንጻ እየገነቡ ሲንፈላሰሱ ቀልባቸው የሚቆጣባቸውን “ልክ አይደላችሁም” ማለት ማን ይቻለዋል? … ዘጋቢውና ሰውየው ካነሷቸው ጥያቄዎች መካከል የሚጠቀሱ ናቸው።

ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም “የወያኔ የጥላቻ ፍሬ” በሚል ርዕስ የዛሬ ዓመት አካባቢ ባወጡት ጽሁፍ ላይ እንደጠቆሙት ግፍ ማብቂያ አለው፡- “ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ ጥላቻ ወደ ንዴት፣ ንዴት ወደ ቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉም ሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደ አውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።”

ስለዚህ አካሄድን በማሳመርና ሚዛን የጠበቀ አስተዳደር በማስፈን አገዛዝን ወደ ህዝባዊ መንግሥት በመቀየር ወግ ነው። ተስማምቶ መኖር እየተቻለ ወገን እየለዩ ማስታጠቅና ባምስትና በአስር ሰዎች የተመደበ የቀድሞ መከላከል፣ የቀድሞ ማጥቃት፣ ካልተቻለም የሚቻለውን አድርጎ የሚሆነውን ማየት በሚል እሳቤ  መንጎድ የትኛውንም ወገን እንደማይጠቅም መረዳት ግድ ይላል። በተለያዩ ወቅቶች አስተያየት የሰጡ እንደሚሉት ህወሃት እንዲህ ካለው አጉል አካሄድ ራሱን በማረቅ ብቸኛ አማራጭ ወደ ሆነው እርቅ ፊቱን እንዲያዞር የሚመለከታቸው ሁሉ ሊያሳስቡት ይገባል።

ኢህአዴግ ዙሪያ ያሉ ድቃይ ድርጅቶችም በዚህ ጉዳይ ላይ በወጉ ሊመክሩና ከወዲሁ የሚበጀውን መንገድ በመከተል ቂምና ምሱን ለማክሰም መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው ብዙዎች ይመክራሉ። ለህሊና ዋጋ በመስጠት የመርዝ እርሻን ማክሰም የጊዜው የከረመ ጥያቄ ነውና ሁሉም ልብ ሊሉት እንደሚገባ በተደጋጋሚ መዘገቡም አይዘነጋም። መርዝ እየዘሩ በጥይት አጭዶ ለመከመር መደራጀት ሌላውን ከሚያስፈራው ይልቅ የበደሉንና የቂሙን ቁስል ይበልጥ የሚያመረቅዝ ይሆናልና ህወሃት ልብ ሊገዛ እንደሚገባ የሚመክሩ ጥቂት አይደሉም። ህወሃት “ንፋስ ዘርቶ አውሎ ነፋስ አላጭድም” ማለት አይችልም – ቀን ጎዶሎ ነውና!!


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule