• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ኦህዴድ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) ላይ ጀገነ

March 27, 2015 10:01 am by Editor Leave a Comment

ኦነግ ሲከተል የነበረው መንገድ ስህተት እንደነበር በይፋ በመናገር የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ) የተሰኘውን አዲስ ድርጅትና ወኪሎች ይዘው ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት አቶ ሌንጮ ለታ ተቀባይ በማጣታቸው ወደመጡበት የተመለሱት ኦህዴድ ባቀረበው ተቃውሞ መሆኑ ታወቀ። የኢህአዴግ አፈ ቀላጤ የስላቅ መልስ ሰጡ። ኦዴግ (ኦዲኤፍ) በ2012 ምርጫ ሊጋበዝ እንደሚችል ቃል ተገብቶለታል።

የኦሮሞን ሕዝብ ትግል ከመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በመነጠል ከኢትዮጵያ (“አቢሲኒያ አገዛዝ”) መገንጠልን አማራጭ አድርጎ ለግማሽ ምዕተ አመት ሲወድቅ ሲነሳ የኖረውን ኦነግ ሲመሩ የነበሩት አቶ ሌንጮ ለታ፣ ወደ አዲስ አበባ ሲያቀኑ ተቃውሞ ደርሶባቸው ነበር። የቀድሞው የትግል ጉዞ ስህተት እንደነበር በይፋ አስታውቀው ለድርድር ኢህአዴግ ደጅ የዘለቁት አቶ ሌንጮ ከጉዟቸው በፊት የተነሳባቸውን ተቃውሞ አስመልክቶ በሰጡት ማስተባበያ ከውሳኔያቸው ንቅንቅ እንደማይሉና በመጪው ምርጫ እንደሚሳተፉ አረጋግጠው ነበር።

ባለፈው ሳምንት ይፋ በወጣ መረጃ አቶ ሌንጮና ባልደረቦቻቸው የሚያናግራቸው በማጣታቸው አዲስ አበባን ለቀው ለመውጣት ተገደዋል። የጎልጉል የዜና አቀባዮች ምንጮቻችውን ጠቅሰው ከስፍራው እንዳሉት ከሆነ እነ አቶ ሌንጮ ቀደም ሲል ቃል ተገብቶላቸው ነበር። ኢህአዴግ እነ ሌንጮ አገር ቤት እንዲገቡ ማስተማመኛ ከመስጠቱም በላይ ሊደራደራቸው ፈቃዱ ነበር። በዋናነት ግን እነ ሌንጮን ኦህዴድ ብብት ውስጥ ማስገባት ነበር ዓላማው።

ኦህዴድ በጉዳዩ ላይ ቁርጥ ያለ አቋም በመያዙና እነ ሌንጮ ድርጅቱ ደጅ እንዲጠጉ ባለመፍቀዱ፣ ኢህአዴግ ለጠቅላይ በሚጫወትበት የምርጫ ወቅት ላይ ኦህዴድን ማስቀየም ከመለስ ሞት ጋር ተያይዞ ተነስቶ የነበረውን ችግር እንዲያገረሽ ያደርገዋል ከሚል ስጋት ህወሃት እንደቀድሞው ኦህዴድ ላይ ጫና ማድረግ አልቻለም። በዚህም የተነሳ  የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዴግ ወይም በእንግሊዝኛው ኦዲኤፍ) የሚያስተናግደው ሳያገኝ ሊመለስ ችሏል።

እነ ሌንጮ ወደ አዲስ አበባ እንዲያቀኑ ፕሮፌሰር ኤፍሬም ይስሃቅና ዲማ ነገዎ ሚና ተጫውተው ነበር። በተለይም ፕሮፌሰሩ ኦስሎ በተደጋጋሚ በመምጣት ምክክር ማካሄዳቸውን እንደሚያውቁ የሚገልጹ ወገኖች፣ አቶ ሌንጮ እንዲህ ባጭር ጊዜ ዕቅዳቸው ከሽፎ ይመለሳሉ ብለው እንዳልገመቱ ይናገራሉ።

sebhat abayየጎልጉል የኦህዴድ ምንጭ “አረና እና ህወሃት መካከል ማንም ጣልቃ እንደማይገባ ሁሉ ኦዴግ እና ኦህዴድ መካከልም ይህ ሊከበር ይገባል” በሚል መቃወሚያ መቅረቡ ተናግረዋል። ምንጮቹ አያይዝውም እነ አቶ ሌንጮ በግል አቶ ስብሃትን ማግኘታቸውንና ከዛሬ አምስት አመት በኋላ በ2012 በሚካሄደው ምርጫ እንዲሳተፉ ድጋፍ እንደሚስጣቸው ማረጋገጫ እንዳገኙ አመልክተዋል። ድርጅቱ ባወጣው መግለጫ የጀመረውን መንገድ እንደሚገፋበት ገልጾዋል።

ጉዳዩን በተመለከተ የተጠየቁት የኢህአዴግ አፈቀላጤ ሽመልስ ከማል፣ “አቶ ሌንጮና የልዑካን ቡድኑ አዲስ አበባ እንደነበሩ አላውቅም ብለዋል” ሲል ሪፖርተር ዘግቧል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule